Administrator

Administrator

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የመካከለኛው ምሥራቅና አፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ፣ አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ በምታደርገው እንቅስቃሴ ወደ “ጸረ-ኢትዮጵያ ጥምረት” አጋድላለች የሚሉ ዘገባዎችን “ሐሰተኛ፣ የተሳሳተና አላስፈላጊ ውጥረት የሚፈጥር” ሲሉ አጣጥለውታል።

በቅርቡ በካይሮ ከግብፅ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ባደረጉት ስብሰባ በቀጠናው ትኩረት ቢስቡም፣ አሜሪካ የምትከተለው ዲፕሎማሲ ተቀናቃኝ ጎራ ከመፍጠር ይልቅ ከሁሉም አጋሮች ጋር ግጭትን በመከላከልና ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል።

አማካሪው በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ዩናይትድ ስቴትስ የጋራ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ ከኢትዮጵያም ሆነ በመላው የአፍሪካ ቀንድ እና የቀይ ባሕር አካባቢ ከሚገኙ ሀገራት ጋር አብራ እንደምትሠራ አረጋግጠዋል።

የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አማች የሆኑት ቡሎስ ከአገራቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ባደረጉት ውይይት የሁለትዮሽ ግንኙነትንና የቀጠናውን ሁኔታ መምከራቸውን የገለጹ ሲሆን፣ የትራምፕ አስተዳደርም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከኤርትራ ጋር የነበረውን ግንኙነት ለማደስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ተመላክቷል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 አሮጌ ቄራ አካባቢ የሚገኘው TNT Construction የግንባታ ፕሮጀክት ተሽከርካሪዎች መንገድን በጭቃ በማበላሸታቸው 55 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት ተጣለባቸው።

ድርጅቱ ድርጊቱን ከፈጸመ በኋላ በወቅቱ የነበረውን ዝናብ ተገን በማድረግ ተሽከርካሪዎቹን ለመሰወር ቢሞክርም፣ የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤት ከልደታ ትራፊክ ማኔጅመንት ጋር በመተባበር ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪዎቹን በመለየት ቅጣቱን ለመጣል ችሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ተቋማት ሥራቸውን ሲያከናውኑ የኮሪደር ልማቶችን፣ የመንገድ መሠረተ ልማቶችንና አረንጓዴ ስፍራዎችን በጥንቃቄ የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስቧል። በተጨማሪም ወቅቱ የክረምት በመሆኑ ለማህበረሰቡ አደጋ የሚያስከትሉ እና የመሠረተ ልማት ጥበቃን ችላ የሚሉ አካላት ላይ ሕግ የማስከበር እርምጃው በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥል ገልጿል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከትኬት ሽያጭ የሰበሰበውን ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሬ ከኤርትራ፣ ሞዛምቢክ እና ሩሲያ ማውጣት አለመቻሉን ገለጸ። የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የተቋሙን የሥራ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ በተለይም ከኤርትራ ያገኘውን ገንዘብ ለማስወጣት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካ ተናግረዋል።

አየር መንገዱ የተያዘበትን ገንዘብ ለማስመለስ በኤርትራ ፍርድ ቤት ክስ መስርቶ የነበረ ቢሆንም፣ ጉዳዩ በፖለቲካዊ ሁኔታዎች ምክንያት ሊሳካ እንዳልቻለ አቶ መስፍን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በአገራቱ የተያዘው ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሬ በአየር መንገዱ የፋይናንስ እንቅስቃሴ ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል።

ዩናይትድ ስቴትስ ከነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአስመራ፣ ጁባ፣ ሃራሬ፣ ባማኮ እና ደርባን ጨምሮ በ24 የአፍሪካ ከተሞች በሚገኙ ኤምባሲዎቿና ቆንስላዎቿ የምትሰጠውን መደበኛ የቪዛ አገልግሎት እንደምትገታ አስታወቀች።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እንዳስታወቀው፣ ይህ ውሳኔ የደህንነት ፍተሻዎችን ለማጠናከር፣ የመንግሥት ወጪን ለመቀነስ እና የቪዛ አሰጣጥ ሂደቱን ወጥ ለማድረግ ያለመ ነው። በዚህም ምክንያት በእነዚህ አገራት የሚገኙ አመልካቾች ለቱሪስት፣ ለንግድ፣ ለሥራ እና ለቋሚ ነዋሪነት ቪዛዎች በተመደቡ ቀጠናዊ ማዕከላት ለመጠቀም ይገደዳሉ።

ሆኖም ውሳኔው የኤምባሲዎቹን መዘጋት የሚያስከትል ባለመሆኑና ቀደም ሲል የተሰጡ ጸንተው የሚሠሩ ቪዛዎች ላይ ተጽዕኖ የማያደርግ መሆኑ ተገልጿል። መደበኛ የቪዛ አገልግሎቶች በአዲስ አበባ፣ ሌጎስ፣ ናይሮቢ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ጆሃንስበርግ እና ጂቡቲን ጨምሮ በዋና ዋና ቀጠናዊ ማዕከላት ባልተቋረጠ ሁኔታ የሚቀጥሉ ይሆናል። ለምሳሌ ያህል በናይጄሪያ አቡጃ ይሰጥ የነበረው አገልግሎት ