በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የደራሲ ሌሊሳ ግርማ “በታችም በምድር” የተሰኘው ወጥ የልቦለድ መፅሐፍ በነገው ዕለት በገበያ ላይ ይውላል፡፡
በተለያዩ መጣጥፎችና አጭር ልብ ወለድ ጽሁፎች በአንባቢያን ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈው ሌሊሳ ግርማ፤ አሁን ደግሞ በመጀመሪያ የወጥ ልቦለድ ድርሰት መጥቻለሁ እያለ ነው፡፡
ደራሲ ሌሊሳ ግርማ፤ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በሚያቀርባቸው ጥበባዊ መጣጥፎቹም ይታወቃል፡፡
ደራሲው ከዚህ ቀደም “የንፋስ ህልም እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች”፣ “አፍሮ ጋዳ”፣ “መሬት - አየር - ሰማይ”፣ “የሰከረ እውነታ”፣ “እስቲ ሙዚቃ”፣ “ነፀብራቅ”፣ “ይመስላል ዘላለም”፣ የሚሰኙ የመጣጥፍና የአጭር ልብ ወለድ ስብስብ መድበሎችን ለአንባቢያን ማበርከቱ ይታወሳል፡፡
የመጽሐፉ አሳታሚ ዋሊያ መፅሐፍት ድርጅት ሲሆን፤ መጽሐፉ ከነገው ዕለት ጀምሮ በከተማዋ በሚገኙ መጻሕፍት ቤቶች ሁሉ ለገበያ እንደሚውል ታውቋል፡፡