Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 10 September 2011 14:01

..አዲሱ ዓመት የንባብ ዘመን ይሁን..

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ዓለምአቀፍ የአፍሪካ ደራስያን ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄዱና ሐፍቱ የሀገራችንን የተለያዩ ታሪካዊና ተፈጥሮአዊ ሥፍራዎች መጎብኘታቸው የዓመቱ የዘርፉ ትልቅ ስኬት ነው፡፡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ የአንጋፋ ሐፍትን ለምሳሌ የጋሽ ፀጋዬን እና የአብዬ መንግሥቱን ሥራዎች ማሳተሙ ሌላው ስኬት ነው፡፡ ለደራስያኑ ጉባኤ በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ዋና ሐፊነቴ፣ በአስተባባሪነት የራሴን አስተዋዖ አድርጌአለሁ፡፡ በወረቀት ዋጋ መናር በርካታ ሥራዎች አለመቅረባቸው የቀረቡትም በኑሮ ውድነት የተጠበቀውን ያህል ገዢ አለማግኘታቸው ዓመቱን አስቸጋሪ አድርገውታል፡፡ በግል ሕይወቴ ከማፈቅራት እሌኒ መስፍን ጋር ጋብቻ መፈፀሜ እጅጉን አስደስቶኛል፡፡ አምና በዚህ ወቅት አርቲስት ፀሐይ ዮሐንስ ያለውን ደግሜ ልዋስና 2004 ዓ.ም የንባብ ዘመን እንዲሆን እመኛለሁ፡፡
እንዳለጌታ ከበደ
ደራሲ

Read 4116 times