በደራሲ እታለም እሸቴ የተጻፈው “የመሐረቡ ምስጢር” የተሰኘ ረዥም ልብወለድ መጽሐፍ ለንባብ የበቃ ሲሆን፤ በመጪው ሳምንት ቅዳሜ ግንቦት 12 ቀን 2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ጀምሮ በሐገር ፍቅር ቴአትር ቤት እንደሚመረቅ ታውቋል፡፡
በፖለቲካዊ ስላቅ ሥራዎቹ የሚታወቀው ሃማ ቱማ በመጽሐፉ ጀርባ ላይ ባሰፈረው አስተያየት፤ “ ---እኔ እንደ እታለም የረዥም ልብወለድ ታሪኮችን ጽፌ ለማቅረብ አልቻልኩም፡፡ እታለም ተራቀቅሁ፣ ከበድኩ፣ ተመጻደቅኹ በማይል ቋንቋ ከሦስት መቶ በላይ ገጾችን የሚያልፍና ከብዙኃኑ ህይወት ጋር የተሳሰረ ትረካን አስለምዳናለች፡፡ የተፈናቃዮችን ኑሮም እንኖረው ዘንድ በሚታመኑ ገጸባህርያት አማካኝነት አቅርባልናለች፡፡ --- እታለም ከዘመናችን የረዥም ልብወለድ ደራሲዎች አንዷና መነበብም ያለባት ናት እላለሁ፡፡” ብሏል፡፡ ደራሲዋ ከዚህ ቀደም “ምንዳ” (2001 ዓ.ም)፣ “ህልመኛዋ እናት” (2004 ዓ.ም) ፣ “ተፈናቃይ ፍቅር” (2008 ዓ.ም) የተሰኙ ረዥም ልብወለድ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አድርሳለች፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል