ርዕሰ አንቀፅ

Rate this item
(15 votes)
ከዕለታት አንድ ቀን አንድ አዋቂና አንድ አላዋቂ በመንገድ ላይ እየተጓዙ ሳለ አንድ አውራዶሮ አጥር ላይ ሆኖ ሲጮህ ያያሉ፡፡ ይሄኔ አላዋቂው፤ “ይሄ አውራ ዶሮ እዚህ መሬት ላይ ሲጮህ‘ኮ እመንግስተ - ሰማይም ልክ ይሄንኑ የሚመስል አውራ ዶሮ በዚሁ ሰዓት ይጮሃል” ይላል፡፡ አዋቂው…
Rate this item
(10 votes)
ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ባላገር አንድ የማያውቀው ጫካ አቋርጦ ወደ መንገዱ ሊወጣ ሲጓዝ፤ አንድ የንጉሥ ልጅ በፈረስ ሆኖ ሲንሸራሸር ባላገሩን ያገኘዋል፡፡ ባላገሩ እጅ አልነሳም ልዑሉን፡፡ አልተሸቆጠቆጠም፡፡ ልዑሉ በጣም ገረመው፡፡ በአገሩ ደንብ ንጉሥን አክብሮ ለጥ ብሎ እጅ መንሳት ነበረበት፡፡ ባያውቅ ነው…
Rate this item
(15 votes)
ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት ቆቅ ሰባት ልጆቿን ይዛ ከቤት ወጥታ መንገድ ትጀምራለች፡፡ 1ኛዋ ጫጩት - እማዬ ወዴት ነው የምንሄደው?እናት - ቆቅ - ወደሩቅ አገር 2ኛዋ ጫጩት - እዚያ አገር ምን አለ?እናት ቆቅ - የተሻለ ኑሮ 3ኛዋ ጫጩት - የተሻለ ኑሮ…
Rate this item
(21 votes)
ከዕለታት አንድ ቀን አንዲት ለአቅመ -ሄዋን የደረሰች የደረሰች ሴት ልጅ የነበረቻቸው እናትና አባት በአንዲት መንደር ይኖሩ ነበር፡፡ ልጅቱ ከቀን ቀን እየወፈረች ሆዷ እየሞላ ትሄዳለች፡፡ የመንደሩ ሰው ሊጠይቃቸው ሲመጣ ጥያቄው አንድ ዓይነት ሆነ፡፡ አንዷ ትመጣና፤ “እንዴት ዋላችሁ?”“ደህና እግዚሃር ይመስገን”“ጤናዎትን እንዴት ከረሙ?”“አልፎ…
Rate this item
(12 votes)
ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ብዙ ጋሻ ቡና መሬት፣ ይጭኑት አጋሠሥ ይለጉሙት ፈረስ ያላቸው የበለፀጉ አባት ያሉት ልጅ አባቱን እንዲህ ይላቸዋል፡፡ “አባዬ”“ወይ”“እንግዲህ ለአቅመ - አዳም ደርሻለሁ፡፡ እንዴት አድርገህ ነው የምትድረኝ?” ሲል ይጠይቃል፡፡ አባቱም፤ “ለመሆኑ ኃላፊነት ለመቀበል ዝግጁ ነህ ወይ?”“አዎን፤ ዝግጁ ነኝ”“እንግዲህ…
Rate this item
(12 votes)
ከበደ ሚካኤል (አዝማሪና ውሃ ሙላት) አንዳንድ ዕውነተኛ ታሪክ ሲቆይ ተረት ይሆናል፡፡ የሚከተለው ተረት የዚያ ዓይነት ነው፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን፤ አንድ የአማርኛ መምህር ስለግጥም አስተማሩና “ቆቅ በሚለው ቃል አንድ ግጥም ፃፉ”አሉና የክፍል ሥራ ሰጡ፡፡ አንድ ሁልጊዜ የሆነ ያልሆነ ጥያቄ እየጠየቀ የሚያስቸግራቸው…