Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 08 December 2012 14:27

“ኢትዮፒካሊንክ” ፕሮግራሙን ሰኞ በዛሚ ይጀምራል

Written by 
Rate this item
(8 votes)

በአክሱም ፒክቸርስ እየተዘጋጀ ላለፉት አምስት ዓመታት በፋና ኤፍ ኤም 98.1 ሲደመጥ የቆየው “ኢትዮፒካሊንክ”፣ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ በዛሚ ኤፍ ኤም ዝግጅቶቹን እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ ውስጥ አዋቂን ጨምሮ ሁሉም ዝግጅቶች እንደሚኖሩና ሌሎች ተጨማሪ ፕሮግራሞችም ሊቀርቡ እንደሚችሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ፕሮግራሙ ከሰኞ እስከ አርብ ከቀኑ 10 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት፤ እንዲሁም ቅዳሜ ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት ለተማሪዎችና ለሠራተኞች በሚመች ሰአት እንደሚተላለፍ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡ “ኢትየፒካሊንክ” በፋና ኤፍ ኤም 98.1 ያቀርብ የነበረውን ፕሮግራም ባለፈው ነሐሴ ወር ከጣቢያው ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ማቋረጡ ይታወሳል፡፡

Read 6665 times

Latest from