Administrator
Wednesday, 29 October 2025 15:42
በ2ዐዐ ቢ. ብር ወጪ 14 መካከለኛና ከፍተኛ ግድቦች እየተሰሩ ነው
በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለሜጋ ኘሮጀክቶች በተሰጠው ትኩረት ከታላቁ ህዳሴ ግድብ በተጨማሪ 14 መካከለኛና ከፍተኛ ግድቦች በ2ዐዐ ቢሊዮን ብር ወጪ እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል፡፡
ጠ/ ሚኒስትሩ ትላንት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሰጡት ማብራሪያ፤ በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች በ1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ወጪ 346 የመንገድ ኘሮጀክቶች በፌደራል መንግስት ግንባታቸው እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የኤሌክትሪክ ኃይል በኢትዮጵያ ሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ በተሰራው ሥራም 11ዐ ቢሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት የመብራት ማስፋፊያ ኘሮጀክት ሥራ መጀመሩን ጠቁመዋል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:37
በመዲናዋ በሦስት ወራት ብቻ ከ3 ሺ በላይ ፍቺ ተፈጽሟል
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ እንዳስታወቀው፤ በመዲናዋ በሩብ ዓመቱ 3 ሺ 32 ፍቺ ተመዝግቧል፡፡
ኤጀንሲው ይህን ያህል ፍቺ የተመዘገበው በተጠቀሰው ጊዜ ጋብቻ ከፈጸሙ 10 ሺ 696 ጥንዶች መካከል መሆኑን ገልጿል።
በመዲናዋ በሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ የተመዘገበው ከፍተኛ መጠን ያለው ፍቺ እጅግ አሳሳቢ ነው ተብሏል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ህብረተሰብ
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:30
የድምፃዊ ሐይሉ አመርጋ አልበም ተመረቀ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:18
ኢትስዊች የመረጃ ማዕከሉን ከብሔራዊ ባንክ ወደ ዘመን ባንክ አዘዋወረ
ኢትስዊች የመረጃ ማዕከሉን ከብሔራዊ ባንክ ወደ ዘመን ባንክ ዋና መስሪያ ቤት ማዘዋወሩን ገልጿል። ትናንት በአዲስ አበባ፣ ሸራተን አዲስ 12ኛ የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ አካሂዷል።
በጉባዔው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ደስታ፣ የ1 ሺሕ ብር አክሲዮን የትርፍ ድርሻ ወደ ብር 486 ማደጉን ገልጸዋል። አክለውም፣ በተቋሙ አማካይነት ከ740 ቢሊየን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር መደረጉን ጠቁመው፣ ይህ የገንዘብ ዝውውር ከ287 ሚሊዮን በላይ በሆነ ግብይት የተፈጸመ መሆኑን አስረድተዋል።
ከዚህ የገንዘብ ዝውውር ውስጥ ከ577 ቢሊዮን ብር በላይ የሚሆነው ከአንድ የፋይናንስ ተቋም ወደ ሌላኛው በተደረገ የገንዘብ ማስተላለፍ የተዘዋወረ መሆኑን ያመለከቱት አቶ ሰለሞን፣ ይህ ከአጠቃላይ የግብይት መጠን 128 ነጥብ 3 ሚሊዮን ያህሉን እንደሚሸፍን ተናግረዋል።
አቶ ሰለሞን "የኩባንያው አጠቃላይ የተከፈለ ካፒታል ከ 2 ቢሊየን 500 ሚሊዮን ተሻግሯል" ያሉ ሲሆን፣ የኩባንያው ዓመታዊ ገቢ 2.2 ቢሊየን ብር መድረሱንም አስታውቀዋል። እንዲሁም ኩባንያው ከታክስ በፊት ያገኘው ትርፍ 1 ነጥብ 42 ቢሊየን ብር መሆኑን አመልክተዋል።
