ባለፉት አሥርታት ብዙ አስደናቂ ሰባኪዎች ታይተዋል። የኬንያው ፓስተር ማኬንዚ ግን ይለያል።
ተከታዮቹን፣ “በፍጥነት በረሃብ ሙቱና ኢየሱስን አግኙት” ብሎ ይነግራቸዋል፡፡ ያላቸውን ሳይጠራጠሩ ያደርጋሉ።
ብዙዎቹ ተከታዮቹ ታዲያ ከገጠሪቱ ኬንያ የመጡና ችግር ያቆራመዳቸው ናቸው። ያለቻቸውን ጥሪት፣ የእርሻ መሬትና ጎጆ ለእርሱ ቤተ ክርስቲያን ተናዘውለት ይቺን ዓለም ይሰናበታሉ።
ፓስተሩ በአስተምህሮው ርህራሄን አያውቅም። ሕጻናት ጭምር በረሃብ እንዲሞቱ ያበረታታል። ልጇ ‘ኢየሱስን እንዲያገኝ’ የጓጓች እናት፤ የምትወደውን የአብራኳን ክፋይ በረሃብ ጠብሳ ሕይወቱ እንድታልፍ ታደርጋለች።
ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል? ምን ብሎ ምዕመኑን ቢሰብክ ነው ነፍሳቸውን ለእርሱ የሚሰጡት? በምን ጥበብ ነው የምዕመንን አእምሮ በዚህ ደረጃ ማጠብ የሚቻለው?
(BBC)
Friday, 05 May 2023 00:00
የጎዳና ላይ ነጋዴ የነበረው ፓስተር፣ ተከታዮቹን እንዴት በረሃብ እንዲሞቱ ማሳመን ቻለ?
Written by Administrator
Published in
ባህል