Administrator

Administrator

• በዓመት 3 ሚ. ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለማምረት ያስችላል
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ በኢትዮጵያ በዓመት እስከ 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለማምረት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ አደረጉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መረጃ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግና በዳንጎቴ ግሩፕ መካከል የማዳበሪያ ማምረቻ ኮምፕሌክስ የድርሻ ስምምነት ፈርመናል ብለዋል።
ፕሮጀክቱ 2.5 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት የሚፈስበት መሆኑን የገለፁት ጠ/ሚኒስትሩ፤ በአመት እስከ ሶስት ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ የሚያመርት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ይኽም ኢትዮጵያን ከዓለም ግንባር ቀደም አምራቾች አንዷ ያደርጋታል ብለዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ለዘመናት ለተፈተኑት ገበሬዎቻችን አስተማማኝ የማዳበሪያ አቅርቦት ያረጋግጣል ሲሉም ጠ/ሚኒስትሩ አክለዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
ነገሩ የተከሰተው ባለፈው ሳምንት በምስራቅ ሀራርጌ ጉርሱም ወረዳ ጎባ ቀበሌ ነው፡፡ አቶ ሙስጠፋ ረሺድ እንደ ሁልጊዜው በሰርክ ተግባራቸው ላይ ውለው ደክሟቸው ከልጆቻቸውና ባለቤታቸው ጋር ቤታቸው ውስጥ ነበሩ፡፡
የሁለት ታዳጊ ልጆች አባት የሆኑት ሙስጠፋ፣ የገጠማቸውን ለዶይቼ ቬለ እንዲህ ሲሉ ያስረዳሉ፤
“ያጋጠመኝ ነገር ያው ፈጣሪ ኑር ካለ ያኖርሃል ነው እንጂ፣ ህይወትን የሚያስቀጥል ነገር እንኳ አልነበረም፡፡ አስፈሪው የዱር እንስሳ ነብር ከምሽቱ በግምት 1፡30 አካባቢ ከቤተሰቦቼ ጋር ቤት ውስጥ እያለን ነው ከተፍ ብሎ ወደ ቤት ዘልቆ የገባብን፡፡ ምንም ዝግጅት አላደረግንም፡፡ ስታየው የሚስፈራ ቁጡ የዱር እንስሳ ነው፡፡ በዚያ ላይ በእርሻ ማሳ ውስጥ ስለፋ ነው የዋልኩኝ፡፡ ልክ እግሮቼን ታጥቤ አረፍ ስል ነው ይህ የሆነው፡፡ በጀርባዬ የወንድሜ መኖሪያ ቤት አለ፡፡ ነብሩ ዘለል አለና ከፍ ያለች ቤት ውስጥ ባለች አልጋ ነገር ላይ ቁጭ አለ፡፡ ነብር ልጆች ያጠቃል ስለሚባል ልጆቼን እንዳያጠቃብኝ ስጋት ገባኝ፡፡ እናም የሆነ ነገር ማድረግ አለብኝ አልኩ፡፡ ያገኘሁትን ዱላ ነገር አንስቼ ላስወጣው ስል ግን ዘሎ ተከመረብኝ” ብለዋል፡፡
በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ከገባው ነብር ጋር ትግል የገጠሙት አባት ሕይወታቸው በተዓምር ተርፏል።
ልጆቻቸውንና ባለቤታቸውን ቢያተርፉም፣ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ቦታ ከሚሰጣቸው ሊቃውንት አንዱ የሆኑት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ 600ኛ ዓመት የዕረፍት መታሰቢያ ለአንድ ዓመት ሊዘከር ነው። ይህን ምክንያት በማድረግ ለቀጣይ አንድ ዓመት የሚቆይ ልዩ የፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በትናንትናው ዕለት ተካሂዷል።
የፕሮጀክቱ ማስጀመሪያ ፕሮግራም በአዲስ አበባ፣ ዮድ አቢሲንያ የባሕል ምግብ አዳራሽ ውስጥ የተካሄደ ሲሆን፣ በዝግጅቱ ላይ የተለያዩ ምሁራንና መምሕራን ተገኝተዋል። መምሕር ዳንኤል ገ/ስላሴ ስለ መጽሐፈ ምስጢር፣ መጋቢ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ (ዶ/ር) ስለ መጽሐፈ ሰዓታት እና መምሕር ዲያቆን ዘላለም ታዬ ደግሞ ስለ ኆኅተ ብርሃን የሊቁ ድርሳናት አጭር የዳሰሳ ጽሑፍ አቅርበዋል።
ይህ ፕሮጀክት የሊቁን ሕይወት፣ ትምሕርቶች እና በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ያላቸውን አስተዋጽዖ ዓመቱን በሙሉ በስፋት ለማስታወስ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ማኀበረ ጽዮን ጠቅላላ ማሕበር አመራሮች በመርሐግብሩ ላይ ገልጸዋል። እንዲሁም ፕሮጀክቱ የአባ ጊዮርጊስን ማንነት፣ በስማቸው የተሰየመውን የጋስጫ ገዳማቸውን ታሪክ፣ የሊቁን አበርክቶ እና የወደፊት ስትራቴጂያዊ ዕቅዶችን በተለያዩ ዝግጅቶችና ፕሮግራሞች በአገር ውስጥና በውጭ አገራት ከተሞች ዓመቱን በሙሉ ለማስተዋወቅ መታቀዱን ተጠቅሷል።
“ዓምደ ሐይማኖት”፣ “ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ” እና “ዳግማዊው ዮሐንስ አፈወርቅ” በሚሉ ስያሜዎች የሚታወቁት አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣ በ1357 ዓ.ም. በቀድሞው ወሎ ክፍለ አገር፣ "ሸግላ" በተባለ ቦታ እንደተወለዱ ይነገራል።
 
