Administrator

Administrator

Saturday, 02 May 2015 12:35

የሰዓሊያን ጥግ

  ፎቶግራፍን አታነሳውም፤ ትፈጥረዋለህ እንጂ፡፡         ቶማስ ሜርቶን
ለማየት ስል ዓይኖቼን እጨፍናለሁ፡፡
ፖል ጋውጉይን
እንደ ስሜቶች ሁሉ ቀለማትም የህይወት ነፀብራቅ ናቸው፡፡     ጃኒሴ ግሊናዌይ
ቀለማትና እኔ አንድ ነን፡፡ ሰዓሊ ነኝ፡፡
ፖል ክሊ
ሰዓሊ ጥሩ ነገር የሚሰራው እየሰራ ያለውን የማያውቅ ከሆነ ብቻ ነው፡፡
ኤድጋር ዴጋስ
የሰዓሊ ሥራ ሁልጊዜም ምስጢሩን ጥልቅ ማድረግ ነው፡፡
ፍራንሲስ ቤከን
ለመሳል ዓይኖችህን መጨፈንና ማዜም አለብህ፡፡
ፓብሎ ፒካሶ
በስዕልና በግጥም ሰስብዕና ሁሉም ነገር ነው፡
ገተ
ማንኛውም ጅል ስዕል መስራት ይችላል፤ ለመሸጥ ግን ብልህ ሰው ይፈልጋል፡፡
ሳሙኤል በትለር
መጀመሪያ ደንስ፤ በኋላ አስብ፡፡
ሳሙኤል ቤኬት
ነገሮችን የምስለው እንደማያቸው ሳይሆን እንደማስባቸው ነው፡፡     ፓብሎ ፒካሶ
ቀለማት የተፈጥሮ ፈገግታዎች ናቸው፡፡
ሊይግ ሃንት
ሰው ሁሉ ስዕልን ለመረዳት ይፈልጋል፡፡ ለምንድን ነው የአዕዋፋትን ዝማሬ የመረዳት ሙከራ የሌለው?
ፓብሎ ፒካሶ
የራሴ ስዕሎች ባለቤት አይደለሁም፤ ምክንያቱም የፒካሶ ኦሪጂናል ስዕል ብዙ ሺ ዶላሮች ያወጣል ይሄ ከአቅሜ በላይ የሆነ ቅንጦት ነው፡፡
ፓብሎ ፒካሶ

Saturday, 02 May 2015 12:22

የየአገሩ አባባል

ጥበብ አልባ ዕውቀት በአሸዋ ላይ እንዳለ ውሃ ነው፡፡
የጊኒያውያን አባባል
ሞኝ ያወራል፤ ብልህ ያደምጣል፡፡
የኢትዮጵያውያን አባባል
ጥበብ በአንድ ጀንበር አይመጣም፡፡
የሶማሊያውን አባባል
በቀውስ ሰዓት ብልህ ድልድይ ሲገነባ፣ ሞኝ ግድብ ይገነባል፡፡
የናይጄሪያውያን አባባል
በኩራት ከተሞላህ ለጥበብ ቦታ የለህም፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
ብልህ ሰው ሁልጊዜ መላ አያጣም፡፡
የታንዛንያውያን አባባል
ማንም ብልህ ሆኖ አልተወለደም፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
ትልቅ ወንበር ንጉስ አያደርግም፡፡
የሱዳናውያን አባባል
የአንበጣዎች ጠብ ለቁራ ፌሽታው ነው፡፡
የሌሴቶ አባባል
ደጋግሞ በመሞከር ጦጣ ከዛፍ መዝለል ትማራለች፡፡
የቡጋንዳ አባባል
ምክር እንግዳ ነው፤ የሚቀበለው ካገኘ ሌቱን ያድራል፡፡ ያለበለዚያ የዚያኑ ዕለት ይመለሰል፡፡
የማላጋሲ አባባል
መጓዝ መማር ነው፡፡
የኬንያውያን አባባል
ባለሙያዎች ባሉበት የተማሪዎች እጥረት አይኖርም፡፡
የስዋሂሊ አባባል
ወተትና ማር ቀለማቸው ይለያያል፤ ነገር ግን አንድ ቤት ተጋርተው በሰላም  ይኖራሉ፡፡
የአፍሪካውያን አባባል
መግባባት ሳይኖር ሰላም ሊኖር አይችልም፡፡
የሴኔጋሎች አባባል
እየመራሁ ነው ብሎ የሚያስብና ተከታይ የሌለው ሰው የእግር ጉዞ እያደረገ ነው፡፡
የማላዊያኖች አባባል

 በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (ኢቢኤስ) ቴሌቪዥን “የጆርዳና ኩሽና ሾው”    አዘጋጅ ጆርዳና ከብዶም የተፃፈው “የጆርዳና የምግብ አዘገጃጀት” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀርቦ እየተነበበ ይገኛል፡፡ መፅሐፉ ከመቶ በላይ የውጭ ምግቦች አዘገጃጀትን የያዘ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን ከተለመደው የአመጋገብ ስርዓታቸው ወጣ ብለው እንደ ፓስታ፣ ፒዛ ያሉ የውጭ ምግቦችን በኩሽናቸው በቀላሉ አዘጋጅተው መመገብ እንዲችሉ ያግዛል ተብሏል፡፡ በኢቢኤስ ቲቪ “ጆርዳና ኩሽና ሾው” እውቅናን ያተረፈችው ባለሙያዋ፤ቦሌ ሩዋንዳ ኤምባሲ አካባቢ “ጆርዳናስ ኪችን ሬስቶራንት” የተሰኘ ምግብ ቤት ከፍታ የውጭ አገር ምግቦችን እያሰናዳች እንደምትሸጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡

 በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ሰርቪስ (ኢቢኤስ) ቴሌቪዥን “የጆርዳና ኩሽና ሾው”    አዘጋጅ ጆርዳና ከብዶም የተፃፈው “የጆርዳና የምግብ አዘገጃጀት” የተሰኘ መፅሀፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀርቦ እየተነበበ ይገኛል፡፡ መፅሐፉ ከመቶ በላይ የውጭ ምግቦች አዘገጃጀትን የያዘ ሲሆን ኢትዮጵያዊያን ከተለመደው የአመጋገብ ስርዓታቸው ወጣ ብለው እንደ ፓስታ፣ ፒዛ ያሉ የውጭ ምግቦችን በኩሽናቸው በቀላሉ አዘጋጅተው መመገብ እንዲችሉ ያግዛል ተብሏል፡፡ በኢቢኤስ ቲቪ “ጆርዳና ኩሽና ሾው” እውቅናን ያተረፈችው ባለሙያዋ፤ቦሌ ሩዋንዳ ኤምባሲ አካባቢ “ጆርዳናስ ኪችን ሬስቶራንት” የተሰኘ ምግብ ቤት ከፍታ የውጭ አገር ምግቦችን እያሰናዳች እንደምትሸጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ማልድ የትምህርት ድጋፍ ኃ.የተ.የግ.ማ ባቀራረቡ የተለየ የልጆችን የንባብን ባህል የሚያዳብር፣ ከመጽሐፍ ጋር የተያያዘ የወላጆች ቀን “Book and fun Kids day” /የህፃናት የንባብና የትምህርታዊ ጨዋታ ቀን/ የፊታችን ማክሰኞ በትሮፒካል ጋርደን መናፈሻ ከ4-11 ሰዓት ድረስ ማዘጋጀቱን ገለፁ፡፡
ከ4-14 ዓመት ላሉ ልጆች በተዘጋጀው በዚህ የልጆች ቀን፤ ወላጆች አስተማሪዎች እንዲሁም ትላልቆች ለልጆች መጽሐፍት ያነባሉ፡፡ ጸሐፊያን በዚሁ ቀን መጽሐፍ የማሳተምን ሂደት ለልጆች ያስረዳሉ፣ የተለያዩ ጨዋታዎችም ይኖራሉ፡፡ ማልድ በ21ኛው ክ/ዘመን ልጆች ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ወላጆች ልጆቻቸውን እንዴት ማሳደግ እንደሚገባቸው ይመክራል ተብሏል፡፡
ማልድ የትምህርት ድጋፍ ሰጪ አስተማሪዎችን በማሰልጠን፣ እንዲሁም ልጆችን ለክፍለዘመኑ ብቁ እንዲሆኑ የሚያግዙ በጥበብና በፈጠራ የተሞሉ ስልጠናዎችን በመስጠት ይታወቃል፡፡

 የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት ለሳምንታት በየዕለቱ መክረዋል

   ለጊዜው ማንነታቸው በውል ያልታወቀ የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን ኢሜይል በህገ-ወጥ መንገድ ሰብረው በመግባት፣ መረጃዎችን ማግኘት እንደቻሉ መረጋገጡን ስካይ ኒውስ ባለፈው ሰኞ ዘገበ፡፡
የዋይትሃውስ የደህንነት ሃላፊዎች ቻይናውያን አልያም ሩስያውያን ሳይሆኑ ሲሉ የጠረጠሯቸው እነዚህ የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች፣ የይለፍ ቁልፉን ሰብረው በመግባት ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለሌሎች ሰዎችና ድርጅቶች የላኳቸውንና ከሌሎች የተላኩላቸውን የኢሜል መልእክቶች ማግኜት መቻላቸው ተረጋግጧል፡፡ድርጊቱ የተፈጸመው ከሳምንታት በፊት ቢሆንም፣ የዋይት ሃውስ ባለስልጣናት ጉዳዩን ሸፋፍነውት እንደቆዩ የጠቆመው ዘገባው፣የአጭበርባሪዎቹ ጉዳይ አሳሳቢ መሆኑን የሚያመለክተው ባለስልጣናቱ ላለፉት ሳምንታት በየዕለቱ እየተሰበሰቡ በጉዳዩ ዙሪያ ሲመክሩ መቆየታቸው ነው ብሏል ዘገባው፡
ሩስያውያን የኢንተርኔት አጭበርባሪዎች የኦባማን የኢሜል መልዕክቶች ለማግኘት የቻሉት፣ ባለፈው አመት በዋይት ሃውስ የሴኪውሪቲ ሲስተም ላይ በደረሰው ቀውስ ያገኙትን ክፍተት በመጠቀም ነው ተብሎ እንደሚገመት የገለጸው ዘገባው፣ ይሄም ሆኖ ግን አጭበርባሪዎቹ ከፍተኛ ጥበቃ የሚደረግለትን የኦባማ  የብላክቤሪ ስልክ መልዕክቶች ማግኘት እንዳልቻሉ አክሎ ገልጧል፡፡

- ዋና ዋናዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫው አልተሳተፉም
- ምዕራባውያን አገራት ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ አይደለም ብለዋል

