በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ወቅታዊ ቀውስ ምክንያት ከፍተኛ የጸጥታ ስጋት በነበረበት የሆርሙዝ ሰርጥ አካባቢ የነበረችው የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ንብረት የሆነችው “አሶሳ” መርከብ ሰርጡን በሰላም መሻገሯ ተሰምቷል።
መርከቧ ከሰርጡ በቅርብ ርቀት ላይ ወደምትገኘው ኮርፋካን ወደብ በመድረስ፣ ለሀገራችን እጅግ ወሳኝ የሆኑ የሕክምና እና የንግድ ጭነቶችን በተሳካ ሁኔታ በመጫን ጉዞዋን አጠናቃ በሰላም ወደ ሀገሯ ተመልሳለች።

