Print this page
Saturday, 05 November 2022 11:41

ከሶሻል ሚዲያ በጨረፍታ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 “በሀገሬ ተስፋ አልቆርጥም የምለው ለዚህ ነው!”

      ምስጋናና ክብር ለኢትዮጵያ ሀገራችን ለተዋደቃችሁ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት!
ምስጋናና ክብር ለአማራ ፋኖ፣ ልዩ ሀይልና ሚሊሻ አባላት!
ምስጋናና ክብር ለአፋር ሚሊሻና ልዩ ሀይል አባላት!
ምስጋናና ክብር በዲፕሎማሲው ጦርነት ከምእራባውያን ጋር ለታገላችሁ በሙሉ!
ልክ የዛሬ ሁለት አመት ነው የኢትዮጵያውያንን ተስፋ ያጨለመ ዜና የሰማነው፤ በሰሜን እዝ ላይ የደረሰው ጭፍጨፋና የትህነግ የጦርነት ክተት፡፡ ዛሬ በሁለት አመቱ ደግሞ ያ ተስፋችን ላይ ብርሀን ፈንጥቋል፡፡ በእርግጥ ትህነግ ወደ ድርድር የገባው በጦርነት ተሸንፎ በመሆኑ፣ ይህ ነው የሚባል ተጽእኖ እንደማያሳድር ግልጽ ነበር።  ይሁን እንጂ የአሜሪካና የአውሮፓ ህብረት ትህነግ ላይ ነፍስ ለመዝራት በኢትዮጵያ ላይ ያሳደሩት ጫናና በተደጋጋሚ የሚያወጡት መግለጫ ሲታይ፣ ትህነግ እንዲህ በቀላሉ ትጥቁን ለመፍታትና እራሱን ለማክሰም ይስማማል ተብሎ አልተጠበቀም፡፡ ይህ ድል የመላው ኢትዮጵያውያን ድል ነው፤ ሽንፈቱ ደግሞ የምእራባውያን፡፡ በቅርቡ ምእራባውያን በዚህ መጠን ዘምተው የተሸነፉበት ግንባር ያለ አይመስለኝም፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት በአንድ ጊዜ በሶስት ጦር ሜዳዎች ድል አድርጓል፤ (1) በምድር ላይ ባለው ጦርነት (2) በዲፕሎማሲ፣ (3) በፓን አፍሪካኒዝም፡፡ ይህ ለሀገራችን ትልቅ ሀይል ነው፡፡ በሸኔና በሌሎች ታጣቂዎች ላይ በአጭር ጊዜ ተመሳሳይ ድል ማስመዝገብና ጅምሩ ያማረውን የእርሻ ምርት በስፋት ማስቀጠል ከተቻለ፣ የሀገራችንን የሰላምና የእድገት ተስፋ የተሟላና እውን ማድረግ ይቻላል፡፡ . . . ምንጊዜም ኢትዮጵያ ተስፋ አላት!
(በድሉ ዋቅጅራ)

Read 1601 times
Administrator

Latest from Administrator