የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አሜሪካ ከማምራቱ በፊት የአዲስ አበባ ዝግጅቱን በዛሬው ዕለት አገባዷል።
ብሔራዊ ቡድኑ ዛሬ ከስሪ ፖይንት አካዳሚ ጋር የልምምድ ጨዋታ ያከናወነ ሲሆን፤ በዚህም 1-0 ማሸነፍ ችሏል።
31 አባላትን የያዘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ልዑክ፣ ዛሬ ምሽት 4:50 ከአዲስ አበባ በመነሳት በሮም በኩል ትራንዚት አድርጎ ረቡዕ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ምሽት 1:00 ገደማ አሜሪካ እንደሚደርስ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

