ናሳ እ.ኤ.አ. በ2032 እና ከዚያ በኋላ "በጨረቃ ላይ መኖርና መስራትን" እውን ለማድረግ ያለውን እቅድ ይፋ አድርጓል። ይህ የጠፈር ተመራማሪዎች ተቋም በመቶዎች የሚቆጠሩ ስኩዌር ማይሎች ስፋት ያለው ቋሚ የጨረቃ ቤዝ ለመገንባት አቅዷል።
ተቋሙ ይህንን የጨረቃ ቤዝ "በጨረቃ ደቡባዊ ዋልታ ላይ ቀጣይነት ያለው የሰው ልጅ ቆይታን እንዲሁም የሰፉ ሳይንሳዊና የንግድ እንቅስቃሴዎችን ለማስቻል የተነደፈ ተነሳሽነት" ሲል ገልጾታል።
ዛሬ ይፋ በተደረገው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት፣ የሰው ልጆች ከ2032 ጀምሮ በቋሚነት ጨረቃ ላይ መኖር ይጀምራሉ።
The Mirror-

