Administrator

Administrator

Saturday, 25 October 2014 10:28

የህፃናት ጥግ

ሞቶ ገዳይ
እግሬን ዛሬ ወስዶ - እጄን እያስቀረ
እያማ ሊበላኝ - ማሰቡ ካልቀረ
የግፍ ጥርሱ ገጦ----
በኔ ጣር አጊጦ-----
ይኖራል እንዳይል የአዳኜ ሹል ስልጣን
አፈንድቼ እምጥል - ስለምሆን ቁንጣን
ቀስ በቀስ ስሞት እንዳይበዛ ነውሬ…፣
            ባንዴ እሚሰለቅጥ - እዘዝልኝ አውሬ፡፡
     ድኖ መግደል!
አምና የዛሬ አመት  - እሁድ አጠባብ ላይ
ሳይፈልጠው ሳይቆርጠው - ታዝዞበት ከላይ
በእለተ ፋሲካ - በሚዳንበት ቀን
ልጅ ሞቶብን ድንገት . . . ከአፈር ጋር አስታርቀን
ቀብረነው ስንመጣ . . . ቢሆነን ሰቀቀን
ይህን ብላቴና . . . ገና እሱ ተፈርቶ
እንዴት ይወስደዋል - ያለ ቀኑ ጠርቶ
አየ የሱ ነገር - አይገርመው እይጨንቀው
የእናትና ልጅን ነገር እያወቀው
ከቀንም ቀን መርጦ ያውም በፋሲካ
ይኸ የማርያም ልጅ . . .
እንዲያው ባል አያውቅም - ስራ አይፈታም ለካ
እያልን እያማን ሳል . . .  ፈጣሪን በትዝብት
መፅናናት ልንፈጥር ለሟቹ እናት አባት
ድንገት የልጁ አባት - ስሜቱ ገንፍሎ
በሚያባባ ዜማ - ጉሮሮውን ስሎ
ፈጣሪን ወቀሰው - አማው እንዲህ ብሎ
“እንደዚህ ያለ ፍርድ - የተገመደለ
በትንሳኤው ምድር - ስንት ቀን እያለ
ኧረ የጉድ አገር - እግዜር ተሳስቶ
ልጄን ገደለብኝ - የራሱን ተነስቶ”፡፡
(ለእየየ)

ስርዝ ድልዝ
ደም የሚፈሰው ልብ በሹል ጦር ተወግቶ
ከጎን ፅጌሬዳ . . .
እምቡጡ ፈንድቶ በቀይ እስክሪቢቶ …
ከሳለችበት ሉክ ከጥቅሱ ቀጥሎ
የላከችልኝን የፍቅር ደብዳቤ …
ሊያነብ እጄ ሲገልጥ እጥፋቱን ነጥሎ
ቁልጭ ካለው ፅሁፍ ከተደረደረው
ልቤ የጓጓለት ሊያነበው ያማረው
መቼ ዝርዝሩን ሆነ የፍቅሯን ሀተታ
ድልዙን ቃል እንጂ . . .
ያስቀረችብኝን ሰርዛ አመንትታ፡፡

(በቅርቡ ለንባብ ከሚበቃው “ቁመታም ጾም” የተሰኘው የአያሌው እውነቴ የግጥም መድብል)

