Administrator

Administrator

 ሩሲያዊው ቢሊየነር ድሚትሪ ራይቦሎቭሌቭ፤ በቅርቡ ከቀድሞ ሚስቱ ጋር የፈፀመውን ፍቺ እንደ ድንገተኛ የቢዝነስ ኪሳራ መቁጠሩ አይቀርም። የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብን እኮ ነው ክፈላት የተባለው፡፡ ቢሊዬነሩ 27 ዓመት በትዳር አብራው ከዘለቀችው ኢሌና ጋር ፍቺ መፈፀሙን ተከትሎ የስዊስ ፍ/ቤት የቀድሞ ባለቤቱ 4.8ቢ. ዶላር ብት ልትካፈል ይገባል ሲል ወስኗል፡፡ የኢሌና ጠበቃ በሰጠው መግለጫ “እጅግ ውድ ፍቺ ነው” ብሎታል። ይሄ እጅግ ውድ የፍቺ ክፍያ ለድሚትሪ ከፍተኛ ኪሳራ ሲሆን ለቀድሞ ሚስቱ ግን የማይታመን የሃብት ጎርፍ ነው፡፡
የዛሬ 15 ዓመት ደግሞ ሌላ ውድ ፍቺ ተፈጽሟል። አውስትራሊያዊው የሚዲያ ከበርቴና ለ32 ዓመታት በትዳር አብራው የኖረችው የ3 ልጆቹ እናት አና ሙድሮክ፤ እ.ኤ.አ በ1999 ዓ.ም ፍቺ ሲፈጽሙ ፍ/ቤት ለሚስትየው የ1.7 ቢሊዮን ዶላር ሃብት (110 ሚ.ዶላር ካሽ ይጨምራል) እንድትካፈል ነበር የወሰነላት። ከሃብት ክፍፍሉም በኋላ ሁለቱም የየራሳቸውን ህይወት ቀጥለዋል፡፡ በእርግጥ ሩፐርት ሙድሮክ በ38 ዓመት ከምታንሰው ዌንዲ ዴንግ ጋር ትዳር የመሰረተው ፍቺ በፈፀመ በ17ኛ ቀኑ ነበር ሳይፈታ በፊት ያዘጋጀ እኮ ነው የሚመስለው፡፡ አናም በበኩሏ፤ ከወራት ቆይታ በኋላ አንድ ኢንቨስተር አግብታለች፡፡ በሃብት ላይ ሃብት አትሉም፡፡ እነ አሜሪካን በመሳሰሉ የበለፀጉ አገራት፤ ቢሊዬነሮችን አግብቶ መፍታት አትራፊ ኢንቨስትመንት እየሆነ ነው፡፡

ውድ እግዚአብሔር፡-
ስቴፕለር ከታላላቅ ፈጠራዎችህ አንዱ ይመስለኛል፡፡
        ሩት
- የ5ዓመት ህፃን

ውድ እግዚአብሔር፡-
ቀናተኛ ዓምላክ ነህ ሲባል ምን ማለት ነው? እኔ እኮ ሁሉ ነገር ያለህ ነበር የሚመስለኝ፡፡
                        ጆን
- የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
የሰንበት ት/ቤት ለምን እሁድ ሆነ? የእረፍት ቀናችን እኮ ነው፡፡
        ራሄል
 - የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
በእናትህ ትንሽዬ ፈረስ ላክልኝ፡፡ ብትፈልግ መዝገብህን ማየት ትችላለህ፡፡ ምንም ጠይቄህ አላውቅም፡፡
                        ብሩስ
- የ 5 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ምናልባት ቃየንና አቤል የየራሳቸው ክፍል ቢኖራቸው ኖሮ አይገዳደሉም ነበር፡፡
ላሪ
 - የ8 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
አንዳንዴ የፀሎት ጊዜም ባይሆን ስለአንተ አስባለሁ፡፡
ማርሻ - የ6 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
ለአንተ ከሚሰሩልህ ሰዎች ሁሉ የበለጠ የምወዳቸው ኖህና ዳዊትን ነው፡፡
ሳሚ
- የ7 ዓመት ህፃን
ውድ እግዚአብሔር፡-
በመፅሃፍ ቅዱስ ላይ እንዳለው ሰውዬ 900 ዓመት መኖር እፈልጋለሁ፡፡ እወድሃለሁ እሺ፡፡
ዶን
- የ6 ዓመት ህፃን

በአብዱል ፈታህ አብደላህ አዘጋጅነት በኮንሶ የባህል ህግ ላይ ጥናት ተደርጐበት የተዘጋጀው “ሤራ አታ ኾንሶ” የተሰኘ መጽሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መጽሐፉ ትኩረት ያደረገው በኮንሶ የባህል ህግ ስርዓት ላይ ሲሆን በጥናቱ ውስጥ የኮንሶ የአገር ሽማግሌዎችና የአካባቢው ተወላጅ ምሁራን ተሳትፈውበታል፡፡ በ197 ገፆች የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ በኮንሶ የባህል ህግ ስርዓት ላይ ትኩረት ቢያደርግም አጠቃላይ የማህበረሰቡን ባህል፣ ወግ፣ ቋንቋና ሃይማኖታዊ ሁነቶች ይቃኛል፡፡ መጽሐፉ በኢትዮጵያ የፍትህ ሥርዓቶች ማዕከልና በኮንሶ ወረዳ አስተዳደር ትብብር ታትሞ በነፃ ለአንባቢያን ደርሷል፡፡ በተያያዘ ዜና የቱሪዝምና እና የሙዚየም ማውጫዎችን በማሳተም የሚታወቀው ሀገሬ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን፤ የኮንሶ ህፃናት ስለ አካባቢያቸው የቱሪዝም መስህቦች እንዲያውቁ የሚረዳቸውን “ኮንሶን ለህፃናት” የተሰኘ የቱሪዝም መጽሐፍ ለንባብ ያበቃ ሲሆን “ሴራ አታ ኾንሶ” ከተባለው መጽሐፍ ጋር በኮንሶ ካራት ከተማ ባለፈው ሳምንት ተመርቋል፡፡

መቀመጫውን አሜሪካ ሂዩስተንና ኢትዮጵያ በማድረግ በቴአትር ዘርፍ የሚንቀሳቀሰው ዮሐንስ ቴአትር ፕሮዳክሽን፤ “ደላሎቹ” የተሰኘውን ቴአትር በሚቀጥለው ሳምንት እሁድ  ለእይታ ያበቃል፡፡ የምርቃት ስነስርዓቱ በዕለቱ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት በሀዋላ ሴንትራል ሆቴል እንደሚካሄድም ድርጅቱ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
በኤርሚያስ ጌታቸው ተደርሶ፣ በህይወት አራጌ በተዘጋጀው በዚህ ቴአትር ላይ ችሮታው ከልካይ፣ ህይወት አራጌ፣ ኤርሚያስ ጌታሁንና ሌሎች አንጋፋና ወጣት ተዋንያን እንደሚሳተፉበት ለማወቅ ተችሏል፡

በዶ/ር መልካሙ ታደሰ የተዘጋጀው “የጐጆ ድርጅት” (Home business) የተሰኘ መጽሐፍ ዛሬ ከቀኑ በ8 ሰዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የባህል ማዕከል ይመረቃል፡፡ መጽሐፉ በዋናነት ዜጐች እውቀታቸውን፣ ችሎታቸውን እንዲሁም ትርፍ ጊዜያቸውን በመጠቀም ከመኖሪያ ቤታቸው ተጨማሪ ገቢ በማግኘት፣ ራሳቸውንና አገራቸውን ተጠቃሚ የሚያደርጉበትን መንገድ ያመላክታል ተብሏል፡፡ በምረቃው ላይ በመጽሐፉ ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግ ታውቋል፡፡

በደራሲ ልዑል ግርማ የተዘጋጀው “ፍቅርና ትግል” የአጫጭር ልቦለዶች መድበል ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ መፅሀፉ በፍቅር ታሪኮችና በማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥን ሲሆን በ287 ገፆች የተቀነበበ ነው፡፡ በ45 ብር ለገበያ እንደቀረበም ታውቋል፡፡ ደራሲ ልዑል ግርማ ከዚህ ቀደም “አራት አርባ አራት” የተሰኘ አነጋጋሪ ረዥም ልብ-ወለድ የፃፈ ሲሆን “የወንድሜ ሚስት” የተሰኘ የአጭር ልብወለድ መድበል ለንባብ ማብቃቱ የሚታወስ ነው፡፡

