Saturday, 22 October 2022 16:23

በዛሬው ሰልፍ ከ1 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይሳተፋል ተብሎ ይጠበቃል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

በመዲናዋ አዲስ አበባ የውጪ ጣልቃገብነትን የሚያወግዝ ህዝባዊ ሰልፍ ዛሬ ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ የሚካሄድ ሲሆን በዚህ ሰልፍ ላይ ከ1 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ይሳተፋል ብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል። ህዝባዊ ሰልፉ  በዋናነት መንግስት የኢትዮጵያን ግዛታዊ አንድትና ሉአላዊነት ለማስከበር በሚያደርገው የመከላከል እርምጃ የውጭ ጣልቃ ገብነትን፣ ኢትዮጵያን ሉአላዊነት የሚጋፉ፣ ሀገራትንና የኢትዮጵያን ገፅታ  ለማበላሸት እንቅልፍ አጥተው የሚሰሩ የውጭ ሚዲያዎችን የሚያወግዝ ነው ተብሏል።
ይህ የሀገርን አንድነትና ክብር ለመጠበቅና የውጭ ጣልቃ ገብነትን በሚያዎግዘው ህዝባዊ ሰልፍ ላይ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ እንዲሳተፍ የአዲስ አበባ የሙያና ሲቪክ ማህበራት እዲሁም የፖለቲካ ፓርዎች የጋራ ምክር ቤት በጋራ በሰጡት መግለጫ ጥሪ አቅርበዋል።

Read 11102 times