 ዋና ዋናዎቹ የሱዳን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ነጻና ፍትሃዊ አይሆንም በሚል ራሳቸውን ባገለሉበት የአገሪቱ ምርጫ የተወዳደሩት ፕሬዚዳንት ኡመር ሃሰን አልበሽር፤ 94.5 በመቶ ድምጽ በማግኘት በቀጣይም አገሪቱን በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ መመረጣቸውን ቢቢሲ ዘገበ።የአገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ሃላፊ ሙክታር አል አሳም ባለፈው ሰኞ ከካርቱም በሰጡት መግለጫ፣ ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲን በመወከል ለፕሬዚዳንትነት የተወዳደሩት አልበሽር፤ ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸውን ያስታወቁ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በበኩሉ፤ ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡት 13.3 ሚሊዮን ዜጎች ውስጥ ድምጽ የሰጡት አንድ ሶስተኛ ያህሉ ብቻ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ አልበሽር በዘንድሮው የሱዳን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይህ ነው የሚባል ፉክክር እንዳልገጠማቸው የዘገበው ዘጋርዲያን በበኩሉ፣ ከተፎካካሪዎች መካከል የተሻለ ድምጽ ያገኙት ፌደራል ትሩዝ ፓርቲን ወክለው የተወዳደሩት ፋደል አልሳይድ ሹያብ መሆናቸውንና ያገኙት ድምጽም 1.43 በመቶ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።ከሚያዝያ 5 ቀን ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በመላ አገሪቱ በተቋቋሙ 11 ሺህ የድምጽ ጣቢያዎች በተከናወነው የድምጽ አሰጣጥ ስነስርአት ላይ ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡት ውስጥ ሁለት ሶስተኛው ድምጽ አለመስጠታቸውንና ለፕሬዚዳንታዊ ምርጫው በተፎካካሪነት የቀረቡት 15 እምብዛም እውቅና የሌላቸው ዕጩ ተወዳዳሪዎች ብቻ እንደነበሩም አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ አሜሪካ፣ እንግሊዝና ኖርዌይን ጨምሮ በርካታ ምዕራባውያን አገራት፣ ላለፉት 25 አመታት ሱዳንን በፕሬዚዳንትነት የመሩት አልበሽር፤ በከፍተኛ ድምጽ ያሸነፉበትንና ባለፈው ሰኞ የተከናወነውን የአገሪቱ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ነጻና ፍትሃዊ አይደለም፣ እውቅና አንሰጠውም ሲሉ የተቹት ሲሆን፣ የቻይናው ፕሬዚደንት ዢ ጂፒንግ በበኩላቸው፤ ለአልበሽር የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት ልከዋል፡፡
ስቲስ ኤንድ ኢኳሊቲ ሙቭመንት የተባለው የአገሪቱ አማጺ ቡድን ባለፈው እሁድ በደቡብ ዳርፉር አካባቢ በሱዳን መንግስት ጦር ላይ በከፈተው ወታደራዊ ጥቃት የጦር ካምፕ ማውደሙንና የጦር መሳሪያዎችን መማረኩን ያስታወቀ ሲሆን፣ የአገሪቱ የጦር ሃይል በበኩሉ አማጽያኑ በሚንቀሳቀሱበት አካባቢ ባደረገው ድብደባ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱን አስታውቋል፡፡ በአየር ድብደባው 16 ሲቪል ዜጎች መሞታቸውንና ከ11 በላይ የሚሆኑ ደግሞ መቁሰላቸውን የዘገበው አይቢታይምስ ነው፡፡
በዳርፉር ግጭት የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል በሚል በአለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ የቀረበባቸውና የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው የ71 አመቱ አልበሽር፣ ድርጊቱን አልፈጸምኩም ሲሉ ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን ዘገባው ጨምሮ አስታውሷል፡
ፕሬዚዳንት አልበሽር እ.ኤ.አ በ1989 በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከያዙበት ጊዜ አንስቶ አገሪቱን እየመሩ ሲሆን ሱዳንን ለረጅም ጊዜ በመምራት ቀዳሚው ሰው እንደሆኑ ይታወቃል፡፡

