Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 03 November 2012 12:58

ንብ ባንክ 287 ሚ. ብር አተረፈ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ባለፈው ዓመት 286.2 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማስመዝገቡን ገለፀ፡፡ ባንኩ በላከው መግለጫ፤ የ2003/4 በጀት ዓመት ሪፖርት፣ ካለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ16.2 በመቶ ዕድገት ማሳየቱንና በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ሂሣብ 5.8 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ ጠቁሞ የሰጠው ብድርም 3.7 ቢሊዮን ብር ባንኩ ባለፈው ዓመት ስድስት ተጨማሪ ቅርንጫፎችን በመክፈት የቅርንጫፎቹን ቁጥር ወደ 56 ከፍ ማደረጉን የጠቆመው መግለጫው፤ በሁለት የውጪ ምንዛሬ ቢሮዎቹ ዘመናዊ የገንዘብ አከፋፈል ሥርዓቱን ለማሳደግ ከአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክና ከሕብረት ባንክ ጋር ፕሪሜየር ስዊች ሶሉሽን አ.ማ. የተባለ ኩባያ መክፈቱን አመልክቷል፡፡ለባንኩ ትርፋማነትና ተወዳዳሪ መሆን የዳሬክተሮች ቦርድ እንዲሁም፣ የአስተዳደሩና የድርጅቱ ሰራተኞች ትጋት ተጠቃሽ እንደሆነ ባንኩ ገልጿል፡፡

Read 3459 times