በራ የመስቀል ደመራ
የአደይ ችቦ እየፋመ እየጋመ
ኢዮሃ እያስገመገመ እየተመመ
የመስቀል ደመራ
በራ።
በራ የአዲስ ዘመን ችቦ
በመስከረም ሰብል አብቦ
ከዋክብቱን ፈነጠቀ
ርችቱን አንጸባረቀ
ተኳለ አዲስ ደመቀ
መስኩን በቀለም አዝርዕት፤ በጥበብ አጥለቀለቀ
ሸለቆው ተንቆጠቆጠ፤ ተራራው አሸበረቀ
ኢዮሃ ኢዮሃ አበባዬ፤ ምድር ህይወት አፈለቀ
ነጋ የአዲስ ዘመን ችቦ
ፈካ፣ ጸዴ አረብቦ
ሌሊቱ እንደጎህ ቀደደ፣ ጨለማው እንደቀን ጠራ
እንደውቅኖስ ዕፀዋት፣ እንደጠፈር ኮከብ ደራ
ምድር ሥጋጃ ለበሰ፣ የጌጥ አልባሳት ተቀባ
ሰማይ በእልልታ አስተጋባ
ኢዮሃ መስከረም ጠባ።
ነጋ የአዲስ ዘመን ችቦ፣ ምድር ሕይወት አፈለቀች
የምስራች አዝርእቷን፤ አዲስ ቡቃያ ወለደች
የአደይ አበባን ለገሰች
ለአዲስ ዘመን አዲስ ብርሃን፤ አዲስ መስከረም ገበየች።
ነጋ፤ የአዲስ ዘመን ችቦ
ፈካ፤ ፀደይ አረብቦ
በራ፤ የመስቀል ደመራ።
(መስከረም- ፲፱፻፰፫ መስቀል አደባባይ)
Published in
የግጥም ጥግ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል