Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 22 December 2012 10:57

የብርሃኑ ተዘራ “ተበቺሳ” አልበም ሰኞ ለገበያ ይቀርባል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ላፎንቴን በሚል ስያሜ ከሙያ አጋሩ ከታደለ ሮባ ጋር አራት አልበሞችን ለአድማጭ ጆሮ ያደረሰው ድምፃዊ ብርሃኑ ተዘራ “ተበቺሳ” በሚል ርዕስ የሰራውን አዲስ የሙዚቃ አልበም የፊታችን ሰኞ ለገበያ እንደሚያቀርብ ታውቋል፡፡ አልበሙ 14 ዘፈኖችን የያዘ ሲሆን የሙዚቃ ቅንብሩን ካሙዙ ካሣ፣ ሔኖክ ነጋሽ፣ እዩኤል መሀሪ፣ ኤፍሬም ብርቅነህ፣ መኮንን ለማ እና መታፈርያ በቀለ እንደተሳተፉበት ተገልጿል፡፡ አልበሙን ያሳተመውና የሚያከፋፍለው ቮካል ሪከርድስ ነው፡፡ ድምፃዊው ከተለያዩ ነባርና ጀማሪ ድምፃውያን ጋር ነጠላ ዜማዎችን የሰራ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ “ኤሌያባ”፣ “ያምቡሌ” እና “አንበሳው አገሳ” የሚሉት ተጠቃሾች ናቸው፡፡

Read 4354 times Last modified on Saturday, 22 December 2012 11:16