Administrator

Administrator

- ቡና ጠጪ ይጭነቀው?.... ምን በወጣው? የቡና ምርትን መጨመር እየተቻለ!

 

የቡና ዋጋ የማይቀመስ እየሆነ ነው ብሏል የሰሞኑ የዎል ስትሪት ጆርናል ዘገባ። በዓለም ገበያ የአንድ ኪሎ ቡና ዋጋ ከ7 ዶላር በላይ ሆኗል። ከአምናው ጋር ሲነጻጸር ዕጥፍ ገደማ ነው ብሏል- ጋዜጣው። እጅግ እየናረ የመጣው ግን ከጥቅምት ወር ወዲህ ነው።
በሁለት ወር ልዩነት የአንድ ኩንታል ቡና አማካይ ዋጋ፣ ከ520 ዶላር ወደ 730 ዶላር አሻቅቧል።
በ1969 ዓ.ም የተመዘገበውን ከፍተኛ ዋጋ በመብለጥ የዘንድሮው ዋጋ አዲስ ሪከርድ ሆኖ ተመዝግቧል።
ቡና ፉት ማለት እንደ ቻይና በመሳሰሉት አገራትም እየተለመደ ስለመጣ ገበያው ሰፍቷል። ዋጋውም ባለፉት ወራት ወደ ላይ ሲጨምር ነበር። ከጥቅምት ወር ወዲህ ያሻቀበው ግን ከብራዚልና ከቬትናም የቡና ምርት ችግር ጋር የተያያዘ ነው።
ዘንድሮ የብራዚል የቡና አዝመራ ከመድረሱ በፊት፣ በዝናብ እጥረት እንደተጎዳ የደቡብ አሜሪካ የቡና ገበያ ባለሙያ ገልጸዋል። ከዝናብ እጥረት በተጨማሪ በሞቃት የአየር ጸባይ የዘንድሮ የቡና ፍሬው ጫጭቷል። ለከርሞ ፍሬ መያዝ ያለባቸው የቡና ዛፎችም ስለጠወለጉ ምርታቸው እንደሚቀንስ ባለሙያው ገምተዋል።


ከሌሎች ኋላ ተነስተው በቡና ምርት ትልቅ ደረጃ ላይ የደረሱት የቬትናም ገበሬዎችን ችግር ገጥሟቸዋል። የዓመቱ ዝናብ ጊዜውን ጠብቆ አልጣለም። እንደምንም ለፍሬ የደረሰው ቡና በሚሰበሰብበት ወቅት ደግሞ ኃይለኛ ዝናብ ድርቅና ጎርፍ መጣባቸው። የገበሬዎችን ሥራ እንደአወሳሰበው የጋዜጣው ዘገባ ይገልጻል።
በእርግጥ የቡና ዋጋ እንዲህ እንደተሰቀለ አይቀርም። የዋጋው ውድነት ቡና ጠጪዎችን የሚፈታተን ከሆነ ፍጆታቸውን ይቀንሳሉ። በተለይ አዳዲስ ለማጅ የቡና ደንበኞች የዋጋ ውድነቱን የመሸከም ትዕግሥት ብዙም አይኖራቸውም። ምክንያት፣ ከቡና ጋር የሚያራርቅ ሰበብ ይሆንባቸዋል።ይህም ባይሆን ግን፣ የቡና ምርት አንዴ ሲበላሽ መልሶ ይሻሻላል። የሌሎች አገራት ገበሬዎች ይገቡበታል።
ለጊዜው ግን ዋጋ አሻቅቧል። እስኪወርድ ድረስም እንደ ኢትዮጵያ በመሳሰሉ አገራት ለቡና ገበሬዎችና ነጋዴዎች ልዩ አጋጣሚ ይሆንላቸዋል። በተለይ ለኢትዮጵያውያኑ።
ሐምሌ ወር ላይ የዶላር ምንዛሬ ተሻሽሎላቸዋል። ወደ ውጭ የሚላከው የቡና መጠንም ጨምሯል።
በዚህ ላይ የዓለም የቡና ዋጋ በጥቂት ወራት ውስጥ እንዲህ ሲያሻቅብ፣ ለኢትዮጵያ የቡና ገበሬዎችና ነጋዴዎች ተጨማሪ ልዩ አጋጣሚ ይሆንላቸዋል። እስከ መቼ ዋጋው እያሻቀበ እንደሚቀጥል ባይታወቅም፣ ዋጋው በተወሰነ ደረጃ ተመልሶ እንደሚቀንስ ነው የሚጠበቀው። እስከዚያው ግን፣ከቡና ኤክስፖርት የሚገኘው ጥቅም ዘንድሮ ከሌሎቹ ዓመታት ሁሉ የላቀ እንደሚሆን ግን አያጠራጥርም።
የአገር ውስጥ ቡና ጠጪዎች ግን ፈረደባቸው። ከኑሮ ውድነት ጋር ተደማምሮ የቡና ዋጋ መጨመሩ ይጎዳቸዋል።
ምናልባት ግን ወደ መፍትሄ ያመራ ይሆናል። የቡና ምርት እየጨመረ ሊሄድ ይችላል።