ባለፈው ቅዳሜ በኔፓል በተከሰተውና በሬክተር ስኬል 7.8 በተመዘገበው አሰቃቂ የርዕደ-መሬት አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ5ሺህ በላይ መድረሱ መረጋገጡን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
በርዕደ-መሬቱ የተጎዱ ዜጎችን የማፈላለጉና እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎችን የመድረሱ እንቅስቃሴ በአስቸጋሪ የአየር ንብረት ሳቢያ አዳጋች ሆኖ የቀጠለ ሲሆን እስካለፈው ረቡዕ ድረስ ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ5ሺህ በላይ መድረሱን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ በአደጋው ከሞቱት በተጨማሪ ከ10ሺህ በላይ ሰዎችም የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን፣ ፍለጋው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የሟቾችም ሆነ የቁስለኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር ተገምቷል፡፡  
ኔፓልን መልሶ ለማቋቋም ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ያስፈልጋል ተብሎ እንደሚገመት ያስታወቀው ዘገባው፣ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት በበኩሉ፤ በአደጋው የደረሰው ጥፋት እስከ 10 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት መግለጹን አስታውቋል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ከሰዓት በኋላ ላንግታንግ በተባለችው የኔፓል አካባቢ በደረሱ ሁለት የመሬት መንሸራተት አደጋዎች፣ ከ200 በላይ ሰዎች የደረሱበት እንደጠፋም ዘገባው ጠቁሟል፡፡
የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሱሺል ኮይራላ በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ ዜጎችን ለመዘከር ባለፈው ማክሰኞ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ብሄራዊ ሃዘን ያወጁ ሲሆን ባለፉት አስር አመታት በርዕደ-መሬት ሳቢያ ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉ ዜጎች ቁጥር ከ10 ሺህ በላይ እንደሚደርስም አስታውቀዋል፡፡
በአደጋው የተጎዱ ዜጎች ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የድረሱልኝ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኙ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በሂሊኮፕተር የታገዘ እንቅስቃሴ እየተደረገ ቢገኝም፣ ከፍተኛ ዝናብና ውሽንፍር ከመኖሩና ከቦታዎቹ ተራራማነት ጋር በተያያዘ፣ በከፋ ሁኔታ በተጎዱ አካባቢዎች ፈጥኖ ለመድረስ አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱንም ገልጸዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የቅዳሜው የኔፓል ርዕደ-መሬት ስምንት ሚሊዮን ያህል ሰዎችን ተጠቂ እንዳደረገ ያስታወቀ ሲሆን፣ ለአስቸኳይ የአደጋ ጊዜ እርዳታ የሚውል 15 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
የተመድ ቃል አቀባይ ፋራህ ሃቅ እንዳሉት፤ የገንዘብ ድጋፉ ተጎጂዎችን ለመታደግ በመስራት ላይ የሚገኙ የሰብዓዊ ተቋማትን እንቅስቃሴ ለማሳደግና ለተጎጂዎቹ የመጠለያ፣ የውሃ፣ የመድሃኒትና የሌሎች አገልግሎቶች አቅርቦቶችን ለማሟላት የሚውል ነው።
ህንድ፣ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ማሌዢያ፣ ፓኪስታን እና እስራኤል ተጎጂዎችን ለመርዳት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ አውሮፕላኖችን ወደ ኔፓል የላኩ ሲሆን አሜሪካ በበኩሏ ለፈጥኖ ደራሽ እርዳታ የሚውል 10 ሚሊዮን ዶላር ለመለገስ ቃል ከመግባቷ በተጨማሪ የእርዳታ ድርጅቶቿን በአደጋው የተጎዱትን ዜጎች እንዲረዱ ወደ ኔፓል ልካለች፡፡

- ዋና ዋናዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫው አልተሳተፉም
- ምዕራባውያን አገራት ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ አይደለም ብለዋል