ከእለታት አንድ ቀን አንድ ሚስቱ ላይ የሚኮራ የሚኩራራ ጉረኛ ባል ነበረ፡፡ አንድ ማታ ሲመጣ ክፉኛ ተፈንክቷል፡፡
“ምነው ውዴ! ምን ነካህ?” አለችው ሚስቱ፡፡
“ዛሬ ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?” አለና ጀመረ፡፡
“ምን ሆነ የእኔ ጌታ?”
“አንዱ አጉል ልታይ ልታይ ባይ ጉራውን ሲነዛ አግኝቼው ‹እረፍ!› አልኩት”
“ማ? ማነው እሚያርፈው?” አለኝ፡፡
“አንተ ነሃ! ካንተ ሌላ ጉራ እሚነዛ አለ እንዴ?”
“አፍህ ካላረፈ እኔ ራሴ አሳርፍሃለሁ! አይለኝም?!”
‹በቃ ወጣ ብለን መተያየት ነዋ!› አልኩትና ቀድሜ ወጣሁ ከቡና ቤቱ፡፡”
ሚስትየውም “ከዛስ?” አለችው፡፡
ባል “እሱም ተከትሎኝ ወጣ!”
ሚስት “ከዛስ?”
ባል “ቀድሜ ቡጢ አቀመስኩት”
ሚስት “ከዛስ? ወደቀ?”
“አይ አልወደቀም”
“ታዲያ ምን ሆነ እሺ?”
“ተቀማመስን”
“ከዚያስ?”
“ከዚያማ እንደምታይኝ ተፈነከትኩ”
“ይሄማ ቡጢ አይደለም!... ዱላ ይዞ ነበር?”
“አይ አንቺ! ወንድ መስሎሻል? ዱላ ይዞ የሚዞር፣ የእኔኑ ነጥቆ ነው እንጂ!?”
*  *    *
የሀገራችን ታሪክ ይሄው ነው! ዱላ ያልያዘው መቺ ነው! ምነው ቢሉ፤ ባለ ዱላው ያቀብለዋልና! ተከራካሪው የሚያቀርበውን ሙግት ተፃራሪው ወስዶ ይሟገትበታል፡፡ “ከሞኝ ደጅ ሞፈር ይቆረጣልም” ነው፡፡ ያም ሆኖ የማታ ማታ ዱላ አቀብሎ ለመፈንከት አጉል መፎከር የቂል ቆንሲል መሆን ነው፡፡ ውስጠ - ሚስጥሩ ጥልቅ ነው፡፡ እነ ሆቺ ሚን በየዋሁ ዘመን “የመሣሪያ ምንጫችን ጠላታችን እራሱ ነው ይሉ ነበር!” ዛሬ ያ የሞኝነት መንገድ ይመስላል!
ችግር እያለብን ችግር የለብንም አንበል፡፡ “መንግስት ማለት የአገሩ አዕምሮ እንጂ የልቡ ሮሮ ብቻ አይደለም” ይላል የአገራችን ዋና ገጣሚ፡፡ ይህን አንርሳ!
“የአብራሄ - ህሊና፣ ዘመን  ፈላስፎች እነስፒኖዛ፣
ሎክ፣ ካንት፣ ሚል፣ ቮልቴር እና ዘመናዊዎቹ እነ ራሰልና ፐፐር … ሁሉም፡፡ ህይወት ማለት ችግር መፍታት ነው፤ ይላሉ፡፡ ምንም ፍፁም ነገር የለም! እድገት ሊመጣ የሚችለው ጥብቅና ኮስታራ እሳቤ ካለ ነው፡፡ ይህ እንግዲህ ከጭንቀት ነፃ የሆነ ነፃነትና ለታላቅነት ዕውቅና የመስጠት ብቃት ሲኖር ነው፡፡ ግን ድክመትን ለማሳየት አለመፍራት! ካለ ነው!” ይላሉ፡፡ የተባለውን ማጣራት የእኛ ፈንታ ነው፡፡ ህይወት ማለት ችግር መፍታት ነውና፡፡ ይህን ያላስተዋለ በችግር ላይ ችግር ቢፈጥር ውጤቱን እሱና እሱ ብቻ ነው የሚያገኘው!!
ከትዕዛዝ አክባሪነት ይልቅ ምክን ሊመራን ይገባል (ስፒኖዛ)፡፡  ትዕዛዝ አለማክበር በፍፁም ግብረገብነት አኳያ ሲታይ እንደጥፋት ይቆጠር ይሆናል፡፡ እንደሎሌነት ሲታሰብ ግን ትዕዛዝን መበገር አግባብ ይሆናል፡፡ ጌታ የሚያዘው የጌትነቱን ልክ ማሳያ አድርጎ ነውና!! አንዳንዴ “ልጅነትን የመሰለ ንፅህና የለም” የሚባለውን ለመቀበል መገደድ አግባብ ነው”፡፡ ቅንነት ወሳኝ ነው ለማለት ነው! ከትላንት ለመማር ቅንነት ያስፈልጋል፡፡ ቂም በቀል ሆድ ውስጥ ካመቅን ነገ ተመልሰን ወደዚያው ስህተት እናመራለን፡፡ ያ ከሆነ ከድጡ ወደማጡ መሄድ ነው፡፡ በራሳችን የትላንት ንፍቀ ክበብ ታጥረን፣ ሌላ ለማየት ተገድበን ያለፈው መርግ ከተጫነን፤ አባዜው አልለቀቀንም ማለት ነው፡፡ ገጣሚው እንዳለው፡-
“ያለፈው አልፏል እያልን፣ ዛሬም ወደዚያው ከሄድን
ድግግሞሹ ካጫጨን፣ እኛስ ከትላንት ምን ተሻልን?!”
ከክፋት ወደ ክፋት፣ ከኋላ ቀርነት ወደ ኋላቀርነት፣ ከጥፋት ወደ ጥፋት እንዳንሄድ አስተዋይ ልቦና ይስጠን፡፡ በስራም ቦታ፣ በፖለቲካ ዳርትም ሥፍራ፣ በህዝብ መሰብሰቢያም ሸንጎ፣ በኮንፈረንስና በሴሚናርም፣ በማህበረሰብም፣ በቤተሰብም፣ መልካም ነገሮችን ካላቆየን፤ ከአንዱ ወደ አንዱ መሄድ ከውድቀት ወደ ውድቀት፤ ከድቀት ወደ ድቀት እንደ መጓዝ ነው፡፡ የሀገራችን ገጣሚና ፀሐፌ ተውኔት ፀጋዬ ገ/መድህን እንዳለው፤
“ያገሬ ሰው ነገር፤ አብረን ወደላይ እንብቀል ሲሉት፤ አሸብልቆ ወደታች ወደመሬት ማጎንቆል” ይሆናል፡፡ የዚህ ውጤቱ የአፍሪካው ተረት ነው - “ከክፉ በሬ ጋር ውለህ፣ ወደ ክፉ ሚስት አትሂድ!”