የቬትናም ገበሬዎች የቡና ምርት ከ30 ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ገበሬዎች ያነሰ ነበር። ዛሬ፣ ከኢትዮጵያ ምርት የሚበልጥ ሦስት ዕጥፍና ከዚያ በላይ የቡና መጠን ያመርታሉ። በሠላሳ ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ምርት ስላልጨመረ አይደለም። የኢትዮጵያ ምርት እንደጨመረ ዓለማቀፍ የቡና ምርት መረጃ ያሳያል። ከ2 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 6 ሚሊዮን ኩንታል።
የቬትናም የቡና ምርት ግን በሠላሳ ዓመታት ውስጥ ወደ 15 ዕጥፍ ደርሷል። ወደ 20 ሚሊዮን ኩንታል ገደማ።
የዓለም የቡና ምርት ከ60 ሚሊዮን ኩንታል ወደ 110 ሚሊዮን ኩንታል የጨመረው በቬትናም ገበሬዎች ብርታት ነው ማለት ይቻላል። ለነገሩ፣ ባለፉት 30 ዓመታት በኮሙኒዝም ምክንያት ታግዶ የቆየው የግል ኢንቨስትመንት ከተፈቀደ ወዲህ እንደ ቬትናም የቀናው አገር የለም - በእርሻም በኢንዱስትሪም።
ከጠቅላላ የአፍሪካ የቡና ምርት፣ የቬትናም ምርት ይበልጣል።
15 ሚሊዮን ኩንታል የነበረው የብራዚላውያን የቡና ምርት፣ ዛሬ ወደ 30 እና 35 ሚሊዮን ኩንታል ደርሷል - እንደ አየሩ ሁኔታ።
የቡናና ሻይ ባለሥልጣን መስሪያ ቤት እንደገለጸው ከሆነ፣ ከሐምሌ ወዲህ በአራት ወራት 1.5 ሚሊዮን ኩንታል ቡና ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ ተሸጧል - በ647 ሚሊዮን ዶላር።
ብዙ ምርት ለመላክ ገበሬዎችንና ነጋዴዎችን ያነሣሣቸው ነገር ቢኖር ነው።
ምን ያህል እንዳነሣሣቸው ለማየት ያህል፣ በመንግሥት ቀደም ሲል የተገመተውን ዕቅድና በተግባር የታየውን የንግድ መጠን ማነጻጸር እንችላለን።
ብዙውን ጊዜ የመንግሥት የግምት ዕቅድ እንደ ሰማይ የራቀ ምኞት ይመስል የለ! የቡና ገበሬዎችና ነጋዴዎች በአራት ወራት ውስጥ 1 ሚሊዮን ኩንታል ቡና ወደ ውጭ ይልካሉ ተብሎ ነበር በመንግሥት የተገመተው። “ዕቅድ” ብለው ነው የሚጠሩት። መንግሥት ቡና ተክሎ የሚለቅም ያስመስሉታል።
ዕቅድ የሚባለው በራስ ለሚከናወን ስራ ነው መቼም። ገበሬዎችና ነጋዴዎች ለሚሰሩት ነገር፣ መንግሥት “ዕቅድ” አወጣሁ ቢል ብዙም ትርጉም አይሰጥም። በእርግጥ መንግሥት ብዙ ገቢ ስለሚያገኝበት፣ አስቀድሞ “የግምት ትንበያ” ማዘጋጀቱ ጠቃሚ ነው። “ዕቅድ” ከማለት ይልቅ “ግምት”፣ ወይም “ትንበያ” ቢል ይሻላል ለማለት ነው።
የሆነ ሆኖ፣ መንግሥት 1 ሚሊዮን ኩንታል ቡና ወደ ውጭ እንደሚላክ ቢተነብይም፣ በተግባር ግን ከትንበያው በ50 በመቶ የሚበልጥ ምርት ተልኳል። 1.5 ሚሊዮን ኩንታል። በእርግጥ ብዙ ምርት ተላከ ማለት የጥራት ደረጃው እንደ ዓምናው ነው ማለት አይደለም። እዚሁ ሊቀር ይችል የነበረውም ነው የሚላከው። እናም አማካይ ዋጋውን ዝቅ ሊያደርገው ይችላል።