 
 
 
 
 
 
 
 
See insights and ads
 
Boost post
 
All reactions:
99
 
 
በጌዴኦ ዞን ራጴ ወረዳ በጫራቃ እና በሀሮ ቀበሌ ትላንት ከምሽቱ 5 ሰዓት አከባቢ የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በደረሰ የመሬት ናዳ እስካሁን የ9 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የጌዴኦ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
‎የጌዴኦ ዞን ፖሊስ ዋና አዛዥ ኢንስፔክተር ብሩ ማርቆስ ለኢቢሲ እንደገለጹት፤ ትላንት ማምሻውን በረዶ ቀላቅሎ የጣለው ከባድ ዝናብ ለአደጋው ምክንያት ሆኗል።
‎በመሬት ናዳው ከሞቱ 9 ሰዎች መካከል 6 ወንዶች ሲሆኑ የተቀሩት ሴቶች መሆናቸውንም አመላክተዋል።
አካባቢው ለናዳ አደጋ ተጋላጭ በመሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባልም ተብሏል።
ኡጋንዳ በቅርቡ ከአዲስ የነዳጅ ማውጫ ሥፍራ ነዳጅ ማምረት እንደምትጀምር አስታወቀች፡፡
ስፑትኒክ እንደዘገበው፤ በሀገሪቱ የሚገኘው የኪንግፊሸር የነዳጅ ፕሮጀክት፣ ከተያዘለት የጊዜ ገደብ አስቀድሞ 95 በመቶ ሥራው ተጠናቋል።
የፕሮጀክቱ የሥራ ኃላፊ ክኖክ ኡጋንዳ እንደገለጡት፤ 15 የነዳጅ ጉድጓዶች ለማምረት ዝግጁ ሆነዋል።
የቻይናው ኩባንያ የኡጋንዳ መንግሥትን ፈቃድ እንዳገኘ ምርት ለመጀመር ዝግጁ እንደሆነና ፍቃዱም በ2018 ዓ.ም አጋማሽ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሪፖርቶች ጠቁመዋል፡፡
ቦታው በቀን 40 ሺህ በርሜል አካባቢ የማምረት አቅም ያለው ሲሆን፤ ነዳጁም ወደ ታንዛኒያ ሊጓጓዝ ይችላል ተብሏል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
May be an image of oil refinery
 