Saturday, 25 October 2014 10:15

የህፃናት ጥግ

የ4 ዓመት ህፃን ከእናቱ ጋር የፎቶ አልበም ሲመለከት ዓይኑ ነፍሰ ጡር ሆና የተነሳችው ፎቶ ላይ ያርፋል፡፡
ህፃን - ማሚ፤ ሆድሽ ለምን ትልቅ ሆነ?
እናት - አንተ ሆዴ ውስጥ ስለነበርክ፡፡
ህፃን - ያኔ ውጠሽኝ የነበረ ጊዜ?
***
ሴትየዋ የ3 ዓመት ዕድሜ ካለው የልጅ ልጃቸው ጋር በስልክ ሲያወሩ ህፃኑ የሚላቸው ስላልተሰማቸው አስሬ “ምን? ምናልከኝ?” እያሉ ያስቸግሩታል፡፡ ህፃን ሆዬም፤ “እማማ፤ ጮክ ብለሽ እያዳመጥሽኝ አይደለም?” አላቸው፡፡
***
አያት የ3 ዓመት ህፃን የሆነውችን የልጅ ልጃቸውን ለማጫወት ያስቡና፤ “ቶሎ ቶሎ እያደግሽ እኮ ነው፤ ትንሽ ቀስ ማለት አለብሽ” ይሏታል፤ እየሳቁ፡፡
ህፃኗ ኮስተር ብላ፤ “የእኔ ጥፋት እኮ አይደለም”
አያት ተገርመው፤ “ታዲያ የማነው?”
ህፃን፤ “የማሚ!”
አያት “እንዴት?”
ህፃን፤ “እሷ ናታ … ቶሎ ቶሎ ልደቴን እያከበረች”
* * *
የ8 ዓመት ህፃን ለእጅ ሥራዋ የሚሆን ጨርቅ ለመቆራረጥ እናቷን መቀስ እንዲሰጧት ትጠይቃለች፡፡ እናትም በአቅራቢያቸው የነበረውንና የወርቅ እጀታ ያለውን ውብ መቀስ አንስተው ሰጧትና፤ “በጥንቃቄ ተጠቀሚበት፤ ለእኔ ትልቅ ትርጉም አለው” ይሏታል፡፡
ህፃን፤ “ዕድሜው ብዙ ነው እንዴ?”
እናት ልጃቸው የመቀሱን ታሪክ የማወቅ ፍላጎት ያደረባት ስለመሰላቸው ማስረዳት ጀመሩ፤ “ከእናቴ ነው የወረስኩት፤ እሷ ደሞ ከእናቷ … እናቷም ….”
ህፃን፤ “ለዚህ ነዋ…”
እናት፤ “ምን የሆነው?”
ህፃን፤ “ዶልዱሞ የማይቆርጠው”

“ክቡር ጠ/ሚ አባታችንን ከሞት ያድኑልን”  የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ልጆች

የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን በእስር ላይ በሚገኙት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ ከአምስት አመታት በፊት የተጣለው የሞት ፍርድ ተፈጻሚ እንዳይሆንና በቆንስላ ሰራተኞች መጎብኘት እንዲችሉ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በግላቸው በላኩት ደብዳቤ መጠየቃቸውን ዘ ኢንዲፔንደንት ከትናንት በስቲያ ዘገበ የአቶ አንዳርጋቸው ልጆች አባታቸውን ከሞት እንዲታደጉላቸውና ከእስር ተፈትተው ዳግም የሚገናኙበትን መንገድ በማመቻቸት በኩል ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው የሚጠይቅ ልብ የሚነካ ደብዳቤ እንደላኩላቸው የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን፣ የልጆቹን ጥያቄ መነሻ በማድረግ ለጠቅላይ ሚንስትር ሃይለማርያም ደብዳቤ መላካቸውን አስታውቀዋል፡፡
የእንግሊዝ የስራ ሃላፊዎች በእስር ላይ የሚገኙትን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን በቋሚነት መጎብኘት እንዲችሉ ግፊት ቢያደርጉም፣ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት በጎ ምላሽ እንዳልሰጡ ለልጆቹና ለእናታቸው በሰጡት ምላሽ የገለጹት ዴቪድ ካሜሩን፣ ከዚህ በፊት የተደረገው ጥረት ውጤታማ አለመሆኑን በማጤን በግላቸው ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ደብዳቤ መላካቸውን አመልክተዋል፡፡የእንግሊዝ መንግስት የቆንስላ አባላት አንዳርጋቸው ጽጌን በቋሚነት መጠየቅና ማማከር የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻችና መንግስታቸው ሲቃወመው የቆየው የሞት ፍርድ ተፈጻሚ እንደማይሆን ማረጋገጫ እንዲሰጥ በላኩት ደብዳቤ መጠየቃቸውን የገለጹት ዴቪድ ካሜሩን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለ ማርያም ለደብዳቤያቸው በጎ ምላሽ እንደሚሰጧቸው ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል፡፡
የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ልጅ የሆነችው የ7 አመቷ ምናበ እና መንታ ወንድሟ ይላቅ፣ ለጠቅላይ ሚንስትር ዴቪድ ካሜሩን በላኩት ደብዳቤ፣ “አባታችን ልጆቹን የሚወድና የሚንከባከብ መልካም አባት ነው፡፡ አባታችንን ከእስር ለማስፈታት ምንድን ነው የሚያደርጉልን?” በማለት መጠየቃቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ የመጀመሪያ ል©cW የ15 አመቷ ህላዊት በበኩሏ፣ “አባታችን በጣም ናፍቆናል፡፡ እባክዎት በቅርብ ጊዜ መልሰው ወደ ቤታችን ያምጡልን” በማለት ስሜቷን እንደገለፀች ዘገባው ጠቁሟል፡፡

