በደራሲና ገጣሚ ሚካኤል አስጨናቂ (ኢ/ር) የተሰናዳው የጸሐይ እግሮች የግጥም መፅሐፍ ለንባብ በቃ። መፅሐፉ በፍቅር በማህበራዊ ጉዳይ፣ በፖለቲካና በበርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ጠንካራ ሀሳቦች የተዳሰሱባቸው 75 ግጥሞችን ያካተተ ነው።
በመፅሐፉ ጀርባ ላይ አስተያየታቸውን ያሰፈሩት ደራሲና ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም፣ ገጣሚና ደራሲ ሰለሞን ሳህለ ትዕዛዙ ና ገጣሚና ደራሲ አሌክስ አብርሃም እንደገለፁት፤ ገጣሚና ደራሲ ወጣት ሚካኤል አስጨናቂ (ኢ/ር) ይህ የግጥም መድብል እንኳን ለግጥም አፍቃሪያን ከግጥም ራቅ ላሉ ሁሉ ግጥም ምን ማለት እንደሆነ ማሳያ ስለመሆኑ ብሎም ገጣሚና ደራሲው ሚካኤል የጎልማሳን ሃሳብ የትልቅ ሰው አስተውሎትን በውጥጡ አጣምሮ የያዘ ወጣት ስለመሆኑና በግጥሞቹ የማይደርስበትና የማይዳስሰው ሀሳብ እንደሌለ እንዲሁም ያልተዳሰሰ የስሜታችን ክፍል እንደሌለ መስክረዋል።
የጸሐይ እግሮች የግጥም ስብስብ መፅሐፍ በ108 ገፅ ተቀንብቦ በ250 ብር ለገበያ ቀርቧል። ደራሲና ገጣሚ ሚካኤል አስጨናቂ (ኢ/ር) ከዚህ ቀደም “ተቤራ” እና “ሸግዬ ሸጊቱ” የተሰኙ ሁለት የአጫጭር ልቦለዶች ስብስብ መፅሀፎችን ለንባብ ማብቃቱ አይዘነጋም።
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና