ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሌባ ወደ አንድ ሰው ግቢ ይገባና ምን የመሰለ ሠንጋ-ፈረስ ይሰርቃል፡፡ በዚያን ሰሞን ያን ሠንጋ-ፈረስ እያጠበ፣ የክት ልብሱን እየለበሰ አደባባይ ብቅ ሲል ዐይን ይገባል፡፡ ሰው ሁሉ እንዴት አማረበት ይለዋል፡፡ እሱም በኩራት ካባ ደርቦ ቼ-በለው ሲል ይታያል፡፡
አንድ ቀን አንድ የታወቀና የተከበረ ጠጅ ቤት ይመጣና ሠንጋ-ፈረሱን ደጅ አሥሮ እየጠጣ ሳለ ለካ ሌባ ደጅ ያቆመውን ሠንጋ-ፈረስ ሰርቆታል፡፡ ሲመጣ ሠንጋ-ፈረሱ የለም፡፡
ከዚያን ቀን ጀምሮ በእግሩ ሲሄድ ይታያል፡፡ ይሄን ያየ አንድ ወዳጁ፤
“አቶ እከሌ እንዴት ነህ?”
“ደህና” ይላል
“ሰሞኑን በሠንጋ-ፈረስ ሆነህ መጭ ስትል፤ አለፈለት፣ ሀብት በሀብት ሆነ ስንል ነበር፡፡ ሥራ እንዴት ነው?”
“እንደምታውቀው የእኛ ሥራ ውጣ-ውረድ ይበዛዋል እንጂ መልካም ነው”