ሲድኒ ሼልደን “The Sands of Time” በሚል በእንግሊዝኛ የፃፈው መጽሐፍ በሙሉ ቀን ታሪኩ “ጦሰኛው ማፍያ” ተብሎ የተተረጎመ ሲሆን ሰሞኑን ለሽያጭ ቀርቧል፡፡ ፋር ኢስት ትሬዲንግ ያሳተመውን ልብ ሰቃይ ልቦለድ እያከፋፈለ ያለው ዩኒቲ መፃሕፍት መደብር ነው፡፡ መጽሐፉ ካሁን ቀደም “እጣ ፈለግ” ተብሎ መተርጎሙ ይታወሳል፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ በሰውነት ማጎልመሻ ጽንሰ ሀሳቦች ላይ ተንተርሶ የተዘጋጀው “በዘመናዊ አሰራር ሰውነትን መገንባት” መጽሐፍ ለንባብ የበቃ ሲሆን በ30.50 ብር እየተሸጠ ነው፡፡ ከመጽሐፉ ገፆች አብዛኞቹ በሥዕላዊ መግለጫዎች የተሸፈነውን መፅሐፍ ያዘጋጀው ኤፍሬም ታዬ ነው፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና