Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 03 September 2011 12:40

ሚዩዚክ ሜይዴይ የውይይት ቦታ ይቀይራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በየ15 ቀን አንድ ጊዜ የመፃሕፍት ንባብ ውይይት በማድረግ ላይ የሚገኘው ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ፣ የመፃሕፍት የመወያያ ቦታ ሊቀይር መሆኑን ገለፀ፡፡ የሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ የመፃሕፍት ንባብና ውይይት ክበብ ሃላፊ አቶ በፍቃዱ አባይ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፣ የእድምተኞች ቁጥር እየጨመረ በመሆኑ የተሻለ ስፋት ያለው መሠብሠቢያ አዳራሽ ያስፈለጋቸው ሲሆን ይህንኑ ተግባራዊ ለማድረግ አመቺ ሥፍራ እየፈለጉ መሆናቸውን እንዲሁም የተሳታፊ ቁጥር በ2004 ዓ.ም ይበልጥ ለማብዛት መዘጋታቸውን ገልፀዋል፡፡

የውይይት መድረኩን አስመልክቶ የመጠይቅ ጥናት አድርገናል ያሉት አቶ በፍቃዱ፤ የውይይት ቀን መቀየር እንደማስያፈልግ፣ ሆን ብለው ሰው ለማስደሰትና ለማስከፋት ወገንተኛ ሆነው የሚመጡትን ለመፃሕፍት ንባብ ውይይት ዓላማ ብቻ እንዲመጡ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በተሰጡ አስተያየቶች መሠረትም ካሁን በኋላ የሚደረጉ ውይይቶች መፃሕፍት ላይ ብቻ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
የሚዩዚክ ሜይ ዴይ ኢትዮጵያ የመፃሕፍት ንባብና የውይይት ክለብ በዘንድሮው ዓመት አስር የልቦለድ መፃሕፍት (አንዱ ትርጉም)፣ ሰባት ኢ-ልቦለድ፣ ሦስት ጥናታዊ ሑፎች እና ሁለት የግጥም መፃሕፍት በ22 ሳምንታት ለውይይት የቀረቡ ሲሆን ከውይይት መሪዎችም አለማየሁ ገላጋይ፣ አስቻለው ከበደ እና ብርሃኑ ከአንድ ጊዜ በላይ ውይይት እንደመሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

Read 4535 times Last modified on Saturday, 03 September 2011 12:43