በአርቲስትና የፎቶግራፍ ባለሙያ ወንድወሰን በየነ የተዘጋጀውና “A Glimpse of Ethiopian II” የተሰኘ የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽን በራዲሰን ብሉ ሆቴል ይከፈታል፡፡ ኤግዚቢሽኑ የፊታችን ሐሙስ ተከፍቶ እስከ ግንቦት 15 ቀን 2006 ዓ.ም ለተመልካች ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በኤግዚቢሽኑ መልክአምድር፣ አሮጌ ቤቶችንና ሌሎች ተፈጥሯዊ ነገሮችን የሚያስቃኙ ፎቶግራፎች እንደሚቀርቡ ታውቋል፡፡

በደራሲ ደሳለኝ ስዩም የተፃፈው “የታሰረ ፍትህ” የተሰኘ ኢ-ልብወለድ መጽሐፍ ታትሞ ለገበያ ቀረበ፡፡ የመጽሐፉ ጭብጥ በህዝብና በገዢው ፓርቲ ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው ተብሏል፡፡ በ3 ምዕራፎችና በ148 ገፆች የተዘጋጀው መጽሐፉ፤ በ35 ብር ከ50 እየተሸጠ ነው፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም “ደም የተፋ ብዕር” የሚል የግጥም መድበልና “የጠረፍ ህልሞች” የተሰኘ ረዥም ልብወለድ ለአንባቢያን ማድረሱ ይታወቃል፡፡

ፈጠራው በአዲስ አበባ የትራፊክ አደጋን ይቀንሳል ተብሏል
“እነዚህ የላቀ የፈጠራ ክህሎት ከታደሉ የአሜሪካ ተማሪዎች ጥቂቶቹ ናቸው” - ባራክ ኦባማ

     የ18 አመት ዕድሜ ያለው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ተማሪ ፈለገ ገብሩ፣ የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ ያስችላል የተባለውን የቴክኖሎጂ ፈጠራውን ባለፈው ሳምንት በዋይት ሃውስ በተካሄደው የሳይንስ ትርዒት ላይ ማቅረቡን ኤምአይቲ ኒውስ ዘገበ፡፡
በማሳቹሴትስ የሚገኘውን ኒውተን ኖርዝ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወክሎ በትርዒቱ ላይ የቀረበው ፈለገ፣ የትምህርት ቤት ጓደኛው ከሆነችው ካሬን ፋን የተባለች የ17 አመት ወጣት ጋር በመተባበር የፈጠረው አዲስ ቴክኖሎጂ፣ የማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን በማስተላለፍና እንቅስቃሴውን የተሳለጠ በማድረግ በአዲስ አበባ ከተማ የሚታውየን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ የሚያስችል እንደሆነ ተነግሯል፡፡
በሳይንስ ትርዒቱ ላይ ተገኝተው የወጣቶችን የተለያዩ የፈጠራ ስራዎች የተመለከቱት ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ፣ በዝግጅቱ ላይ ስራዎቻቸውን ላቀረቡ ተማሪዎች ያላቸውን አድናቆት በመግለጽ፣ እነዚህ በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉ ወጣቶች፣ የላቀ ፈጠራ ክህሎት ከታደሉ በርካታ የአሜሪካ ተማሪዎች ጥቂቶቹ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ዴቪድ ሁድሰን በዋይት ሃውስ ድረገጽ ላይ ፈጠራውን በተመለከተ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ “እነዚህ ወጣቶች በአለማችን እንደ ኢትዮጵያ በትራፊክ አደጋ በርካታ ቁጥር ያላቸው እግረኞች የሚሞቱበት አገር እንደሌለ በማጤን ነው፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ተግባራዊ የሚደረግና አደጋውን ለመቀነስ የሚያስችል ፈጠራ በማመንጨት ያቀረቡት ”ብለዋል፡፡
የቴክኖሎጂ ፈጠራው አሽከርካሪዎች እግረኞችን በተመለከተ መረጃ የሚያገኙበት እንዲሁም እግረኞችም የተጨናነቁ መንገዶችን ያለ ችግር ማቋረጥ የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው ያሉት ሁድሰን፣ ፈጠራው የጸሃይ ብርሃንን በሃይል ምንጭነት የሚጠቀምና የተሸከርካሪዎችን ፍጥነት በማስላት የተወሰነ ቦታ ላይ የሚደርሱበትን ጊዜ የሚያሰላ፣ ለእግረኞችም መንገድ ማቋረጥ የሚችሉበትን የተመረጠ ጊዜ የሚጠቁም መሆኑን ተናግረዋል፡፡
 በሚማሩበት ትምህርት ቤት የተቋቋመው ኢንቬንቲም የተባለ የፈጠራ ክበብ መሪዎች የሆኑት ፈለገ እና ካረን በፈጠራ ስራ ላይ የመግፋት ዕቅድ ያላቸው ሲሆን፣ ፈለገ በአሁኑ ወቅት በብራውን ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ሳይንስና የቪዡዋል አርት የመጀመሪያ ዓመት ትምህርቱን በመከታተል ላይ ይገኛል፡፡“የፈጠራ ስራዎቻቸውን በዋይት ሃውስ የሳይንስ ትርዒት ላይ እንዲያቀርቡ መጋበዛቸው፣ ለእነዚህ ልጆች እጅግ የሚደንቅ ክብር ነው የሚያጎናጽፋቸው፡፡ ፈለገም ሆነ ሌሎቹ ተሳታፊ ተማሪዎች ለሌሎች ወጣቶች መነቃቃትን የሚፈጥር የፈጠራ ተነሳሽነትና የአላማ ጽናት የተላበሱ ናቸው።” ብለዋል ሌሊልሰን-ኤምአይቲ የተባለው የፈጠራ ፕሮግራም መምህርና የፕሮጀክቱ አማካሪ የሆኑት ሌይ ስታብሩክስ፡፡
ኤምአይቲ ኒውስ እንደዘገበው፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊው ገብሩ፣ በአገሩ በኢትዮጵያ ከትራፊክ አደጋ ጋር በተያያዘ እግረኞች የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች በተመለከተ ለኢንቬንቲቭ ያቀረበውን መረጃ መነሻ በማድረግ ፕሮጀክቱ ሊቀጥል ችሏል፡፡