 
 
 
 
ኒጀር ዜጎቿ በአውሮፓ ሀገራት ኤምባሲዎች ቪዛ ለማግኘት ለሚደርስባቸው ውጣ ውረድ በሰጠችው አፀፋዊ ምላሽ፤ የአውሮፓ ዜጎች የሀገሪቱን ቪዛ ማግኘት የሚችሉባቸው ቦታዎችን ገድባለች።
የኒጀር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባካሪ ያኡ ሳንጋሬ በሰጡት መግለጫ፤ "ከዚህ በኋላ የጣሊያን፣ የኔዘርላንድ፣ የጀርመን፣ የቤልጂየምና የዩናይትድ ኪንግደም ሀገራት ዜጎች ወደ ኒጀር ለመግባት ቪዛ ማግኘት የሚችሉት በጄኔቫ፣ አንካራና ሞስኮ በሚገኙ የኒጀር ኤምባሲዎች ብቻ ነው" ብለዋል።
ሳንጋሬ አክለውም፤ ዲፕሎማቶችና የአገልግሎት ፓስፖርት የያዙ ግለሰቦች በብራሰልስ ከሚገኘው የኒጀር ኤምባሲ ቪዛ ማግኘት እንደሚችሉ ገልፀዋል።
ውሳኔው ኒጀር ዜጎቼ የአውሮፓ ቪዛ ለማግኘት ወደ ጎረቤት ሀገራት ለምን መጓዝ ይጠበቅባቸዋል በማለት ቅሬታ ማቅረቧን ተከትሎ የመጣ ነው። የአውሮፓ ህብረት ኤምባሲዎች በኒያሜ ባሉ ቢሮዎቻቸው ውስጥ ቪዛ እንዲሰጡ የቀረበው ጥያቄም መልስ ሳያገኝ መቅረቱን ስፑትኒክ ዘግቧል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
 
 
 
 
 
 
 
 
 
 
በቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ የተመራ የልዑካን ቡድን፣ በቼክ ሪፐብሊክ የሚገኘውን ኦምኒፖል የአውሮፕላን አምራች ኩባንያን ጎበኘ።
ኩባንያው በአቪዬሽን ዘርፉ ከ80 ዓመት በላይ ልምድ እንዳለው ተገልጿል።
በኦምኒፖል አውሮፕላን አምራች ኩባንያ በተደረገው ጉብኝት ለቱሪዝም መዳረሻዎች የሚሆኑና ቱሪስቶችን ማጓጓዝ የሚያስችሉ አነስተኛ አውሮፕላኖችን መመልከታቸውንም ሚኒስትሯ ገልፀዋል።
አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለማስተዋወቅና የቱሪዝም መሰረተ ልማትን ለማሟላት ያለመ ምክክርና ጉብኝት መካሄዱንም ተናግረዋል።
የአውሮፕላን አምራች ኩባንያው አመራሮች የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ለመደገፍ ፍላጎት እንዳላቸው ተናግረዋል ሲል የቱሪዝም ሚኒስቴር ባወጣው መረጃ ጠቁሟል፡፡
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

የእንግሊዝ እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር የአመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማት ስነ ስርአት በአሁኑ ስአት በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡

ሙሀመድ ሳላ፣ ደክለን ራይስ፣ ቡሩኖ ፈርናዴዝ፣ አሌክሳንደር ይሳቅ፣ አሌክሲስ ማክ አሊስተር እና ኮል ፓልመር የመጨረሻ ዕጩዎች እንደሆኑም ይታወቃል፡፡

በሴቶችም፣ በወጣቶችም ዘርፍ አሸናፊዎቹ የሚለዩ ይሆናል፡፡

መንግስት በአዲሱ የደሞዝ ጭማሪ ምክንያት ለ160 ቢለየን ብር ተጨማሪ ወጭ እንደሚዳረግ ገልጿል። እስኪ የጭማሪውን ፋይዳ ለመረዳት ቁጥሮችን በአንጻራዊ ስሌት እናጢናቸው።
ቋሚ ደሞዝተኛው ገንዘቡ ኪሱ ከመግባቱ በፊት በገቢ ግብር ምክንያት ዝቅተኛው ተከፋይ 15% ከፍተኛው ደግሞ 35% ይቆረጥበታል። ዝርዝሩ ውስጥ መግባት ስለሚያዳግት አማካዩን ቁጥር እንወሰድ።
አማካዩ (15+35)/2 = 25% ይሆናል። ወደፊት እድሜውና ጤናው ከፈቀደለት የጡረታ ተከፋይ የሚያደርገው ቢሆንም ዛሬ ላይ ለጡረታ 7% ከደሞዙ በቀጥታ ይቆረጥበታል። 25%+7% = 32% ይሆናል።
160,000,000,000*0.32= 51,200,000,000 ይሆናል። ይህ ማለት ሃምሳ አንድ ቢሊየን 200 ሚሊየን ብር የደሞዝ ጭማሪው ተቀጣሪው እጁ ከመድረሱ በፊት ወደ መንግስት ካዝና ይመለሳል። በደሞዝ መልክ የሚከፋፉለው ቀሪ 108,800,000,000 ብር ይሆናል።
ደሞዙ እጁ ላይ ከገባ በኋላ ደግሞ በሚሸምተው ቁሳቁስና በሚገዛው አገልግሎት ላይ 15% ቫት ይከፍላል። 108,800,000,000 *0.15 = 16,320,000,000 ይሆናል።
ይህ ማለት ደግሞ ከ160 ቢሊየን ብር ጭማሪ ውስጥ ደሞዝተኛውን ሳያገለግል በገቢ ግብር፣ በጡረታና በቫት ብቻ ወደ መንግስት ካዝና ተመልሶ የሚገባው ብር 67,520,000,000 ሲሆን ጭማሪው ደግሞ 92,480,000,000 ብር ይሆናል።
በመቀጠል ቀሪዎቹን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ የግብር ዓይነቶች እናንተው አስሏቸው። ፕሮፐርቲ ታክስ (1%)፣ ተርን ኦቨር ታክስ(2%)፣ ትራንዛክሽን ታክስ (0.1% እስከ 1.5%) .... ግሽበቱንና ሌላውን ቀጣይ ቅንስናሻ በሕሊናችሁ አክሉበት
ከዚህ ሁሉ ቅንስናሽ በኋላ የሚገኘው የደሞዝ ጭማሪ ኢሚንት ቢሆንም አይጠቅምም ማለት በእግሩ ተጓጉዞ፣ በቀን አንዴ ቀምሶ ከሚያተርፋት "ደሞዙ" ላይ በየእለቱ ለልጆቹ ደረቅ ዳቦ የማቅረብ ግዴታ የተጣለባትን ቋሚ ደሞዝተኛ ፈተናና መከራ በቅጡና በልኩ አለመረዳት ይሆናል።
ተወደደም ተጠላ፣ አነሰም ተከመረ ጭማሪው ጎዳን ለመውጣት እየተንደረደረ የነበረውን ቋሚ የመንግስት ደሞዝተኛ እንደሚደጉምና አንድ ቀዳዳ እንደሚደፍንለት ጥርጥር የለኝም። ደሞዝ መቼም በቂ ሆኖ አያውቅም። በቂ ካልሆነ ደግሞ ጭማሪው ይቅር ለማለት ቋሚ ደሞዝተኛውን እሱና ቤተሰቡን ከነ መከራው ሆኖ መገኘትን ይጠይቃል።
ሙሼ ሰሙ-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…