ዛሬ በተደረገው የወንዶች 100 ሜትር ፍጻሜ ጀማይካውያኑ 1ኛ እና 2ኛ ወጥተዋል፡፡
ኦብሊኬ ሴቪሊ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ የገባበት 9 ሰከንድ 77 ማይክሮ ሰከንድ የግል ምርጥ ሰዓቱም ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
ለመጨረሻ ጊዜ በ2015 የቤጂንግ ዓለም ሻምፒዮና በአትሌት ዩሲያን ቦልት የወርቅ ሜዳልያ ያገኝችው ጃማይካ፤ ከ10 ዓመት በኋላ ከወርቅ ሜዳልያው ጋር ተገናኝታለች፡፡
ሌላኛው ጃማይካዊ ኪሻኒ ቶምሰን 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል፡፡ አሜሪካዊው ኖህ ላይስ 3ኛ ደረጃን አግኝቷል፡፡
በሴቶች 100 ሜትር ፍጻሜ ደግሞ አሜሪካዊቷ ጀፈርሰን ውድን አሸንፋለች፡፡
Ebc sport-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

