Administrator
የባርነትን ሰቆቃ የሚዘክሩት አስገራሚ ሀውልቶች!
21ኛው የዓለም ከ20 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጀምራል
21ኛው የዓለም ከ20 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው ዕለት በአሜሪካ ኦሪገን መካሄድ ይጀምራል፡፡
በሻምፒዮናው በ46 የውድድር ዘርፎች ከ147 ሀገራት የተወጣጡ 1 ሺህ 800 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ተመላክቷል፡፡
ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው በ5 ሺህ ሜትር፣ 3ሺህ ሜትር፣ 1 ሺህ 500 ሜትር እና በ800 ሜትር በሁለቱም ፆታዎች ትሳተፋለች፡፡
በተጨማሪም በ3 ሺህ ሜትር መሰናክል እና በ400 ሜትር በሴቶች እንዲሁም በርምጃ ውድድር ደግሞ በሁለቱም ፆታዎች የምትሳተፍ ይሆናል፡፡
ዛሬ በመክፈቻው ዕለት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የፍጻሜ እና የማጣሪያ ውድድራቸውን ያደርጋሉ።
ምሽት 4 ከ 43 ላይ በ800 ሜትር ወንዶች ማጣሪያ ነጋሄ እያሱ እና የሮሳን ግርማ ሲካፈሉ፤ በሴቶች ደግሞ በዚሁ ርቀት ምሽት 5 ከ 35 ሐብታም ገበየሁ እና ደራርቱ ሽብሩ ማጣሪያቸውን ያከናውናሉ።
ሌሊት 11 ከ 53 በሴቶች 5 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር እመቤት ጥላሁን እና አልማዝ ዮሃንስ የመጀመሪያውን ሜዳሊያ ለማሸነፍ ብርቱ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡
ማለዳ 12 ከ 20 በወንዶች 5 ሺህ ሜትር የፍጻሜ ውድድር ደግሞ ማማሩ ጎዴ እና ዳምጠው ከበደ የሚሳተፉ ይሆናል፡፡
ሻምፒዮናው በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 ቀን እስከ ነሀሴ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
ታላቋ ባለውለታ ወ/ሮ መዓዛ ቅጣው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
ግራጫ ቀለም የጥበብ ማዕከል መገለጫ አይሆንም
ኢትዮጵያዊው አርቲስት ያሬድ ንጉሱ በካናዳ ታሪካዊ የሥነ-ጥበብ ሥራ አስመረቀ
የ«እናርጅና እናውጋ» ደራሲ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ ሊያበቃ ነው
በ“እናርጅና እናውጋ” መጽሐፉ የሚታወቀውና በ2016 ዓ.ም በክብር አዋርድ “የዓመቱ ምርጥ የግጥም መጽሐፍ” አሸናፊ የነበረው ጌራወርቅ ጥላዬ፣ “የቃል ሊቀ መኳስ” የተሰኘ አዲስ መጽሐፉን ከሕትመት አውጥቷል። 128 ገጾች ያሉትና በ300 ብር የጀርባ ዋጋ በ1,000 ኮፒ ታትሞ የወጣው ይህ መጽሐፍ፣ ለአንባቢያን ይፋ የሚሆንበት ትክክለኛ ቀን ግን ገና አልተወሰነም።
ደራሲው ከመጽሐፍት በተጨማሪ በሙዚቃ ግጥም ድርሰት የሚታወቅ ሲሆን፣ ለአብነትም በአፍሪማ አዋርድ እጩ የነበረውንና በዩጋንዳ በተካሄደው አይኮኒክ አዋርድ “የዓመቱ ምርጥ ዘፈን” ተብሎ የተሸለመውን የሃሌሉያ ተ/ጻዲቅን “የልቤ ቁምነገር” የተሰኘ ተወዳጅ ዘፈን የደረሰው እሱ ነው። ጌራወርቅ ከዚህ ቀደም “ሙሉ አካል ትዝታ” በሚል ርዕስ ልቦለድ መጽሐፍ እንደሚያሳትም መናገሩም ይታወሳል።
ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት፡ የስልክ ሱስን የሰበረው ባለታክሲ
ወጣት ሰሎሞን አማረ (በማርኬቲንግ ማኔጅመንት የተመረቀ) አዲስ አበባ ውስጥ የሚያበራራትን ሜትር ታክሲ ወደ "ተንቀሳቃሽ ቤተ-መጽሐፍት" በመቀየር አዲስ ፈጠራን አስተዋውቋል።
-
ወጣቱ ከስልክና ማህበራዊ ሚዲያ ሱስ ተላቆ ወደ ንባብ ባህል እንዲመለስ ማስቻል፤ የትራፊክ መጨናነቅን ለንባብ አጋጣሚ መጠቀም።
-
ተሳፋሪዎች በጉዞ ወቅት መጽሐፍትን ያነባሉ፤ ከተመቻቸውም እዚያው ገዝተው ይሄዳሉ።
-
ከትራንስፖርት አገልግሎት ጎን ለጎን መጽሐፍትን በመሸጥ ድርብ ገቢ ያገኛል፤ በቲክቶክ (Sol Books) ገጹም መጽሐፍትን ያሰተዋውቃል።
-
ሌሎች የትራንስፖርት አቅራቢዎችም ይህን አርአያነት ያለው ተግባር በመከተል ታክሲዎችን የዕውቀት ማዕከል እንዲያደርጉ ጥሪ ያቀርባል።
"ስለ ዕቅዱ የሰማሁት ከመገናኛ ብዙኃን ነው" - አርሴን ቬንገር
የቀድሞው የአርሰናል አሰልጣኝ እና የአሁኑ የፊፋ የዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ልማት ኃላፊ አርሴን ቬንገር፣ በፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ቀርቦ ሳይሳካ በቀረው የ'ፊፋ ፉትቦል ኢንተርቴይመንት' (FFE) ስትራቴጂክ ዕቅድ ውስጥ ምንም ዓይነት ተሳትፎ እንዳልነበራቸው አስታወቁ። ቬንገር ስለ ዕቅዱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰሙት ከመገናኛ ብዙኃን እንደነበር ገልጸው፣ አከራካሪው ዕቅድ እንዲሰረዝ የተደረገው ውሳኔም እጅግ አስፈላጊ እና ትክክለኛ እርምጃ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በፊፋ ውስጥ ያላቸው በኃላፊነት የሚያከናውኑት ሥራ በጨዋታ መረጃዎች ትንተና፣ በዓለም ዙሪያ በሚገኙ 60 አካዳሚዎች እና በወጣቶች ስልጠና ላይ ብቻ ያተኮረ መሆኑን የገለጹት ቬንገር፣ በተጨማሪም ለIFAB በቴክኒክ አማካሪነት እያገለገሉ ይገኛሉ። አክለውም ፊፋ በገለልተኝነት፣ በግልጽነት እና በታማኝነት ማገልገል እንዳለበት በመግለጽ፣ የእሳቸው ትኩረት አሁንም እግር ኳስን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማሳደግ በሚደረገው ሙያዊ ጉዞ ላይ ብቻ መሆኑን አብራርተዋል።