Saturday, 07 June 2014 14:09

የፍቅር ጥግ

ፍቅር እሳት ነው፡፡ ልብህን ያሙቀው ወይም ቤትህን ያቃጥለው ግን ማወቅ አትችልም፡፡
ጆአን ክራውፎርድ
ብዙ ሰዎች ካንተ ጋር በሊሞዚን ተሳፍረው መሄድ ይሻሉ፡፡ አንተ የምትፈልገው ግን ሊሞዚኑ ሲበላሽ አብረውህ አውቶብስ የሚሳፈሩትን ነው፡፡
ኦፕራ ዊንፍሬይ
ፍቅር እርስ በእርስ መተያየት አይደለም፤ ወደ አንድ አቅጣጫ አብሮ ማየት እንጂ፡፡
አንቶይኔ ዴ ሴይንት ኢኤክዮፔሪ
ፍቅር ከባድ የአዕምሮ በሽታ ነው፡፡
ፍቅር ማብሪያ ማጥፊያው በሌላ ሰው ቁጥጥር ሥር የሆነ የኤሌክትሪክ ብርድልብስ ነው፡፡
ካቲ ካርሊሌ
ፍቅር ፒያኖ እንደመጫወት ነው፡፡ መጀመሪያ በህጎቹ መሰረት መጫወት መማር አለብህ፡፡ ከዚያ ህጎቹን ረስተህ ልብህ እንዳዘዘህ መጫወት ይኖርብሃል፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
በመጀመሪያ እይታ የሚይዝ የፍቅር ልክፍት በሁለተኛ እይታ ይድናል፡፡
የአሜሪካዊያን አባባል
ፍቅር ሰዎችን ይፈውሳል - ሰጪውንም ተቀባዩንም፡፡
ዶ/ር ካርል ሚኒንገር
ፍቅር ትጋት የሚጠይቅ ከባድ ሥራ ነው፡፡ ከባድ ሥራ ደግሞ አንዳንዴ መጉዳቱ አይቀርም፡፡
ያልታወቀ ደራሲ