Saturday, 06 May 2023 18:31

የድምፃዊ አደም መሃመድ “ኦሮሚያ” አልበም ዛሬ በሂልተን ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከዚህ ቀደም በለቀቃቸው 12 የኦሮምኛ ምርጥ ነጠላ ዜማዎቹ ተወዳጅነትን ያተረፈው ድምፃዊ አደም መሀመድ የመጀመሪያ ሙሉ ስራ የሆነው “ኦሮሚያ” አልበም ዛሬ በሂልተን ሆቴል በድምቀት ይመረቃል፡፡ ድምፃዊውና የአልበሙ አስመራቂ ኮሚቴ አባላት በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ በኬና ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳብራሩት፤ አልበሙ 14 ዘፈኖችን የያዘ ሲሆን የሁሉንም የኦሮሚያ አካባቢዎች ባህል፣ ተፈጥሮና እሴት የሚዳስስ በመሆኑ መጠሪያው “ኦሮሚያ” ተብሏል።
102 ሚሊዮን ብር የወጣበትና ተሰርቶ ለመጠናቀቅ 5 ዓመታን የፈጀው አልበሙ፤ ሚክሲንግና ማስተሪንግ የተሰራው በእውቁ የሙዚቃ ሰው አበጋዝ ክብረ ወርቅ ሺዎታ ሲሆን ግጥምና ዜማ ላይ ድምፃዊ አደም መሃመድና መኮንን ለማን ጨምሮ በርካቶች ተሳትፈውበታ ተብሏል፡፡
በዚህ አልበም ምርቃ ላይ በርካታ ድምፃዊያን፣ ታዋቂ ሰዎች፣ የመንግስት የስራ ሃፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙ ሲሆን የተለያዩ የመዝናኛ ፕሮግራሞ እንደተዘጋጁ ተገልጿል። ድምፃዊ አደም  መሀመድም ከቀድሞ ነጠላ ዜማዎቹና ከአዲሱ ስራው የተመረጡ ዘፈኖችን እንደሚያቀነቅን ታውቋል።

Read 1430 times