እንዲያም ሆኖ፣ በቡና የውጭ ንግድ ላይ አስገራሚ ለውጥ እንደታየ አያጠራጥርም።
የጥቅምት ወርን ለይተን ብናይ፣ ከዓምናው ጋር ሲነጻጸር፣ ዕጥፍ ያህል የቡና ምርት ወደ ውጭ ተልኳል።
አምና 177 ሺ ኩንታል፣ ዘንድሮ 351 ሺ ኩንታል።
በዚህ አያያዙ የሚቀጥል ይመስላችኋል? ሊቀጥል ይችላል። የቻይና ኩባንያዎች ብቻ፣ ቢያንስ ቢያንስ 1 ሚሊዮን ኩንታል የኢትዮጵያ ቡና ለመግዛት ማቀዳቸውን ገልጸዋል።
እናም በዚህ አያያዙ፣ በዓመት ውስጥ እስከ 5 ሚሊዮን ኩንታል የሚደርስ ቡና ወይም ከዚያ በላይ ወደ ዓለም ገበያ መሄዱ ይቀራል?
ከ1.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ፣ ምናልባትም እስከ 2 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ገቢም ሊያመጣ ይችላል።
በእስከ ዛሬ ዓመታዊ የቡና ኤክስፖርት ከፍተኛው መጠን 3 ሚሊዮን ኩንታል ነው። የዐሥራ አምስት ዓመታት መረጃዎችን ስናይ ግን በአብዛኛው ከ2 እስከ 2.5 ሚሊዮን ኩንታል ነው- የአራችን የቡና ኤክስፖርት።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው “ከፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በብሔራዊ ቤተመንግሥት በነበረን የሁለትዮሽ ውይይት ሰፋ ያለ መጠነርዕይ ባላቸው የሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገናል” ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ እና የፈረንሳይ መንግሥት በብሔራዊ ቤተመንግስት እና በመካሄድ ላይ ባለው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እድሳት ሥራዎች ላይ ላደረጉት አስተዋፅዖም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በውይይታችን በተለያዩ ዘርፎች የሚኖሩ ትብብሮችን የፈተሽን ሲሆን የፈረንሳይን ኢንቨስትመንት መጨመርን አስመልክቶ ብሎም በትምህርት እና ባሕል ዘርፎች ያለንን ግንኙነት በማጠናከር ጉዳዮች ላይ ተነጋግረናል” ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በውይይቱ የሀገራቱን ታሪካዊ ትስስር ይበልጥ የመገንባት አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት መስጠታቸውንም አመላክተዋል፡፡

የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሐውልት ሥር የአበባ ጉንጉን አስቀምጠዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤም ለፕሬዚዳንት ማክሮን የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

“ብሔራዊ ባንክ ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት ጉልህ ሚና ይጫወታል”

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ የሰጡት የብሔራዊ ባንክ ገዥ የአገሪቱን የፋይናንስ ሥርዓት ዲጂታል ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል። አክለውም፤ በዚህ ዓመት በባንኮች የተመቻቹ የዲጂታል የገንዘብ ዝውውሮች፣ ከጥሬ ገንዘብ ልውውጦች መብለጣቸውን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ የባንክ ተግባራት ሙሉ በሙሉ በብሔራዊ ባንክ ቁጥጥር ስር መሆኑን የባንኩ ገዢ አቶ ማሞ ምሕረቱ አስታውቀዋል። በብሔራዊ ባንክ እየተካሄደ ያለው ማሻሻያ፣ የፋይናንስ ስርዓቱን ከዲጂታል እድገቶች ጋር ለማዘመንና ለማጣጣም ያለመ መሆኑንም አብራርተዋል።
አዲስ በፀደቀው የባንክ አዋጅ ላይ የግንዛቤ ክፍተቶች እንዳሉ በማንሳትም፣ ከምክር ቤቱ የተሰነዘሩ አንዳንድ ጥያቄዎችን ተችተዋል። አዲሱ አዋጅ ብሔራዊ ባንክ በቅርቡ ካደረገው ማሻሻያ ጋር በቀጥታ የተያያዘ እንዳልሆነም ገዥው ጠቁመዋል። ነገር ግን መሰል አዋጆች በተደጋጋሚ መተግበራቸው በባንክ ስራዎች ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ሊያሳድር እንደሚችል አስጠንቅቀዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ የተሻሻለ የባንክ ደንብ አለመኖሩን የገለጹት ገዢው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ በምክር ቤቱ የተነሱ ጥያቄዎች እንዲመለሱ ጠይቀዋል። የብሔራዊ ባንክ ማሻሻያዎች በዋናነት ከገንዘብ ፖሊሲ ማስተካከያዎች ጋር የተያያዙ መሆናቸውን በመጠቆምም፤ ምክር ቤቱ የእነዚህን ለውጦች ትክክለኛ ትርጓሜ እንዲያረጋግጥ አሳስበዋል።
የብሔራዊ ባንክ አፈጻጸምን ያወደሱት አቶ ማሞ ምሕረቱ፤ እርምጃዎቹ ከሌሎች የአፍሪካ ማዕከላዊ ባንኮች ጋር ሲነፃፀሩ የበለጠ ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል። ብሔራዊ ባንክ ኢኮኖሚውን በማረጋጋት ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ገልፀው፤ የባንኩን የሥራ አፈፃፀም “የሚመሰገን” ነው ሲሉ አድንቀውታል፡፡ የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ የሚፈቅደው ረቂቅ አዋጅ በሳምንቱ አጋማሽ ላይ በፓርላማ በአብላጫ ድምጽ መፅደቁ ይታወቃል።
አምስት የሚደርሱ የውጭ አገር ባንኮች የኢትዮጵያን የባንክ ዘርፍ ለመቀላቀል ፍላጎት ማሳየታቸው የተነገረ ሲሆን፤ ከእነዚህም ውስጥ የኬንያ ስታንዳርድ ባንክ፣ የኬንያ ሲቲ ባንክና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ባንክ ይገኙበታል። ባለፈው ዓመት ሀምሌ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው መተግበሩን ተከትሎ፣ በኢትዮጵያ፤ ፋይናንስና ባንክ ዘርፎች የፖሊሲ ማሻሻያዎች እየተደረጉ ሲሆን፤ ይሄም የውጭ ኢንቨስትመንትን እንደሚስብ ይጠበቃል። በተመሳሳይ የባንክ ሥራ ማሻሻያ አዋጅም በህዝብ ም/ቤት አባላት መፅደቁ ይታወቃል። በያዝነው ዓመት የዲጂታል ገንዘብ ዝውውር ከጥሬ ገንዘብም ልውውጥ በላቀ መጠን መከናወኑ የተገለፀ ሲሆን፤ የኤቲኤም ተጠቃሚዎች ቁጥር መጨመሩም ታውቋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ ኮሬ ዞን የነዳጅ ዋጋ ንረት እንደተከሰተ ተገለፀ። ነዋሪዎቹ ለአዲስ አድማስ እንደገለጹት፤ ከዋጋው መናር በተጨማሪ የአቅርቦት ችግር በመኖሩ ነዋሪው በትራንስፖርት እጥረት እየተንገላታ ነው ተብሏል።
ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድየኬሌ ከተማ ነዋሪ በሰጡት አስተያየት፤ የነዳጅ አቅርቦቱ መስተጓጎል ከጀመረ ስምንት ወራት እንዳስቆጠረ ተናግረዋል። “የቤንዚን ዕጥረቱ ከማሕበረሰቡ ኑሮ ጋር ‘ተሳስሯል’ ያሉት ነዋሪው፣ በከተማው የሞተር ሳይክል አከራዮች ስለሚበዙ እና የመብራት መቆራረጥ ስላለ፣ እንዲሁም በርካታ የጄኔሌተር ተጠቃሚ ስላለ የቤንዚን ዕጥረቱ ያሳረፈው ተጽዕኖ ቀላል አለመሆኑን አብራርተዋል።
“የቤንዚን አቅርቦቱ ሙሉ በሙሉ ባይቋረጥም፣ በነጋዴዎች የመሽሸግ ተግባር ይፈጸማል ተብሏል። አንድ ሊትር ቤንዚን ከ370 እስከ 400 ብር ይሸጣል ያሉት ነዋሪው፤ በተጨማሪም፣ በከተማይቱ ውስጥ ያለው የነዳጅ ማደያ አንድ ብቻ ነው። ይህም ከሌሎች ሁኔታዎች ጋር ተዳምሮ የዕለት ተለት ዕንቅስቃሴና በእጅጉ እንደሚያስተጓጉል ነዋሪው ተናግረዋል።
አብዛኛውን ጊዜ ቤንዚን እንደማይመጣና አልፎ አልፎ ከመጣም የነዳጅ ማደያው በኮንትሮባንድ ንግድ ለተሰማሩ ነጋዴዎች አሳልፎ እንደሚሰጥም ጠቅሰዋል።
በተጨማሪም በቴሌብር አማካይነት ክፍያ ፈጽመው ነዳጅ የሚያስቀዱ ተጠቃሚዎች እንደሌሉ የጠቆሙት ነዋሪው፣ ከሁሉም በላይ በከተማዋ ውስጥ አንድ የነዳጅ ማደያ ብቻ መኖሩ ተጠቃሚዎችን አማራጭ አልባ አድርጓቸዋል ተብሏል።
በኮሬ ዞን የመምህራን እና መንግስት ሰራተኞች ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማሕበር ስር የሚተዳደረው ይኸው የነዳጅ ማደያ የሚያቀርበው ቤንዚን የተደራሽነት መጠኑ የማሕበረሰቡን ፍላጎት የሚያሟላ አለመሆኑን አስረድተዋል፣ ነዋሪው። ከዚህም ባሻገር፣ የከተማዋ ማሕበረሰብ በከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ ጨምረው ተናግረዋል።
ነዋሪው በግላቸው የሞተር ሳይክል ማከራየት ስራ ላይ የተሰማሩ ሲሆኑ፣ ኬሌ ከተማ ውስጥ ሞተር ሳይክል በማከራየት ስራ የተሰማሩ ወጣቶች በነዳጅ እጥረቱ ሳቢያ የዕለት ጉርሳቸውን መሸፈን እንዳልቻሉ ተጠቁሟል። “ስራ ካቆምኩ ሁለት ወር እየሆነኝ ነው” የሚሉት እኚሁ ነዋሪ፣ የትራንሰፖርት አገልግሎት የሚሰጡ የባጃጅ ተሽከርካሪዎችም ስራ ማቆማቸውን ተናግረዋል።
የቤንዚን ስርጭት ላይ ቁጥጥር የሚያደርጉ የመንግስት አካላት እንደሌሉና “ከሕገ ከህገ-ወጥ” ነጋዴዎች ጋር ተባብረው እንደሚሰሩ ያነሱት ነዋሪው፣ ከነዋሪዎች ስለ ቤንዚን ጥያቄ ሲቀርብ “ጉዳዩን እየተከታተልን ነው፣ ምላሽ እንሰጣለን” ቢሉም፣ ሆኖም ግን ጉዳዩ ለችግሩ ዕልባት ሰጥተው እንደማያውቁ አመልክተዋል።
በኬሌ ከተማ የሞተር ሳይክል መለዋወጫ እያስመጡ በመሸጥ ሥራ ላይ እንደተሰማሩ የነገሩን ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አስተያየት ሰጪ በበኩላቸው፤ የተከሰተው የቤንዚን ዕጥረት የሚሸጧቸውን የመለዋወጫ ዕቃዎች ለማስመጣት እንቅፋት እንደሆነባቸው ተናግረዋል።
የዞኑ ባለስልጣናት የተፈጠረው ችግር ላይ ትኩረት አድርገው መፍትሔ ለመስጠት አለመቻላቸውን እኚሁ ነዋሪ ገልጸዋል። ሁኔታው በዚሁ ከቀጠለ፣ የሚፈጠረው ችግር እጅግ አስከፊ እየሆነ እንደሚመጣም አስረድተዋል።