 ዋና ዋናዎቹ የሱዳን ተቃዋሚ ፓርቲዎች ነጻና ፍትሃዊ አይሆንም በሚል ራሳቸውን ባገለሉበት የአገሪቱ ምርጫ የተወዳደሩት ፕሬዚዳንት ኡመር ሃሰን አልበሽር፤ 94.5 በመቶ ድምጽ በማግኘት በቀጣይም አገሪቱን በፕሬዚዳንትነት እንዲመሩ መመረጣቸውን ቢቢሲ ዘገበ።የአገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን ሃላፊ ሙክታር አል አሳም ባለፈው ሰኞ ከካርቱም በሰጡት መግለጫ፣ ናሽናል ኮንግረስ ፓርቲን በመወከል ለፕሬዚዳንትነት የተወዳደሩት አልበሽር፤ ከ5 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸውን ያስታወቁ ሲሆን የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን በበኩሉ፤ ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡት 13.3 ሚሊዮን ዜጎች ውስጥ ድምጽ የሰጡት አንድ ሶስተኛ ያህሉ ብቻ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ አልበሽር በዘንድሮው የሱዳን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይህ ነው የሚባል ፉክክር እንዳልገጠማቸው የዘገበው ዘጋርዲያን በበኩሉ፣ ከተፎካካሪዎች መካከል የተሻለ ድምጽ ያገኙት ፌደራል ትሩዝ ፓርቲን ወክለው የተወዳደሩት ፋደል አልሳይድ ሹያብ መሆናቸውንና ያገኙት ድምጽም 1.43 በመቶ ብቻ መሆኑን አስታውቋል።ከሚያዝያ 5 ቀን ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በመላ አገሪቱ በተቋቋሙ 11 ሺህ የድምጽ ጣቢያዎች በተከናወነው የድምጽ አሰጣጥ ስነስርአት ላይ ድምጽ ለመስጠት ከተመዘገቡት ውስጥ ሁለት ሶስተኛው ድምጽ አለመስጠታቸውንና ለፕሬዚዳንታዊ ምርጫው በተፎካካሪነት የቀረቡት 15 እምብዛም እውቅና የሌላቸው ዕጩ ተወዳዳሪዎች ብቻ እንደነበሩም አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡ አሜሪካ፣ እንግሊዝና ኖርዌይን ጨምሮ በርካታ ምዕራባውያን አገራት፣ ላለፉት 25 አመታት ሱዳንን በፕሬዚዳንትነት የመሩት አልበሽር፤ በከፍተኛ ድምጽ ያሸነፉበትንና ባለፈው ሰኞ የተከናወነውን የአገሪቱ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ነጻና ፍትሃዊ አይደለም፣ እውቅና አንሰጠውም ሲሉ የተቹት ሲሆን፣ የቻይናው ፕሬዚደንት ዢ ጂፒንግ በበኩላቸው፤ ለአልበሽር የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት ልከዋል፡፡
ስቲስ ኤንድ ኢኳሊቲ ሙቭመንት የተባለው የአገሪቱ አማጺ ቡድን ባለፈው እሁድ በደቡብ ዳርፉር አካባቢ በሱዳን መንግስት ጦር ላይ በከፈተው ወታደራዊ ጥቃት የጦር ካምፕ ማውደሙንና የጦር መሳሪያዎችን መማረኩን ያስታወቀ ሲሆን፣ የአገሪቱ የጦር ሃይል በበኩሉ አማጽያኑ በሚንቀሳቀሱበት አካባቢ ባደረገው ድብደባ ከፍተኛ ውድመት ማድረሱን አስታውቋል፡፡ በአየር ድብደባው 16 ሲቪል ዜጎች መሞታቸውንና ከ11 በላይ የሚሆኑ ደግሞ መቁሰላቸውን የዘገበው አይቢታይምስ ነው፡፡
በዳርፉር ግጭት የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጽመዋል በሚል በአለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ የቀረበባቸውና የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው የ71 አመቱ አልበሽር፣ ድርጊቱን አልፈጸምኩም ሲሉ ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን ዘገባው ጨምሮ አስታውሷል፡
ፕሬዚዳንት አልበሽር እ.ኤ.አ በ1989 በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ከያዙበት ጊዜ አንስቶ አገሪቱን እየመሩ ሲሆን ሱዳንን ለረጅም ጊዜ በመምራት ቀዳሚው ሰው እንደሆኑ ይታወቃል፡፡

