Print this page
Saturday, 20 May 2023 15:11

የ”ቢግ 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ” ኤግዚቢሽን ዛሬ ይጠናቀቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በዲኤምጂ ኢቨንትስና በአገር በቀሉ ኢቲኤል ኢቨንትስ ኤንድ ኮሚዩኒኬሽን ትብብር የተዘጋጀውና ለ3 ቀናት የዘለቀው የቢግ 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ ኤግዚቢሽን ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡
በግንባታው ዘርፍ የተሰማሩ አለማቀፍና አገር በቀል ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ይኸው ከግንቦት 10 ቀን 2015 ጀምሮ እስከ ዛሬ ለ3 ቀናት ክፍት ሆኖ የቆየው ኤግዚቢሽኑ፤ በዘርፉ ያሉ እድሎችንና አማራጮችን በመጠቆም በዘርፉ የተሰማሩ ግብአት አቅራቢዎች በተለያዩ ግዙፍ ግንባታዎች ላይ ተሳትፎ እንዲያደርጉና የራሳቸውን አሻራ እንዲያኖሩ ምቹ እድሎችን ፈጥሯል ተብሏል፡፡ ከ24 የአለማችን አገራት የተውጣጡ ከ140 በላይ የኤግዚቢሽን አቅራቢዎች የተሳተፉበት ይኸው ኤግዚቢሽን፤ በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴርና በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዕውቅናና ድጋፍ ተደርጎለታል፡፡በሚሊኒየም አዳራሽ የተካሄደውና በቆየው ኢግዝቢሽን ላይ ከ6ሺ በላይ የህንፃ ንድፍና ግንባታ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች፣ የህንፃ ጥገናና የንብረት አስተዳደር ባለሙያዎችና እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ ከሆኑ የዘርፉ አካላት እና ልሂቃን ጋር በአንድ መድረክ ለመገናኘት ያስቻለም ነው፡፡ ቢግ 5 በመካከለኛው ምስራቅና በአፍሪካ በግንባታ እንዱስትሪ ውስጥ ከአራት አስርት አመታት በላይ ግንባር ቀደም ሆኖ ቆይቷል፡፡
ቢግ 5 ኮንስትራክት፤ ኢትዮጵያ የሀገር ውስጥና የውጪ ኩባንያዎች ሙያዊ ክህሎታቸውንና እውቀታቸውን ለኢትዮጵያ የግንባታ እንዱስትሪ የሚያሳዩበት ሁነኛ መንገድ እንደሆነም በዚሁ ጊዜ ተገልጿል፡፡


Read 1188 times
Administrator

Latest from Administrator