በአሁን ወቅት ሰላም ሰፍኗል ተብሏል በቴፒ ከተማ በተደረገው ውይይት ዶ/ር ሽፈራው ተ/ማርያም ተገኝተዋል

     በጋምቤላ ክልል ባለፉት ሳምንታት ግጭት ተቀስቅሶባቸው በነበሩ አካባቢዎች በአሁኑ ሰዓት ሰላም ሰፍኗል የተባለ ሲሆን በግጭቱ ተሳትፈዋል የተባሉ አመራሮችንና ሌሎች አካላትን በቁጥጥር ስር አውሎ ወንጀለኛን የመለየት ስራ እየተሰራ ነው ተብሏል፡፡ ሰሞኑን የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም በተገኙበት ግጭቱ በተፈጠረባቸው የደቡብ ክልልና የጋምቤላ ክልል አዋሳኝ ድንበሮች አመራሮችና ሌሎች የየክልሎቹ ከፍተኛ ባለስልጣናት የ3 ቀናት ውይይት በቴፒ ከተማ አካሂደዋል፡፡
በውይይቱ ላይ ተሳታፊ የነበሩት የጋምቤላ ክልል የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሳይመን ቱርያል ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ የሁለቱ ክልሎች ባለስልጣናት በተገኙበት በተካሄደው ውይይት በግጭቱ ተሳትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩ አመራሮችን ጨምሮ ሌሎች አካላት በህግ ቁጥጥር ስር ውለው የማጣራት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ግጭቱ ተቀስቅሶባቸው የነበሩት የጎደሬ ወረዳና አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ በአሁን ሰዓት መከላከያ ሰራዊትና የፀጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ጥበቃ በማድረግ ላይ መሆናቸውን የጠቆሙት ባለስልጣኑ፤ በአካባቢው ሰላም መስፈኑንም ተናግረዋል፡፡
የተረጋጋ ሁኔታ መፈጠሩን ተከትሎም ህብረተሰቡ ወደ ቀዬው ተመልሶ ሰላማዊ ኑሮውን እየመራ ነው የተባለ ሲሆን ት/ቤቶችም መደበኛ የመማር ማስተማር ስራቸውን መቀጠላቸውም ታውቋል፡፡
በግጭቱ የጠፋው የሰው ህይወትና የወደመው ንብረት በመጣራት ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በግጭቱ ተሳታፊ መሆናቸው በተረጋገጠባቸው አካላት ላይ በሁለት ሳምንት ውስጥ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል ተብሏል፡፡
በአካባቢው ለሁለት ሳምንት በዘለቀው ግጭት የውጭ ሃይሎች ተሳታፊ ሳይሆኑ እንዳልቀረም በውይይቱ ወቅት ተጠቁሟል፡፡
በአዲስ አመት ዋዜማ ከተቀሰቀሰውና በጎደሬ ወረዳ መዘንገር ዞን ከተፈጠረው ግጭት በተጨማሪ በዚሁ ወረዳ ቴፒ አካባቢ በቅርቡ ማንነታቸው ያልታወቁ ታጣቂዎች መንገድ ላይ አድፍጠው በመጠበቅ ከአስር በላይ የፌደራል ፖሊስ አባላትን ገድለዋል፡፡