 

“ብልፅግና ም/ቤቱን የግሉ መጠቀሚያ አድርጎታል”

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ከብልፅግና ጋር እየተሞዳሞደ ነው በሚል በተቃዋሚዎች ኮከስ ክስ ቀረበበት። ኮከሱ የጋራ ምክር ቤቱ በቅርቡ ባደረገው ጠቅላላ ጉባዔ አዲስ አመራር መምረጡን አጥብቆ ኮንኗል።
ኢሕአፓ፣ ኦፌኮ፣ ዎብን፣ ሕብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና ኦነግ የተካተቱበት የተቃዋሚ ፓርቲዎች ኮከስ ባለፈው ረቡዕ ታህሳስ 9 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ የጋራ ምክር ቤቱ የተቋቋመው በመሠረታዊ አገራዊ አጀንዳዎች ዙርያ በትብብርና በመወያየት የጋራ መድረክና አሰራር በማበጀት ለመንቀሳቀስ መሆኑን አመልክቷል። “ይሁንና ምክር ቤቱ ከተቋቋመበት የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን የማጠናከር ዓላማና ተልዕኮ በመውጣት የብልፅግና ፓርቲ ታዛዥ፣ ጉዳይ ፈጻሚና አስፈጻሚ እንዲሆን ከፍተኛ ጫና እየተደረገበት ነው” ሲል ኮከሱ ወቅሷል።
“ከዓላማው ውጪ እየተንቀሳቀሰ ነው” በሚል በተቃዋሚዎች ኮከስ የተነቀፈው የጋራ ምክር ቤቱ፤ ብልጽግና ፓርቲን ያለ ውድድር ሰይሞና ሌሎችን በምርጫ ስም አስቀምጦ አዲስ አመራር መምረጡንና ደንብ መቅረጹን ፓርቲዎቹ ተቃውመዋል።
“የፖለቲካ ድርጅቶች ሃሳብ መለዋወጫ እንዲሆን የመሰረቱትን የጋራ ምክር ቤት ብልጽግና ቀስ በቀስ በስልታዊውና በሚታወቀው የኢህአዴግ አካሄድና ዘዴዎች አሽመድምዶታል” ያለው የተቃዋሚዎች ኮከስ፤ “ይህ አካሄድ ከተጨባጭ የዘመነ ፖለቲካ አካሄድ ጋር ስለሚቃረን ምክር ቤቱ ወደተመሰረተለት ቃልኪዳን እንዲመለስ አጥብቀን እንጠይቃለን” ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ ገዢውን ፓርቲ ጨምሮ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች በተፈራረሙት የቃልኪዳን ሰነድ አማካይነት ከዓመታት በፊት መቋቋሙን ጠቅሰው ያስታወሱት የኢህአፓ ተቀዳሚ ሊቀመንበር መጋቢ ብሉይ አብርሃም ሃይማኖት፣ የተቋቋመበት ዋና ዓላማዎቹ በአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ማስፈንና በፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ የሚደርሱ ተጽዕኖዎችን መከላከል፣ እንዲሁም የፖለቲካ ምሕዳሩን ማስፋትና የተለያየ አመለካከት ያላቸው ፓርቲዎች ተቀራርበው በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ እንዲሰሩ ማስቻል መሆናቸውን ተናግረዋል። ነገር ግን “ብልጽግና ፓርቲ ምክር ቤቱን የግሉ መጠቀሚያ ማድረግ ጀመረ። እኛ ‘ሕገ ወጥ ነው’ ብለን ባልተገኘንበት ጉባዔ ላይ በአቋራጭ ብልጽግና ያለውድድር ስልጣን እንዲኖረው ተደረገ” ያሉት ፓርቲዎች፤ በሌላ በኩል የምክር ቤቱ ስራ አስፈጻሚ ውስጥ በየዓመቱ ምርጫ ይደረግ ነበር። ሆኖም ያለውድድርና ምርጫ የብልጽግና አባል የሆነ ማንኛውም ተወካይ በክልሎችም ሆነ በፌደራል ደረጃ መቀመጫ ‘ይኑረው’ የሚል ሕግ ጸደቀ” ብለዋል።
ይህ ሕግ የኮከሱ አባል ፓርቲዎችን እንደማይገዛ መጋቢ ብሉይ በማስታወቅ፣ በአዲሱ ሕግ መሰረት ለስራ አስፈጻሚው የሁለት ዓመት ተጨማሪ የስልጣን ዕድሜ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ከህዳር 7 እስከ 9 ቀን 2017 ዓ.ም. ዘ ሃብ በተሰኘው ሆቴል የተደረገው የጋራ ምክር ቤቱ ጠቅላላ ጉባዔ፣ ከስራ አስፈጻሚ አመራር ምርጫ ባሻገር ይኸው ሕግ የጸደቀበት እንደሆነና የኮከሱ አባል የሆኑ ፓርቲዎች እንደማይቀበሉት ጠቁመዋል።
“በአማራና ኦሮሚያ ክልል የሚካሄዱ ጦርነቶች እንዲቆሙ ጥሪ የሚያቀርብ መግለጫ ‘እናውጣ’ ብለን ለጋራ ምክር ቤቱ ብንማጸንም ሰሚ አላገኘንም” የሚሉት መጋቢ ብሉይ፣ “[የጋራ ምክር ቤቱ] ከእኛ ዕውቅና ውጪ መግለጫ እየሰጡ ነው” ሲሉ ተናግረዋል። በተጨማሪም፣ መጋቢ ብሉይ አብርሃም፣ በጋራ ምክር ቤቱ ውስጥ “ያሉ ችግሮችን” ለመቅረፍ የተደረገ ሙከራ እንደሌለና ከመነሻውም ምክር ቤቱ ከኮከሱ አባል ፓርቲዎች ጋር ለመነጋገር ፍላጎት እንዳላሳየ ተናግረዋል።
“የገዢው ፓርቲ አጃቢ ሆኖ መሄድ ተገቢ አይደለም። ምክር ቤቱ እንዲድን ጥረት እናደርጋለን። ነገር ግን ጥረታችን ካልተሳካ ለሕዝብ የሚወግን ጠንካራ ምክር ቤት እናቋቁማለን” ሲሉ መጋቢ ብሉይ አብርሃም አቋማቸውን አስታውቀዋል።

