ጸደይ ባንክ በዛሬው ዕለት በ11 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ካፒታል፣ በ148 ቅርንጫፎች ሥራ እንደሚጀምር የባንኩ ቦርድ አስታውቋል።
ባንኩ ሥራ ለመጀመር የሚያስችለውን ቅድመ ሁኔታ ማጠናቀቁን አስመልክቶ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ መግለጫ ሰጥቷል።
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መኮንን የለውምወሰን፤ ባንኩ የተሳለጠ አገልግሎት መሥጠት ይችል ዘንድ ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂ የታጠቀ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ጸደይ ባንክ በአጠቃላይ 46 ቢሊየን ብር የሚገመት ሃብት እንዳለውና በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክትም ገልጸዋል።
ባንኩ 7 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የተከፈለ ጠቅላላ ካፒታል ይዞ ሥራ እንደሚጀምር ነው የተገለጸው፡፡
Published in
ዜና