ውድ ፕሬዚዳንት ኦባማ፡-
ጠብመንጃን መጠቀም ማቆም እንችላለን? እባክህ ማንም ሰው ጠብመንጃ የምትችለውን ሁሉ እያደረግህ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ በጣን ነው የማመሰግንህ፡፡
ታጃህ - የ10 ዓመት ህፃን
ውድ ፕሬዚዳንት ኦባማ፡-
ጠብመንጃን በተመለከተ አንዳንድ የህግ ለውጦች መደረግ ያለባቸው ይመስለኛል፡፡ አሜሪካ ነፃ አገር ናት፤ ቢሆንም ግን በጠብመንጃ ላይ ገደብ መደረግ አለበት የሚል ሃሳብ አለኝ፡፡ እባክህን ሰዎች ከባድ መሳሪያ እንዲይዙ አትፍቀድላቸው፡፡ መሳሪያ ለመያዝ በቂ ምክንያት ሊኖር ይገባል ብዬ አስባለሁ፡፡ ባለፈው ጊዜ ት/ቤት ውስጥ በተከሰተው ግድያ በጣም አዝኛለሁ፡፡
ጆሲ - የ12 ዓመት ህፃን
ውድ ፕሬዚዳንት ኦባማ፡-
እኔ የምኖረው ቺካጐ ውስጥ ነው፡፡ 9 ዓመቴ ነው፡፡ ያንተም ሴት ልጅ 9 ዓመቷ ይመስለኛል፡፡ አዲሱ ቤትህን እንደወደድከው ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ አሁን በጣም ዝነኛ ሆነሃል፡፡ አዲሱ ቤትህ ፒዛ ልትጋብዘኝ ትችላለህ? ኦባማ፤ ይመችህ!
ብሪያን - የ9 ዓመት ህፃን
ውድ ፕሬዚዳንት ካርተር፡-
እባክህን ሰዎች ዓሳ ነባሪዎችን እንዳይገድሉ አስቁማቸው፡፡ በየወሩ ብዙ ዓሳ ነባሪዎች እንደሚገደሉ አውቃለሁ፡፡ ለእነሱ ጥበቃ የሚያደርግ ህግ ብታወጣም ጥሩ ይመስለኛል፡፡
ቦቢ - የ12 ዓመት ህፃን
ውድ ፕሬዚዳንት ካርተር፡-
በጣም ግሩም ሰው ትመስለኛለህ፡፡ ኦሃዮን ከገባችበት የኢነርጂ (ሃይል) ቀውስ በማውጣት አሜሪካን መለወጥ ያስፈልጋል ያልከው ነገር ትክክል ይመስለኛል፡፡ ገና 13 ዓመቴ ቢሆንም እንደ አሜሪካ ፕሬዚዳንትነትህ በጣም እወድሃለሁ፡፡
ብሪያን - የ13 ዓመት ህፃን

Monday, 20 October 2014 08:40

እንቆቅልሽ

  • ከአንድ ፓውንድ ላባና ከአንድ ፓውንድ ሸክላ የትኛው የበለጠ ይመዝናል?
    • በግድግዳ ውስጥ መመልከት እንድንችል ያደረገን የፈጠራ ውጤት ምንድን ነው?
    • በጨለማ ክፍል ውስጥ ነኝ ብለህ አስብ፡፡ እንዴት ከጨለማ ክፍሉ ትወጣለህ?
    • ቆዳዬን ስትገፉኝ እኔ ሳላለቅስ እናንተ ታለቅሳላችሁ፡፡
    • ስትመግቡኝ እኖራለሁ፤ ውሃ ስታጠጡኝ ግን እሞታለሁ፡፡

 


