Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 03 September 2011 12:58

ከ100 በላይ ዘፈኖች በቻይና እንዳይሰራጩ እገዳ ተጥሏል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የቻይና የባህል ሚኒስትር የባህል ደህንነትን አደጋ ላይ ይጥላሉ ያላቸውን ከ100 በላይ ዘፈኖች በአገሪቱ እንዳይሰራጩ እገዳ መጣሉን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡  
የቻይና መንግስት በሳንሱር ያልታዩና በይፋ ምዝገባ ያልተደረገላቸው ዘፈኖች በቀጥታ ከኢንተርኔት የሚገበዩበትን ሁኔታ በመቃወም እገዳውን የጣለ ሲሆን ማዕቀቡ ዘፈኖቹ ከያዙት ጭብጥ ጋር የተገናኘ አለመሆኑን ገልጿል፡፡ በቻይና የባህል ሚኒስትር ከታገዱ 100 ዘፈኖች መካከል ታይዋን፣ ሆንግ ኮንግና ጃፓን የተለቀቁት አብዛኛውን ድርሻ ቢወስዱም የቢዮንሴ፣ የካናዬ ዌስት፣ የሌዲ ጋጋ እና የኬቲ ፔሪ የሙዚቃ ሥራዎች በዝርዝሩ መካተታቸውን የሲኤንኤን ዘገባ አመልክቷል፡፡

የቻይና ባህል ሚኒስትር በህገወጥነት የፈረጃቸው ከ100 በላይ ሙዚቃዎች በቻይና እንዳይሰራጩ የሰጠው ቀነ ገደብ አንድ ሳምንት የቀረው ሲሆን የአርቲስቶቹ ዌብሳይቶች እንዲዘጉም ተወስኗል፡፡ በቻይና ሙዚቃ ኢንዱስትሪ በየዓመቱ ከ100 በላይ አልበሞች እንደሚሰራጩ ሲታወቅ ገበያው እስከ 179 ሚሊዮን ዶላር ይንቀሳቀስበታል፡፡

 

Read 4349 times Last modified on Saturday, 03 September 2011 13:02