ኢትስዊች ካከናወናቸው ዓበይት ክንውኖች መካከል፣ በብሔራዊ ባንክ ስር የነበረውን የመረጃ ማዕከል ወደ ዘመን ባንክ ዋና መስሪያ ቤት እንዲዘዋወር ማድረጉ ተጠቃሽ መሆኑን አቶ ሰለሞን ገልጸዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ ተቋሙ በዋና መስሪያ ቤትነት የሚያገለግለውን ባለ12 ፎቅ ሕንጻ ለመግዛት መቻሉንም ጨምረው አስታውቀዋል።
በሁሉም የግል እና የመንግስት ባንኮች እንዲሁም በብሔራዊ ባንክ ባለቤትነት የሚተዳደረው ኢትስዊች አክሲዮን ማሕበር፤ በፋይናንስ ተቋማት፣ በአገር ውስጥ የክፍያ ስርዓት እና በብሔራዊ የክፍያ ስርዓት መካከል የእርስ በርስ የገንዘብ ዝውውር ስርዓት እንዲኖር ለማድረግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:08
ሉሲና ሰላም ከ2 ወር በኋላ ወደ አገራቸው ተመለሱ
በቼክ ሪፐብሊክ ለእይታ ቀርበው የነበሩት ሉሲና ሰላም ከሁለት ወር ቆይታ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመለሱ፡፡
ሁለቱ ቅሪተ አካላት በፕራግ ሙዚየም የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው፣ ዛሬ ንጋት ላይ አዲስ አበባ መግባታቸውን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ሁለቱ ቅርሶች ከነሐሴ 10 ቀን 2017 እስከ ጥቅምት 13 ቀን 2018 በነበራቸው ቆይታ ከመላው አውሮፓ በጎረፉ ቱሪስቶች እንደተጎበኙና የኢትየጵያን የሰው ዘር መገኛነት በዓለም አደባባይ ማስተዋወቃቸውን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:07
ጋና ትምህርት በእንግሊዝኛ እንዳይሰጥ ከለከለች
የጋና መንግሥት ከመዋዕለ ሕፃናት እስከ አንደኛ ደረጃ ድረስ በአገር ውስጥ ቋንቋዎች ማስተማርን አስገዳጅ ማድረጉ የተዘገበ ሲሆን፤ እስከዛሬ የማስተማሪያ ቋንቋ ሆኖ የቆየው እንግሊዝኛ ቀርቷል ነው የተባለው፡፡
እርምጃው ባህላዊ ማንነትን ለማጠናከርና በወጣት ተማሪዎች መካከል የትምህርት ውጤቶችን ለማሻሻል ያለመ እንደሆነ ተነግሯል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ከአለም ዙሪያ
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:05
ዩኒቨርሲቲው የተማሪዎቹን ጸጉር ማስቆረጥ ጀምሯል!
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎቹን ጸጉር ማስቆረጥ ጀምሯል አሉ፡፡ እኔ መጀመሪያ ስሰማ የምር አልመሰለኝም ነበር፡፡ አሁን እንደሚታየው ግን ጭራሽ ህግ የወጣለትም ጉዳይ ነው፡፡
"ዩኒቨርሲቲ" ተብለው እንዲህ አይነት ሀሳብ ከየት እንደመጣላቸው ራሱ አላውቅም፡፡ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ማስተካከል የሚገባው በጣም ብዙ ጉዳይ እያለ ከዚህ ለምን መጀመር እንደፈለገም አልገባኝም፡፡ ዞሮ ዞሮ እንዲህ አይነት ሀሳብ መነሻው ህዝበኝነት (populism) ነው ብዬ እገምታለሁ፡፡
ተራ ጭብጨባ የመቃረም አባዜ ያመጣው ሀሳብ እንደሆነ እጠረጥራለሁ፡፡ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ "ከፍተኛ የትምህርት ተቋም" ነው፡፡ ስለዚህም ማተኮር ያለበት ስለ ጸጉር ርዝማኔ ሳይሆን ከጸጉር በታች ያለው ጭንቅላት ስለሚያፈልቀው ሀሳብ ብቻ ነው፡፡ዩኒቨርሲቲው በአብዛኛው በሀያዎቹ ውስጥ ያሉ ወጣቶችን እንደማስተማሩ አንዳንድ ነገሮችን ለእድሜና ለተፈጥሮ መተው አለበት፡፡ ጸጉራችንን ተቆርጠን ስንመጣ "ጨዋ" የሚል ሙገሳ ሊሰጡን የሚገባው ወላጆቻችን እንጂ ዩኒቨርሲቲው አይደለም፡፡
ህዝበኝነት ይጥፋ!