    መልስ
ሁለቱም እኩል ናቸው
መስኮት
ማሰቡን በማቆም
ሽንኩርት
እሳት


Monday, 20 October 2014 08:38

ማራኪ አንቀፅ

    ማታ ከራት በኋላ መኝታ ክፍሌ ውስጥ ብቻዬን ነበርኩ፡፡ በሩ ተንኳኳና ከፈትኩት፡፡ ጋናዊቷ ሄለንና ሲዳናዊቷ አህላም ቆመዋል፡፡ ተዘግቶ ከነበረው በር በስተጀርባ እንደ እኔ ለሥልጠና የመጡ ሴቶች ቆመው አያለሁ የሚል ደቃቅ ግምት እንኳን ስላልነበረኝ ግራ ተጋባሁ፡፡ እኔ ዩኒቨርሲቲ ስማር ሴቶች ወደ ወንዶች፤ ወንዶችም ወደ ሴቶች መኝታ ክፍል ድርሽ እንዲሉ አይፈቀድም ነበር፡፡ ግር ቢለኝም ቀድሜ፣ “ታዲያስ! እንዴት ናችሁ?” ያልኳቸው እኔ ነበርኩ፡፡ ፊቴ ግን፣ “ምነው በሰላም ነው ወደ ወንዶች ዶርም የመጣችሁት?” የሚል ጥያቄ ከአንደበቴ በላይ ጮኸ እንደጠየቃቸው እርግጠኛ ነኝ፡፡
ምናልባት በቃል ካቀረብኩት ሰላምታ ይልቅ ፊቴ ላይ የተንፀባረቀው ጥያቄ በጉልህ ተሰምቷት ይሆናል፤ ጋናዊቷ ሄለን ለሰላምታዬ ምላሽ ሳትሰጥ፣ “አህላም አብረኸን ወደ ባሩ እንድንሄድ ትፈልጋለች፡፡” አለችኝ ፈገግ ብላ፡፡ ከእንግሊዝኛዋ ከምዕራብ አፍሪካ ከመጡ ሰልጣኞች ጋር ጭራሽ የማይነፃፀር ጥርት ብሎ የሚሰማ ነው፡፡ ዩጋንዳ የገባሁት ከሁለት ቀናት በፊት ነበር፡፡ እዚህ በምዕራብ ዩጋንዳ፣ ኪባሌ ደን ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ወደሚገኘው የማካራሬ ዩኒቨርሲቲ የመስክ ሥልጠና ጣቢያ ከሌሎች ሃያ ስድስት ሠልጣኞች ጋር የደረስነው ትላንት ነው፡፡
“አህላም ራሷ አትናገርም እንዴ ሄለን የምታወራላት?” ብዬ እያሰብኩ ዞር ብዬ በትዝብት ሳያት፣ ሱዳናዊቷ አህላም፣ “አዎ፣ ከእኛ ጋር እንድትመጣ ፈልገን ነበር፡፡” ብላ ቀይ ፊቷን በውብ ፈገግታ አደመቀችው፡፡ ፊቷ ላይ የዋህነትና ግልጽነት ይነበባል፡፡ ረጅምና ደርባባ ናት፡፡
መኝታ ክፍሌ ተንኳክቶ በሴቶች ስጋበዝ ከኩራት ይልቅ የተሰማኝ መደነቅ ነበር፡፡ የእኛ አገር ሴቶች መቼም እንዲህ አያደርጉም፡፡ ሱዳኖች እንዲህ ያደርጋሉ ማለት ነው? … አልመሰለኝም፡፡ አህላም የተለየች መሆን አለባት፡፡ ወይም ከእኔ ጋር ማምሸት እንደምትፈልግ ስትነግራት ሄለን አደፋፍራት ይሆናል ወደ መኝታ ክፍሌ የመጡት፡፡ … ለነገሩ ከሌሎች አፍሪካውያን ይልቅ እኔ ከሷ ጋር የሚቀራረብ መልክ አለኝ፡፡ ገና ካሁኑ ዘመዶቿን ናፈቀች ማለት ነው? ብዬ እያሰብኩ፣ ሰለቀኑ ውሏቸው እየጠየቅኳቸው ወደ ባሩ ስንወርድ አህላም ቁጥብ ለመሆን ሞከረች፡፡ እንግሊዝኛዋ ጥሩ ፍሰት የለውም እንጂ ለመግባቢያ በቂ ነው፡፡ ባሩ በረንዳ ላይ ተቀምጠን ለስላሳ ጠጣን፤ ዳማ ተጫወትን፡፡ አህላም ወሬ ለመፍጠር አልሞከረችም፡፡ ጭምት ሆነችብኝ፡፡ አንደበቷን ገና በእንግሊዝኛ ስላላፍታታችም የፈለገችውን እንደልብ ለማውራት ይቸግራታል፡፡ ከሷ ይልቅ በጣም ጥሩ እንግሊዝኛ ከምታወራው ከሄለን ጋር ብዙ ሳናወራ አልቀረንም፡፡ ከሷ ጋር ብዙ ባንጫወትም አህላም አጠገቧ በመቀመጤ ደስተኛ ነበረች፡፡
(ከደራሲ ኢዮብ ጌታሁን “አለላ መልኮች” የተሰኘ ልብወለድ የተቀነጨበ)

Monday, 20 October 2014 08:24

የፀሃፍት ጥግ

* ውሸት ፍጥነት አለው፤ እውነት ደግሞ ፅናት፡፡
ኤዴጋር ጄ.  ሞህን
* እጅግ አደገኛ ውሸት የሚሆኑት በጥቂቱ   የተዛቡ እውነቶች ናቸው፡፡
ጆርጅ ክሪስቶፍ ሊችተንበርግ
* ግማሽ እውነት ማለት ሙሉ ውሸት ነው፡፡
የአይሁዳውያን አባባል
* ለአንተ ብሎ የዋሸ፣ በአንተ ላይም መዋሸቱ    አይቀርም፡፡
የቦስኒያዎች አባባል
* ማንንም ስለማልፈራ ጨርሶ አልዋሽም፡፡
  የምትዋሸው የምትፈራ ሲሆን ብቻ ነው ፡፡
ጆን ጎቲ
* ሁሌም ጨካኝ ሳይሆኑ ሃቀኛ የመሆኛ     
   መንገድ  አለ፡፡
አርተር ዶብሪን
* እንደማንኛውም ውድ እቃዎች ሁሉ    
   እውነትም ብዙ ጊዜ ይጭበረበራል፡፡
ጄምስ ካርዲናል ጊቦንስ
* እውነትን ማበላሸት ከፈለግህ ለጥጠው፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
* ውሸት ስትናገር የአንድን ሰው እውነት   
 የመስማት መብት እየሰረቅህ ነው፡፡
ካሊድ ሆስኒ
* ብዋሽ ግዴለኝም፤ ትክክል አለመሆን ግን  ያስጠላኛል፡፡
ሳሙኤል በትለር
* ሃቀኝነት የጥበብ መፅሐፍ የመጀመርያው  
   ምዕራፍ ነው፡፡
ቶማስ ጄፈርሰን
* ውሸት ከመናገር የበለጠ የሚከፋው ቀሪ     ህይወትን ለውሸት ታማኝ ሆኖ መኖር ነው፡፡
ሮበርት ብራውልት

