Thursday, 24 October 2024 00:00

የኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 3.7 ሚ. ዶላር እንዲከፍለው ጠየቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ 3.7 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት የረጅም ጊዜ ዕዳውን እንዲከፍል ጠየቀ፡፡

የኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን በጻፈው ደብዳቤ፣ ይህ ዕዳ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የቆየ መሆኑን አሰታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን በረራ ያቆመው ከኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት በፊት ነበር፡፡ በኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን እየተጠየቀ ያለው ክፍያ እ.ኤ.አ የ1997/1998 ዓ.ም ነው ተብሏል።

ይህን ተከትሎም፣ የኤርትራ መንግስት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ኤርትራ ውስጥ በሚገኝ ፍርድ ቤት መክሰሱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የኤርትራ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን፣ አየር መንገዱ በኤርትራ የሚያደርገውን በረራ እስከ ሴፕቴምበር 30/ 2024 እንዲያቆም የሰጠውን የጊዜ ገደብ ተከትሎ፣ አየር መንገዱ ባለፈው ወር፣ በረራውን ማቆሙ ይታወቃል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሃላፊዎች ባለፈው ወር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የገንዘቡን መጠን ሳይጠቅሱ፣ የኤርትራ መንግስት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዕዳ እንዳለበት ገልጸው ነበር፤ የገንዘቡን መጠን ሳይገልጹ።

የኤርትራ መንግሥት፣ ለአየር መንገዱ መክፈል ያለበት የ3 ሚሊዮን ዶላር ዕዳ እንዳለበት ተነግሯል፡፡

Read 1299 times