(Ab Bella-)
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:04
"ለትግራይ የሚመደበው በጀት ለልማት ሳይሆን ለታጣቂ እየዋለ ነው"
“ለትግራይ ክልል ውስጥ ተጨማሪ ውጊያ አንፈልግም፤ ከዚያ ይልቅ ተባበረን ሀገር ማልማት ነው የምንፈልገው። ከዚያ ውጭ መንግሥትን በሃይል ለመጣል ፍላጎት ካለ እሱ ፈጽሞ ሊሳካ አይችልም። የፌደራል መንግስት ለትግራይ ክልል የሚመድበው በጀት ለልማት ሳይሆን ለታጣቂ እየዋለ ነው፤ ይህም ትክክል አይደለም። ትግራይ ልማት ያስፈልጋታል። በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በትብበር ለልማት መስራት ይገባል።”
ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:03
ማክሮን በወታደራዊ አዛዥነት ለመታወስ ተስፋ አድርገዋል - ሩሲያ
የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት 'ማክሮን በዩክሬን ወታደራዊ ጣልቃ ገብነትን እያለሙ ነው ያለው የሩሲያ የውጭ ደህንነት አገልግሎት፤ አሁንም በታሪክ መዝገብ በወታደራዊ አዛዥነት ለመስፍር ተስፋ አድርገዋል ብሏል፡፡
በፕሬዚዳንቱ መመሪያ መሠረት የፈረንሳይ የጦር ኃይሎች ጄኔራል ኢታማዦር ሹም፣ የኪዬቭ አገዛዝን ለመደገፍ እስከ 2 ሺህ የሚደርሱ ወታደሮችንና መኮንኖችን ወደ ዩክሬን ለማሠማራት እየተዘጋጁ መሆኑን አገልግሎቱ ማስታወቁን ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡
የዚህ ኃይል ዋና አካል በዋናነት ከላቲን አሜሪካ ሀገራት የተመለመሉ የፈረንሳይ የውጭ ወታደሮችን ያቀፈ እንደሆነ ተጠቁሟል።
“እነዚህ ምልምል ወታደሮች በዩክሬን ድንበር አቅራቢያ በሚገኙ የፖላንድ አካባቢዎች ተሠማርተው ከፍተኛ የውጊያ ቅንጅት ሥልጠና እየወሰዱ ነው።” ብሏል፤የውጭ ደህንነት አገልግሎቱ፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
Published in
ዜና
Tagged under
Wednesday, 29 October 2025 15:01
ኢሎን መስክ አዲስ የበይነ መረብ ኢንሳይክሎፒዲያ ይፋ አደረገ
ቢሊየነሩ ኤሎን መስክ፣ ግሮኪፒዲያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የሚሰራ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ ለዊኪፒዲያ አማራጭ እንደሚሆን ገልጿል።
መስክ ባለፈው ወር ዊኪፒዲያ ለፅሁፎቹ እነ ኒውዮርክ ታይምስን በምንጭነት እንደሚጠቀም አንስቶ የሚሰጠው መረጃ የተዛባ ነው በማለት አዲስ ኢንሳይክሎፒዲያ እንደሚያወጣ አስታውቆ ነበር።
ግሮኪፒዲያ ላይ እንደ ዊኪፒዲያ ሰዎች መፃፍና ማስተካከል የማይችሉ ሲሆን፤ ፅሁፎቹ ግሮክ በተሰኘው የራሱ የሰው ሰራሽ አስተውሎት የሃቅ ማጣራት ይደረግባቸዋል ተብሏል። ሰዎች ምንም እንኳን ፅሁፎቹ ላይ ማስተካከያ ማድረግ ባይችሉም የተሳሳተ ነው ብለው የሚያምኑት መረጃ ካለ እንዲስተካከል ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።
ዊኪፒዲያን የሚያስተዳድረው ዊኪሚዲያ ፋውንዴሽን፣ ግሮኪፒዲያ እንዴት እንደሚሰራ ለመረዳት እየጣረ መሆኑን ገልፆ፣ የዊኪፒዲያ እውቀት ሁሌም የሰው ነው፤ ግሮኪፒዲያ ራሱ ለመኖር ዊኪፒዲያ ያስፈልጋል"ብሏል።
ዊኪፒዲያ በአሁኑ ወቅት በእንግሊዝኛ የተፃፉ ከ7.1 ሚሊየን በላይ ፅሁፎች ሲኖሩት፣ ግሮኪፒዲያ አሁን ላይ ከ885 ሺህ በላይ ፅሁፎች አሉት።
ኤሎን መስክ በተጨማሪ በዚህ አመት መጨረሻ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መተግበሪያው ግሮክ፣ ዊኪፒዲያን በምንጭነት እንዳይጠቀም እንደሚደረግ ገልጿል ሲል ቲክቫህ መጋዚን አስነብቧል፡፡
Published in
ዜና
Tagged under

