በ28ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ለቀጣይ አራት አመት ፌዴሬሽኑን በፕሬዝዳንት ለመምራት ምርጫ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ለፕሬዝደንትነት 6 እጩዎች የቀረቡ ሲሆን፤ ፕሮፋይላቸውም ለጉባኤው ቀርቧል፡፡
አስመራጭ ኮሚቴው ማብራሪያ እየሰጠ ነው፡፡
1.ገ/እግዚአብሄር ገ/ማርያም... ከትግራይ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
2.አቶ ያዬህ አዲስ.. ከአማራ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
3.ስለሺ ስህን... ከኦሮሚያ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
4.ሪሳል ኦፒዮ... ከጋምቤላ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
5.አቶ ዱቤ ጅሎ... ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እንዲሁም፤
6. ኮ/ር ግርማ ዳባ... ከደቡብ ኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ለመሆን እየተወዳደሩ ይገኛል፡፡
በምርጫው ሂደት 27 ድምጽ ሰጪዎች አሉ፡፡