Friday, 06 December 2024 20:58

በኢትዮጵያ የሚኖሩትን የውጭ አገር ሰዎችን ያዋረደ ፣ የማይገባም ቃል የተናገረ እንደ ሕጉ በብርቱ ቅጣት ይቀጣል !!!

Written by 
Rate this item
(2 votes)

"የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ለሕዝብ ማስታወቂያ"

ከዚህ ቀድሞ በመስከረም 11 ቀን 1928 ዓ.ም በተነገረው አዋጅ እንደሰማችሁት የኢጣልያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ የአጥቂነት ሥራ በመሥራቱ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ከተነሣበት ጠላት እንዲከላከል ምንም ቢታዘዝ ጠላት የተባሉት ወሰን አልፈው መሣሪያ ይዘው የወገኖቻችንን የኢትዮጵያን ሰዎች ደም ለማፍሰስ የሚመጡ ኢጣልያኖች ናቸው እንጂ በአዲስ አበባ ከተማም ቢሆን ከከተማ ውጭም ቢሆን በኢትዮጵያ የሰላማዊነት ሥራ እየሠሩ ለመኖር የመጡት አይደሉምና የኢትዮጵያ ሕዝብ በእንግዳ ተቀባይነቱና በአክባሪነቱ ከውጭ አገር ሰዎች ጋራ ተስማምቶ በሳላም በመኖሩ በዓለም የተመሰገነ ስለሆነ ይህ መልካም ስማችን ሳይጠፋ ተከብሮ እንዲኖር ገፍቶ የመጣውን ጠላታችንን ወደድንበራችን ሒደን ለመመለስ ከማሰብ በቀር በመካከላችን እኛን ዘመድ አድርገው በሚኖሩ የውጭ አገር ሰዎች ላይ ማናቸውንም የጠላትነት አሳብ የሚገልጥ ነገር እንዳታደርጉ እናስታውቃለን። አሁን ከኢጣልያን ጋራ በተነሣው ጠብ ምክንያት በማስፈራራት በመጋፋት ወይም የማይገባ ቃል በመናገር ይህን በመሰለ አደራረግ ሁሉ በኢትዮጵያ የሚኖሩትን የውጭ አገር ሰዎች ያዋረደ፥ የማይገባም ቃል የተናገረ እንደ ሕጉ በብርቱ ቅጣት ይቀጣል።

መስከረም 14 ቀን 1928 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከንቲባ

ምንጭ:- ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ

Read 306 times