Administrator

Administrator

Friday, 31 October 2025 08:12

የመጻሕፍት ምርቃት!

በዝግጅቱ ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች፣የጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም የሚድያ አካላት በቦታው በመገኘት ዝግጅቱን በመዘገብ ለሕዝቡ እንድታደርሱ ከወዲሁ በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡

* ከ5 ሺሕ በላይ ሰዎች ይገበኙታል ተብሎ ይጠበቃል
ከ14 አገራት የተውጣጡ ከ100 በላይ ዓለም አቀፍ የእንስሳት ሃብት ዘርፍ ተዋናዮች የሚሳተፉበት የንግድ ትርዒት ዛሬ በአዲስ አበባ፣ ሚሊኒየም አዳራሽ መካሄድ ጀምሯል። በዚህ የንግድ ትርዒት ላይ ከ5000 በላይ የኢትዮጵያ፣ የምስራቅ አፍሪካና ዓለም አቀፍ አገራት ጎብኚዎች እንደሚጠበቁ ተነግሯል።
በዚሁ የንግድ ትርዒት ስር፣ 14ኛው የኢትዮ ፖልተሪ ኤክስፖ (ኢትዮቼከስ)፤ 10ኛው የአፍሪካ እንሰሳት ዓውደ ርዕይና ጉባዔ (አሌክ) እንዲሁም 5ኛው የአፒካልቸር እና አኳካልቸር ኢትዮጵያ ዓለማቀፍ የንግድ ትርዒትና ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ የሚካሄደው የባዮ ኢነርጂ የንግድ ትርዒት በአንድነት የሚከናወኑ ሲሆን፣ በንግድ ትርዒቱ ላይ ጥራት ያላቸው የዘርፉ ዋነኛ አንቀሳቃሾች እንደሚሳተፉበት ተገልጿል።
የፕራና ኢቨንትስ የፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ሜሮን ስሎሞን እንደተናገሩት፣ ባለፉት ዓመታት የተካሄዱት ዓውደ ርዕይና ጉባዔዎች ለዶሮ፣ ዕንቁላል፣ ወተትና ስጋ ንዑስ ዘርፎች ዕድገትና ልማት ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል። አክለውም፣ "እነዚህ ሁነቶች ለዘርፉ ባለሞያዎችና ለንግዱ ማሕበረሰብ ትልቁ መሰባሰቢያ በመሆናቸው የገበያ ትስስር በመፍጠር፣ አዳዲስ ቴከኖሎጂዎችን በማስተዋወቅ፣ የዕውቀት ሽግግርን በማምጣት እንዲሁም የኢንቨስትመንት ዕድሎችን በማስተዋወቅ ለዘርፉ ልማት ያላቸውን ከፍተኛ አስተዋጽዖ ማረጋገጥ ችለዋል" ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ፕራና ኤቨንትስና መቀመጫውን ሱዳን ባደረገው አጋሩ ኤክስፖ ቲም ትብብር የሚዘጋጀው ሁሉን-አቀፍ የእንስሳት እርባታ ቴከኖሎጂ፣ ግብዓት እና መፍትሔዎች ላይ ትኩረት የሚያደርገው ዓለም አቀፉ የንግድ ትርዒት፣ የእንስሳት ሃብት የገበያ ስንሰለቶች ላይ ያሉ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን የገበያ ትስስር ለመፍጠር እንዲሁም የዕውቀትና የቴከኖሎጂ ሽግግር ለማምጣት ኔዘርላንድን ጨምሮ ከ14 አገራት የተውጣጡ ከ100 በላይ የዘርፉ ድርጅቶች እንደሚሳተፉ ለማወቅ ተችሏል።
በኢትዮጵያ ባሕላዊ የዶሮ እርባታ እስካሁን በስፋት የሚዘወተር ልምድ መሆኑን በመድረኩ ላይ ሲጠቆም፣ ዘመናዊ የዶሮ እርባታን በማስፋፋት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አስፈላጊውን አስተዋፅኦ ለማድረግ የሚዘጋጅ ብቸኛው የዘርፉ ዓለም አቀፍ ሁነት የኢትዮ ዶሮ ኤክስፖ መሆኑም ተጠቅሷል። እንዲሁም የአፍሪካ የእንስሳት ሃብት ዓውደርዕይና ጉባዔ ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የእንስሳት ሃብት ባለቤት መሆኗ ባያጠራጥርም፣ በዘርፉ ያላት ምርታማነትና የነፍስ ወከፍ ፍጆታ ከዓለም ዝቅተኛ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የወተት እና የስጋ ዘርፉን በዘመናዊ መልክ ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራበት "መድረክ ነው" ተብሏል።
የንግድ ትርዒቱ ከጥቅምት 20 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል።
 
 
 
የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ አቶ የማነ ገ/መስቀል፣ የኢትዮጵያው ገዥ ብልጽግና ፓርቲ በባሕር በር ጉዳይ ላይ የሚከተለው "አምታች የኾነ አካሄድ" በቀጠናው ጦርነት ሊቀሰቅስ ይችላል በማለት ከሰሞኑ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አስጠንቅቀዋል።
የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹምና ሌሎች የአገሪቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች በኤርትራ ላይ "የጦርነት ዛቻ" ማሰማት ቀጥለዋል በማለት የከሠሡት ቃል አቀባዩ፤ በሌላ በኩል ደሞ ብልጽግና ኢትዮጵያን ከምጽዋ፣ አሰብና ከጅቡቲዋ ታጁራ ወደብ ጋር የሚያገናኝ የባቡር ሐዲድ ለመገንባት እንዳቀደ በመግለጽ፣ "አምታች አካሄድ" ይከተላል በማለት ተችተዋል።
ቃል አቀባዩ በዚህ ሳምንት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ በወደብ ጉዳይ ከተናገሩ በኋላ ቃል አቀባዩ በሰጡት ምላሽ፤ ብልጽግና ፓርቲ በአሰብ ወደብ ዙሪያ የሚያሠማው "ቅዠት" እየተባባሰ ሄዷል ብለዋል፡፡
አቶ የማነ፣ ማክሰኞ'ለት በኢትዮጵያ ፓርላማ ውስጥ የተሠማው ትርክት፣ "ከተቻለ በድርድር፤ ካልተቻለ በወታደራዊ ወረራ የአሰብ ወደብ ባለቤት እንኾናለን" የሚል ይዘት አለው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ የቅኝ ግዛት ትርክት ሲቃኝ የኖረው ማራኪ በሚመስሉ አመክንዮዎች ወይም ሕዝቦችን የማሠልጠን ተልዕኮ በሚል ምክንያት ነበር ያሉት ቃል አቀባዩ፤ "ሞኛሞኝ የሆነው የብልጽግና ትርክት ግን በዘመናዊ ታሪክ ተሠምቶ አያውቅም" ብለዋል።
(ዋዜማ)
የትግራይ የዘር ማጥፋት ኮሚሽን፣ የትግራዩ ጦርነት ያስከተለው ማኅበራዊ ውድመትና ኪሳራ 10 ነጥብ 8 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት በጥናት ማረጋገጡን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ጦርነቱ ከፍተኛውን ውድመት ያደረሰው በትምህርት ዘርፉ ላይ መኾኑን ይጠቅሳል።
ሪፖርቱ፣ የኤርትራ ሠራዊት በትምህርት፣ በጤና ሥርዓቶች፣ በቅርሶች፣ በታሪካዊ ሕንጻዎች፣ በእደ ጥበባትና በታሪካዊ ቁሳቁሶች ላይ ከ38 እስከ 56 በመቶ የሚደርስ ጉዳት አድርሷል ብሏል።
ባንጻሩ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ በቁጠባና ብድር ተቋማት፣ በኅብረት ሥራ ማኅበራት፣ በአነስተኛ ማኅበራዊ አገልግሎት ሠጪ ተቋማት ላይ የ27 ነጥብ 2 በመቶ ጉዳት ማድረሱን ኮሚሽኑ ገልጧል።
[ዋዜማ]
የዝነኛው አቀንቃኝ ዘ ዊክንድ (አቤል ተስፋዬ)፣ የተጣራ የሀብት መጠን በአራት ዓመታት ውስጥ በሦስት እጥፍ አድጎ 600 ሚሊዮን ዶላር መድረሱ ተዘገበ፡፡
ሰለብሪቲ ኔት ዎርዝ ድረ-ገጽ እንደገለጸው፤ የዚህ ዓለማቀፍ ድምጻዊ አጠቃላይ ሀብት እ.ኤ.አ. በ2021 ከነበረበት 200 ሚሊዮን ዶላር በአራት ዓመታት ወደ 600 ሚሊዮን ዶላር አሻቅቧል - የ400 ሚሊዮን ዶላር ጭማሪ በማሳየት፡፡
የድምጻዊው "Blinding Lights"ን የመሳሰሉ ተወዳጅ ሥራዎቹ በበይነመረብ የሙዚቃ ማሰራጫ መድረኮች በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ጊዜያት መደመጣቸው ለገቢው መጨመር የጎላ አስተዋጽኦ ማድረጋቸው የተነገረ ሲሆን፤ እ.ኤ.አ. በ2024 ከስፖቲፋይ ብቻ ከ50 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱ ተጠቁሟል፡፡
በተጨማሪም ዝነኛው አቀንቃኝ ከአዳዲስ፣ ፑማና ሌሎች ታላላቅ ኩባንያዎች ጋር ባለው የሥራ ውል ከፍተኛ ገቢ እንደሚያገኝ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
ዘ ዊክንድ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ በስፋት እንደሚሳተፍም ይታወቃል፡፡
በኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለሜጋ ኘሮጀክቶች በተሰጠው ትኩረት ከታላቁ ህዳሴ ግድብ በተጨማሪ 14 መካከለኛና ከፍተኛ ግድቦች በ2ዐዐ ቢሊዮን ብር ወጪ እየተሰሩ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል፡፡
ጠ/ ሚኒስትሩ ትላንት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሰጡት ማብራሪያ፤ በሀገሪቱ ሁሉም አካባቢዎች በ1 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር ወጪ 346 የመንገድ ኘሮጀክቶች በፌደራል መንግስት ግንባታቸው እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የኤሌክትሪክ ኃይል በኢትዮጵያ ሁሉም አካባቢ ተደራሽ ለማድረግ በተሰራው ሥራም 11ዐ ቢሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት የመብራት ማስፋፊያ ኘሮጀክት ሥራ መጀመሩን ጠቁመዋል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ እንዳስታወቀው፤ በመዲናዋ በሩብ ዓመቱ 3 ሺ 32 ፍቺ ተመዝግቧል፡፡
ኤጀንሲው ይህን ያህል ፍቺ የተመዘገበው በተጠቀሰው ጊዜ ጋብቻ ከፈጸሙ 10 ሺ 696 ጥንዶች መካከል መሆኑን ገልጿል።
በመዲናዋ በሦስት ወራት ጊዜ ውስጥ የተመዘገበው ከፍተኛ መጠን ያለው ፍቺ እጅግ አሳሳቢ ነው ተብሏል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

አልበሙ ከጥቅምት 21 ጀምሮ በሀይሉ አመርጋ የዩቲዩብ ቻናል 

Page 2 of 790