Monday, 20 October 2014 08:21

ዋሽንግተን - በአዲስ አበባ

        ለትምህርት ወደ አሜሪካ የሄዱት በወጣትነታቸው ነው - በ20 እና በ21 ዓመታቸው፡፡ ከአገር የወጡበትን ዓላማ ለማሳካት ኮሌጅ ገብተው ሴቷ ስለ አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ (ሆርቲካልቸር)፣ ወንዱ ደግሞ ስለ ቴክኒክ ሙያ ተምረዋል፡፡
በአሜሪካ መኖር የሚቻለው እየሰሩ ነው፡፡ ያለበለዚያ ዶላር የሚመነዝር ቅልጥጥ ያለ የከበርቴ ልጅ መሆን የግድ ነው፡፡ ወጣቶቹ እንደዚያ ስላልሆኑ፣ ተግተው መሥራት ነበረባቸው፡፡ በዋሺንግተን ዲሲና ሜሪላንድም “አዲስ አበባ” የተባለ ምግብ ቤት ከፍተው የኢትዮጵያን ባህልና ምግብ በማስተዋወቅ ከ30 ዓመት በላይ እየሰሩ ኖረዋል፡፡
ዕድሜአቸውን በሙሉ በውጭ አገር መኖር አልፈለጉም፡፡ ወደ አገራቸው ተመልሰው በቋጠሯት ገንዘብ ኢንቨስት በማድረግ፣ ለወገኖቻቸው የሥራ ዕድል በመፍጠር፣ ለአገራቸው ዕድገት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ለማበርከት ወሰኑ፡፡
ወ/ሮ ወርቅነሽ ጌታቸውና አቶ አስፋው አምዴ የተወለዱት በአዲስ አበባ ከተማ ነው፡፡ አቶ አስፋው፣ በቀድሞው ልዑል መኮንን በአሁኑ አዲስ ከተማ መሰናዶ ት/ቤት የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ አሜሪካ የሄዱት እ.ኤ.አ በ1970 ዓ.ም ነው፡፡
ወ/ሮ ወርቅነሽ ደግሞ 1ኛ ደረጃን በአርበኞች ት/ቤት፣ 2ኛ ደረጃን በቀድሞው እቴጌ መነን፣ በአሁኑ የካቲት 12 መሰናዶ ት/ቤት ጨርሰው ወደ አሜሪካ ዋሽንግተን የተጓዙት ከአምስት ዓመት በኋላ ነበር፡፡
በዚያው ዓመት ነበር ሁለቱ ጥንዶች የተዋወቁት፡፡ ከዚያም እንደ ድርጅትም እንደ ማህበረሰብም ሆነው ከዚህ የሚሄዱትን ኢትዮጵያውያን በመቀበል፣ አገሪቷንም ለአሜሪካ በማስተዋወቅ በአምባሳደርነት ሲያገለግል የቆየውንና ታዋቂውን “አዲስ አበባ ምግብ ቤት” እ.ኤ.አ በ1984 ዓ.ም በዋሽንግተን ዲሲ መክፈታቸውን ይናገራሉ፡፡
እዚያም የኢትዮጵያን ምግብና ባህል በማስተዋወቅ ለ21 ዓመት ሰሩ፡፡ ምግብ ቤቱ የበለጠ ታዋቂ እየሆነ፣ የሚያስተናግደው አበሻም ሆነ ፈረንጅ እየጨመረ ሲሄድ፣ መኪና ማቆሚያ ቦታ ጠበበ፡፡
 በ2005 ዓ.ም ሜሪላንድ ወደተባለችው ከተማ ተዛውረው፣ እዚያም ታዋቂውን አዲስ አበባ ምግብ ቤት መክፈታቸውን ተናግረዋል፡፡ በሜሪላንድ 8 ዓመት ከሰሩ በኋላ ነው ጓዛቸውን ጠቅልለው ወደ አዲስ አበባ የመጡት፡፡ጥንዶቹ ከ10 ዓመት በፊት ቦታ ገዝተው የሆቴል ግንባታ ጀመሩ፡፡
70 የመኝታ ክፍሎች ያሉትና አትላስ አካባቢ የሚገኘው ዋሺንግተን ሆቴል ሥራ የጀመረው በቅርቡ ቢሆንም በሚሰጠው ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በህብረተሰቡ ዘንድ ጥሩ ተቀባይነት እያገኘ መሆኑን ወ/ሮ ወርቅነሽ ይናገራሉ፡፡
