Print this page
Saturday, 13 May 2023 20:17

የታዋቂው የክላርኔት ተጫዋች ዳዊት ፍሬው የቀብር ስነ-ስርዓት እሁድ ይፈጸማል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስክሬኑን በነፃ አጓጉዟል


        ታዋቂው የክላርኔት መሳሪያ ተጫዋች ዳዊት ፍሬው ኃይሉ የቀብር ስነ-ስርዓት ነገ እሁድ ግንቦት 6 ቀን 2015 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ይፈጸማል። የቀብር አስፈጻሚ ኮሚቴው ትናንት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ዛሬ ከሰዓት በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን  ጸሎተ ፍትሀት የሚደረግ ሲሆን እሑድ ጠዋት በሀገር ፍቅር ቴያትር ቤት በተዘጋጀ የሽኝት ስነ-ሥርዓት ስንብት ተካሂዶ፣ ቀትር 7፡00 ሰዓት ላይ ቀብር ስነ-ስርዓቱ እንደሚፈጸም አስታውቋል።
ዳዊት በቅርቡ ለስራ ጣሊያን ሀገር በሄደበት ወቅት ባረፈበት የሆቴል ክፍል ሕይወቱ አልፎ መገኘቱ ይታወሳል። በሙዚቃ የሙያ ዘመኑ 3 የሙዚቃ አልበም የሰራው ዳዊት ፍሬው፤ የአንጋፋው ድምጻዊ ፍሬው ኃይሉ ልጅ ነው።

Read 1671 times
Administrator

Latest from Administrator