Print this page
Saturday, 20 May 2023 15:06

ኤሊት ፊንቴክስ ሶሉሽንስ “ብድር ለገበሬውና ብድር ለወጣቱ” የተሰኘ ኢንሽዬቲቭ ይፋ አደረገ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ኤሊት ፊንቴክስ ሶሉሽንስ ኃ/የተ/የግል ማኀበር፣  ኢ- ብድር በተሰኘ ሲስተም አማካኝነት፣ “ብድር ለገበሬውና ብድር ለወጣቱ”  የተሰኘ ኢንሽዬቲቭ፣ ባለፈው ረቡዕ  በሀርመኒ ሆቴል ይፋ አደረገ፡፡ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አልአዛር ሰለሞን  እንደተናገሩት፤  በማኀበራዊ ክሬዲት ኢንሽየቲቭ ሥር፣ “ብድር ለገበሬ፣ ብድር ለወጣቶች” በሚል በድምሩ ሁለት ሚሊዮን ዜጎችን በኢ - ብድር ክሬዲት ማኔጅመንት ሲስተም ለመድረስ አቅዶ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ አንድ ደንበኛ በኢ- ብድር አማካኝነት ተመዝግቦ ለባንኮች የብድር ጥያቄ ለማቅረብ አስፈላጊ መረጃዎች ከ5 ደቂቃ ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቁ የገለፁት አቶ አልአዛር፤ ባንኮች ሥራውን በተናጠል ሲያከናውኑ የብድር አናሊስስ መሥራት ብቻውን ወራትን ይፈጅባቸው እንደነበር በማስታወስ፣ ኢ- ብድር ይህን ችግርም በአስተማማኝ መልኩ ይፈታል ብለዋል። ገበሬዎች በእጃቸው የሚገኘውን መሬት፣ ከብቶች፣ የንብ ቀፎ በዋስትና በማስያዝ እንዲበደሩ የሚያስችል ሕግ ትግበራ ላይ በገጠመው ችግር በአመዛኙ ተፈፃሚ አለመሆኑን በመጥቀስ፣ የኢ-ብድር ሲስተም ይኸንን ችግር ለመቅረፍ እንደሚያስችል ተናግረዋል።


Read 1251 times
Administrator

Latest from Administrator