Sunday, 31 March 2024 00:00

በ45ኛው ዓለም አገር አቋራጭ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የሁለተኛነት ደረጃ በመያዝ ጨርሳለች፡፡

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በሰርቢያ ቤልግሬድ በተካሄደው የ45ኛው ዓለም   አገር አቋራጭ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአምስት ምድቦች ማለትም  8ኪ.ሜ. ከ20 ዓመት በታች  ወንዶች  ፣ 6 ኪ.ሜ. ከ20 ዓመት በታች  ሴቶች  ፣ 4x2 ኪ.ሜ የድብልቅ ሪሌ ሴት/ወንድ  ፣ የ10 ኪ.ሜ. የአዋቂ ሴቶች እና አዋቂ ወንዶች  በተካተቱበት ውድድር ከ51 አገራት  የመጡ 485 የሚሆኑ አትሌቶች ተፎካክረውበታል።  በዚህም ውድድር ኢትዮጵያ በ14 ሴት እና በ14 ወንድ በ28 አትሌቶች የተወከለች ሲሆን በ ሁለት ወርቅ ፣በስድስት ብር እና በሁለት ነሃስ በአጠቃላይ በ10 ሜዳሊያ ከአለም የሁለተኛነት ደረጃ በመያዝ ውድድሩርን ጨርሳለች ፡፡

Read 374 times Last modified on Tuesday, 02 April 2024 11:04