 

ዘነበች ታደሰ ማን ነች? ለምንስ ጭራ ቀረሽ የሚል ስያሜ ተሰጣት? ለጥበብ ምን አበረከተች? የሚሉ ጥያቄዎችን ሊመልስ የሚችል የአርቲስት ዘነበች ታደሰን ህይወት የሚዳስስ በፅሁፍና በምስል የተደራጀ መፅሐፍ በዶ/ር ጌታቸው ተድላ ተዘጋጅቶ ለአንባቢያን ሊቀርብ ነው።
ታህሳስ 12 2017 በሀገር ፍቅር ቴአትር የሚመረቀው ይህ መፅሀፍ 167 ገፆች ያሉት ነው።

ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት የመገናኛ ብዙሃን ሚና የላቀ መሆኑን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት ገለፀ። ምክር ቤቱ ከተለያዩ የሚዲያ ባለሞያዎችና የዩኒቨርስቲ ምሁራን ጋር “በሀገራዊ ምክክሩ የመገናኛ ብዙኃን ሚና ምን ይመስላል“ በሚለው ጉዳይ ላይ ምክክር አድርጓል።
መገናኛ ብዙሃን ታማኝ፣ ነፃና ገለልተኛ የሆነ ሙያዊ ሃላፊነት የሚስተናገድበት ተቋም መሆኑን ያነሱት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አማረ አረጋዊ፤ ኢትዮጵያ የጀመረችው ሀገራዊ ምክክር የተሳካና ውጤታማ እንዲሆን መገናኛ ብዙኃን ድርሻቸው የጎላ እንደሆነና ለዚህም በትጋት መስራት እንደሚገባ ገልጸል፡፡
ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያ ከገባችበት ችግር የምትወጣበት አይነተኛ መንገድ ነው ያሉት የሀገራዊ ምክክሩ ኮሚሽነር ተገኘ ወርቅ ጌቱ (ዶ/ር) ፤ ምክክሩ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች እየተሰራ እንዳለና በቀጣይም በአማራና በትግራይ ክልሎች ምክክሩን ለመጀመር የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡
በአማራ ክልል ሀገራዊ ምክክሩን ለመጀመር ከ1 ሺህ 700 በላይ ተባባሪ አካላትን አሰልጥኗልም ብለዋል። በሀገራዊ ምክክሩ ላይ መገናኛ ብዙኃን ላበረከቱት አስተዋፅኦ አመስግነው፣ ምክክሩ የተሳካ እንዲሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ የድርሻውን ማበርከት እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

ሲንቄ ባንክ፤ የሲንቄ ኢንቨስትመንት ባንክን ለማቋቋምና የድርጅት ስትራቴጂን፣ ተግባራዊ ስትራቴጂን እንዲሁም የሂደትና ዳግም የማወቀርያ ድርጅታዊ ዲዛይንን ለማዳበር የሚያግዝ የምክር አገልግሎት ለማግኘት ከዴሎይት ጋር ስምምነት ተፈራረመ።
የፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓ.ም በሒልተን አዲስ ሆቴል መካሄዱ ታውቋል፡፡
የስምምነት ውሉን የተፈራረሙት የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ነዋይ መገርሳና የአጋር ዴሎይት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ አማካሪ ድርጅት መሪ የሆኑት አቶ ቴዎድሮስ ሲሳይ ሲሆኑ፤ በሥነስርዓቱ ላይ የባንኩ ከፍተኛ አመራር፣ እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ የሰብአዊ ካፒታል ሊድ ዳይሬክተር የሆኑት የዴሎይት ማኔጅመንት ዶ/ር ፖል ኦካቴጅ ተገኝተዋል፡፡
Page 10 of 753