Wednesday, 01 October 2025 12:43

“ኢትዮጵያ ኬንያን ከኃይል መቋረጥና ከፈረቃ ታድጋለች”

Written by 
Rate this item
(3 votes)
ኬንያ ከውጭ ከምታገኘው አጠቃላይ የሃይል አቅርቦት 83 በመቶውን ኢትዮጵያ እንደምታቀርብ ተገለጸ፡፡ በዚህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊየን ዶላር ገደማ ማዳን ችላለች ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያ በተያዘው ዓመት እስከ ሰኔ 2025 ድረስ ኬንያ ከውጭ ካስገባችው ጠቅላላ የኤሌክትሪክ ሃይል 83 በመቶውን በመሸፈን ፣ የኬንያ ቀዳሚ የኃይል ምንጭ መሆኗ ተጠቁሟል፡፡
የኬንያው ካፒታል ኤፍ ኤም የአገሪቱን የኢነርጂና ነዳጅ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የኢትዮጵያ የሃይል አቅርቦት ከአገር ውስጥ የኃይል ማመንጫ የበለጠ ወጪ ቆጣቢ ሲሆን፤ ይህም ኬንያ በዓመት 10 ሚሊዮን ዶላር እንድታድን ያስችላታል፡፡
የኬንያው ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ጋዜጣ በበኩሉ፤ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት በኬንያ ሊፈጠር የሚችለውን የኃይል ቀውስ በመከላከል ረገድ ወሳኝ ነው ሲል ገልፆታል፡፡
“ኢትዮጵያ ኬንያን ከመብራት መጥፋትና ከፈረቃ ታድጋለች” ሲልም ጋዜጣው ዘግቧል፡፡
AS-
ቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 1838 times