Wednesday, 12 February 2025 20:34

“ሳላዛት” ረዥም ልብወለድ ለገበያ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በአብርሃም ገነት የተጻፈው “ሳላዛት” የተሰኘ ረዥም ልብወለድ መጽሐፍ፤ ሰሞኑን ገበያ ላይ እንደዋለ ደራሲው ለአዲስ አድማስ ገለጸ፡፡

በ500 ብር ለሽያጭ የቀረበው ልብወለድ መጽሐፉ፤ በጃፋርና በሀሁ መጽሐፍ መደብሮች ማግኘት እንደሚቻል ታውቋል፡፡

አብርሃም ገነት በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በሚጽፋቸው ተወዳጅ አጫጭር ልብወለዶቹና ወጎቹም ይታወቃል፡፡

“ሳላዛት” በረዥም ልብወለድ ዘርፍ፣ ለጸሃፊው የበኩር ሥራው እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

****
"አለማችን ፕላኔታዊ ውሕደት ያስፈልጋታል"

”--ዓለምን በአንድ ፌደሬሽን ማሰባሰብ ግቡ ሰዋዊና ፕላኔታዊ አንድነት ለማምጣት ቢሆንም ውጤቱ ግን ከዚህ ያለፈ ነው። ዓለምን በአንድ ፕላኔታዊ ፌደሬሽን ማሰባሰብ ያስፈለገው ጦርነትን ለማስቀረት፣ ሰላምና ፍትሕን ለማስፈን፣ የምድር አየር ንብረት ለሰው ልጅና ለሌሎችም ፍጡራን ተስማሚ ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግና ስልጣኔን በተለይም የህዋ ስልጣኔን ለማቀላጠፍ ነው። ስለ ህዋ ስልጣኔ በቀጣዩ ሁለንታዊ መድረክ ስለምናወሳ አሁን በዝርዝር አንሄድበትም። አስተዳደርን በተመለከተ ይህ ፌደሬሽን፣ ዓለምን ጠቅልሎ ይዞ የሚገዛ ተደርጎ መታሰብ የለበትም። አሁን በፌደሬሽኑ ስር ያሉ ሀገራትን እውነታ በተግባር ማየት ትችላላችሁ። የፌደሬሽኑ ስልጣን እንደ መከላከያ፣ የህዋ ምርምር፣ አየር ንብረትና የውጭ ግንኙነት ባሉ የተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ነው። እነዚህ ጉዳዮች በቁጥር ውስን ቢሆኑም የምድርንና የሰው ልጅን ዕጣ የሚወስኑ ታላላቅ ጉዳዮች ናቸው። እነዚህ ታላላቅ ጉዳዮች ላይ ስኬት ማምጣት የሚቻለው በሀገራት ደረጃ በተበጣጠሰ ሁኔታ ሳይሆን እንደ ፕላኔት በአንድ ማዕከል መሥራት ሲቻል ነው። ከዚህ ውጭ ሀገራቱ ራሳቸውን ነው የሚያስተዳድሩት። ዓለም በሙሉ በፌደሬሽኑ ስትካተት ደግሞ የፌደሬሽኑ የውጭ ግንኙነት ስልጣን ፕላኔቷን ወደ መወከል ይሸጋገራል።”

( ከ”ሳላዛት“ የተቀነጨበ)
***

መጽሐፉ፤ በአዲስ አበባ በጃፋር እና ሀሁ መጽሐፍ መደብሮች፣ እንዲሁም በባሕርዳር አዳነ መፅሐፍ መደብርና በሌሎች የክፍለ ሀገር ከተሞች መፅሐፍ መደብሮችም ይገኛል፡፡
በቀጥታ መግዛት ለምትፈልጉ ባሕር ዳር፡- 0910625217 አዲስ አበባ፡- 091 396 0314 ወይም 091 128 0984 ደዉሎ ማግኘት ይቻላል፡፡

Read 1278 times