Saturday, 05 November 2022 11:41

አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በ77ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያስተላለፉት መልዕክት

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   ከሶሻል ሚዲያ በጨረፍታ

   “እየሰማን ያለነው የሰላም መልእክት ሳይሆን ተከታታይ ማስጠንቀቂያዎችን ነው። ነገር ግን በርካታ የፖለቲካ ምስቅልቅሎችን ማለፍ እንደቻለች ኩሩ አፍሪካዊት ሀገር [የተባበሩት መንግሥታት] አባል ሀገራትን አንድ ነገር ማስታወስ እፈልጋለሁ።
በርካታ ችግሮቻችንን ተጋፍጠን እንዳለፍናቸው ሁሉ፣ ዛሬም የገጠሙንን ችግሮች በእርግጠኝነት እንሻገራቸዋለን። በአንዳንድ ኃያላን ሀገሮች ዐይን ፊት ልክ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት እንደሆነው [ኢትዮጵያውያን] ዐቅመቢስ መስለን እንታይ ይሆናል።
ክቡር ሊቀ መንበር፤ ...
አንድ ነገር ግን ላረጋግጥልዎት እወዳለሁ።
የውስጣችን መንፈስ ጽኑ ነው! ... የውስጣዊ መንፈሳችን ጥንካሬ ኢትዮጵያዊ ሆኖ ለመቆም ብቻ ሳይሆን ሰላማዊ ለመሆን እና ተግዳሮቶቻችንን ለመፍታትም ጭምር ነው።
የ120 ሚሊዮን ሕዝባችንን ዕድል ለ200 ኤክስፐርቶች ልንተወው አንችልም።
ይህንን ብዬ፤ ... ሁልጊዜም ቢሆን በጎ ሀሳብ ያላቸውን ተሳታፊዎች በደስታ የምንቀበል ሲሆን ሊያወግዙን እና ለሞት አሳልፈው ሊሰጡን ቀድመው የወሰኑትን ግን “የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር ይበላቸው” እላለሁ።
ስለዚህ እንደ [ኢትዮጽያ] መንግሥት ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው፤ ሁሉም የሰብአዊ መብት ጥሰት ላይ የተሳተፉትን ተጠያቂ እናደርጋቸዋለን።  ይህንንም የምናደርገው የተወሰኑ ድርጅቶችን ወይንም ኤክስፐርቶችን ለማስደሰት ሳይሆን ለራሳችን መርህ ስንል ነው። ዘላቂ ሰላም መስፈን የሚችለው በሁሉም አካባቢዎች ለተሠሩ ወንጀሎች ተጠያቂነት እና ፍትሕ ሲሰፍን ብቻ መሆኑን እንረዳለን። ነገር ግን ይህ በሀገሪቱ ባለቤትነት መመራት አለበት።
አመሠግናለሁ፤ ክቡር ሊቀ መንበር፡፡”

Read 1496 times