ለመጀመሪያ ጊዜ በ2012 ዓ.ም ታትሞ ለንባብ የበቃውና ተወዳጅነትን አትርፎ በዚያው ዓመት ብቻ አራት ጊዜ ታትሞ ዝናን ያተረፈው የደራሲ ሜሪ ፈለቀ "ጠበኛ እውነቶች" መጽሐፍ፤ ከሦስት ዓመት ቆይታ በኋላ አምስተኛ ዕትም መጽሐፍ ለአንባቢያን ቀርቧል።
"ጠበኛ እውነቶች" በ4 ክፍሎች የተከፈለ ልብወለድ ሲሆን፤ የተለያየ ማህበራዊና ግላዊ ሕይወትን የሚዳስስ መፅሐፍ ነው።
መጽሐፉ በ252 ገጾች የተቀነበበ ሲሆን፤ በውስጡ የተካተቱ አራቱ ታሪኮች፡- “ቅዳሴና ቀረርቶ፣ ቀላውጦ ማስመለስ፣ እናቴን ተመኘኋት፣ ምርጫ አልባ ምርጫ” ይሰኛሉ ::
"ጠበኛ እውነቶች"፤ በሁሉም መጻሕፍት መደብሮች እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