Saturday, 30 May 2026 00:00

ፒኤስጂ የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ በላ!

Written by 
Rate this item
(0 votes)
የፈረንሳዩ ሀያል ክለብ ፒኤስጂ በታሪክ እጅግ አስገራሚ የሚባል ስኬት በማስመዝገብ፣ ለአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ውድድር የደረሰውን አርሰናልን በመለያ ምት በመርታት ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የሻምፒዮናው ባለቤት መሆኑን አረጋግጧል። በፑሽካሽ አሬና በተደረገው በዚህ እጅግ አስደናቂ የፍጻሜ ፍልሚያ፣ ካይ ሀቨርትዝ ለአርሰናል ቀዳሚዋን ግብ ቢያስቆጥርም ፒኤስጂዎች ተስፋ ሳይቆርጡ በመታገል በኦስማን ዴምቤሌ የ65ኛው ደቂቃ የፍጹም ቅጣት ምት ግብ አማካኝነት ወደ ጨዋታው ተመልሰዋል።
መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜና የ30 ደቂቃ ጭማሪ ሰዓት 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ አሸናፊውን ለመለየት ወደ መለያ ምት አምርቷል። ፒኤስጂዎች ባሳዩት የተረጋጋ ብቃትና ከፍተኛ ልምድ በመለያ ምት 4 ለ 3 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ዋንጫውን በድጋሚ ወደ ፓሪስ መውሰድ የቻሉ ሲሆን፣ በአውሮፓ እግር ኳስ መድረክ ላይ ያላቸውን ፍፁም የበላይነት በድጋሚ በተግባር አስመስክረዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Read 60 times