Tuesday, 26 May 2026 08:57

ሩሲያ የውጭ ዜጎችና ዲፕሎማቶች የኪቭ ከተማን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)
ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪቭ በሚገኙ የወታደራዊና ከመንግሥት ጋር ግንኙነት ያላቸው ተቋማት ላይ “ስልታዊ ጥቃቶችን” ለመሰንዘር መዘጋጀቷን ይፋ አድርጋለች። ይህንን ተከትሎም በኪቭ የሚገኙ የውጭ አገር ዜጎች፣ ዲፕሎማቶችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በአስቸኳይ ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ይህ የሞስኮ ከባድ ማስጠንቀቂያ የወጣው፣ ሩሲያ በቅርቡ በኪቭ ላይ ካደረገቻቸው ትልልቅ የሚሳይልና የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃቶች ማግስት ነው። ሩሲያ ይህንን እርምጃ የወሰደችው ዩክሬን በሩሲያ ቁጥጥር ስር በምትገኘው ሉሃንስክ ግዛት ላይ ለሰነዘረችው ጥቃት የአጸፋ ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ገልጻለች።
Read 3048 times