ለስብሰባ፣ ለመዝናናትም ሆነ ለሥራ… ከውጭ ለሚመጡ መሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና የቢዝነስ ሰዎች ያዘጋጀነው 5ኛና 6ኛ ፎቅ ያሉት ቪአይፒ ክፍሎች እኛን ከሌሎች ሆቴሎች ይለዩናል ያሉት ወ/ሮ ወርቅነሽ፤ በሁለቱ ፎቆች ያሉት ክፍሎች ለአንድ መሪ ቤተሰብ፣ ባለሥልጣናትና አጃቢዎች ወይም ለአንድ አገር ዲፕሎማትና አብረውት ለሚመጡ የሥራ ኃላፊዎች ወይም ለአንድ አገር የቢዝነስ አባላት ቡድን … የሚከራዩ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ቪአይፒ ክፍሉ የራሱ ሳሎን፣ የራሱ ምግብ ማብሰያ (ኪችን) ለቤተሰብና አብረው ላሉ እንግዶች የሚሆኑ 5 መኝታ ክፍሎች፣ ጃኩዚ፣ ስቲምና ሳውና ባዝ፣ ዋና መኝታ ቤት፣ የራሱ ባርና መዝናኛ ቴራስ፣ ልዩ የደህንነት ጥበቃ… ያሉት መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አሁን ያልተጠናቀቁ ነገሮች ስላሉ ሁሉም ነገር ሲያልቅ ሆቴሉ በጠቅላላ 180 ሚሊዮን ብር ይፈጃል ያሉት አቶ አስፋው፤ ዋሺንግተን በነበረው አዲስ አበባ የባህል ምግብ ቤት የተሰየመው የምግብ አዳራሽ ሁሉንም ዓይነት ባህላዊ ምግቦች ያዘጋጃል ብለዋል፡፡
 ኮሎምቢያ በማለት የበሰየሙት ዘመናዊ ሬስቶራንት ከ40 በላይ የውጭ አገር ምግቦች እንደሚያዘጋጅ፣ ሁለት ባር እንዲሁም በመቅደላ የተሰየመ ትልቅ አዳራሽ፣ ጆርጅታውን ጂምና ስፓ፣ አዲስ አበባን 360 ዲግሪ እያዩ የሚዝናኑበትና በ18 ዲስትሪክት የተሰየመ ቴራስ ሬስቶራንትና ባር፣ … እንዳሉት ገልጸው፤ ሆቴሉንና የተለያዩ አገልግሎት መስጪያዎችን በውጭ አገር ስሞች የሰየሟቸው ለብዙ ዓመታት የሚያውቋቸውን የአሜሪካ አካባቢዎች ለማስታወስ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡የሆቴሉ ምግብ በእንግዶች የተወደደ ንፁህ፣ ጣፋጭና ጥራቱን የጠበቀ ቢሆንም ዋጋው ተመጣጣኝ በመሆኑ ኪስ አይጐዳም፣ አንድ ምግብ በ150 ብር መመገብ ይቻላል፣ ከዚያም በታች አለ ብለዋል፡፡
የመኝታ ክፍሎቹ ዋጋ ሲንግል ቤድ 95 ዶላር፣ ደብል ቤድ 120 ዶላር፣ ሱት ክፍሎች 160 ዶላር፣ ልዩ የሆነው ቪአይፒ 950 ዶላር እንደሆኑ ጠቅሰው፣ ስብሰባ ሲኖርና አስጐብኚ ድርጅቶች በርከት ያሉ እንግዶች ሲያመጡ የዋጋ ቅናሽ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡
ሆቴሉን ሲሰሩ ነገሩ ሁሉ አልጋ በአልጋ እንዳልነበረ የጠቀሱት አቶ አስፋው፤ መንግሥት ኢንቨስትመንትን ለማበረታታት በሰጠው ዕድል ቋሚ ዕቃዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዳስገቡ ገልፀው፣ ከባንክ ብድር ማግኘት፣ የጉምሩክ ቢሮክራሲ፣ ባለሙያ የሆነ የኮንስትራክሽን ሠራተኛ እጥረት… ዋና ዋናዎቹ ችግሮች እንደነበሩ ገልፀዋል፡፡ ሆቴሉ ለ130 ዜጎች የሥራ ዕድል እንደፈጠረም ለማወቅ ተችሏል፡፡