ምንም እንኳን በጋዛ ሰርጥ ውስጥ ከፍተኛ ጦርነትና ውድመት የቀጠለ ቢሆንም፣ ፍልስጤማውያን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የታደሙበትና ለ50 ጥንዶች የሚሆን ታላቅ የጅምላ ሰርግ ስነ-ስርዓት አካሂደዋል።
ይህንን የጅምላ ሰርግ ያዘጋጀውና ሙሉ ወጪውን የሸፈነው "አይ ኤች ኤች" የተባለው የቱርክ ሰብአዊ እርዳታ ድርጅት ነው።
ከቅርብ ጊዜው ጦርነት በኋላ በጋዛ የጋብቻ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ የተቀየረ ሲሆን፤ ቀደም ሲል ጥንዶች ተጋብተው ወደ ትዳር ቤታቸው ይገቡ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን ተጋብተው የሚገቡት ወደ "ትዳር ድንኳን" ነው — እሱም እራሱ ከተገኘ።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