ባለፈው ቅዳሜ በኔፓል በተከሰተውና በሬክተር ስኬል 7.8 በተመዘገበው አሰቃቂ የርዕደ-መሬት አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ5ሺህ በላይ መድረሱ መረጋገጡን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡
በርዕደ-መሬቱ የተጎዱ ዜጎችን የማፈላለጉና እርዳታ የሚፈልጉ ዜጎችን የመድረሱ እንቅስቃሴ በአስቸጋሪ የአየር ንብረት ሳቢያ አዳጋች ሆኖ የቀጠለ ሲሆን እስካለፈው ረቡዕ ድረስ ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከ5ሺህ በላይ መድረሱን ዘገባው አመልክቷል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ በአደጋው ከሞቱት በተጨማሪ ከ10ሺህ በላይ ሰዎችም የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን፣ ፍለጋው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የሟቾችም ሆነ የቁስለኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር ተገምቷል፡፡  
ኔፓልን መልሶ ለማቋቋም ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ያስፈልጋል ተብሎ እንደሚገመት ያስታወቀው ዘገባው፣ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መስሪያ ቤት በበኩሉ፤ በአደጋው የደረሰው ጥፋት እስከ 10 ቢሊዮን ዶላር እንደሚገመት መግለጹን አስታውቋል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ከሰዓት በኋላ ላንግታንግ በተባለችው የኔፓል አካባቢ በደረሱ ሁለት የመሬት መንሸራተት አደጋዎች፣ ከ200 በላይ ሰዎች የደረሱበት እንደጠፋም ዘገባው ጠቁሟል፡፡
የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሱሺል ኮይራላ በአደጋው ህይወታቸው ያለፈ ዜጎችን ለመዘከር ባለፈው ማክሰኞ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ብሄራዊ ሃዘን ያወጁ ሲሆን ባለፉት አስር አመታት በርዕደ-መሬት ሳቢያ ለህልፈተ ህይወት የተዳረጉ ዜጎች ቁጥር ከ10 ሺህ በላይ እንደሚደርስም አስታውቀዋል፡፡
በአደጋው የተጎዱ ዜጎች ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የድረሱልኝ ጥያቄ እያቀረቡ እንደሚገኙ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በሂሊኮፕተር የታገዘ እንቅስቃሴ እየተደረገ ቢገኝም፣ ከፍተኛ ዝናብና ውሽንፍር ከመኖሩና ከቦታዎቹ ተራራማነት ጋር በተያያዘ፣ በከፋ ሁኔታ በተጎዱ አካባቢዎች ፈጥኖ ለመድረስ አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱንም ገልጸዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ የቅዳሜው የኔፓል ርዕደ-መሬት ስምንት ሚሊዮን ያህል ሰዎችን ተጠቂ እንዳደረገ ያስታወቀ ሲሆን፣ ለአስቸኳይ የአደጋ ጊዜ እርዳታ የሚውል 15 ሚሊዮን ዶላር ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
የተመድ ቃል አቀባይ ፋራህ ሃቅ እንዳሉት፤ የገንዘብ ድጋፉ ተጎጂዎችን ለመታደግ በመስራት ላይ የሚገኙ የሰብዓዊ ተቋማትን እንቅስቃሴ ለማሳደግና ለተጎጂዎቹ የመጠለያ፣ የውሃ፣ የመድሃኒትና የሌሎች አገልግሎቶች አቅርቦቶችን ለማሟላት የሚውል ነው።
ህንድ፣ አሜሪካ፣ ቻይና፣ ማሌዢያ፣ ፓኪስታን እና እስራኤል ተጎጂዎችን ለመርዳት የሚደረገውን እንቅስቃሴ ለመደገፍ አውሮፕላኖችን ወደ ኔፓል የላኩ ሲሆን አሜሪካ በበኩሏ ለፈጥኖ ደራሽ እርዳታ የሚውል 10 ሚሊዮን ዶላር ለመለገስ ቃል ከመግባቷ በተጨማሪ የእርዳታ ድርጅቶቿን በአደጋው የተጎዱትን ዜጎች እንዲረዱ ወደ ኔፓል ልካለች፡፡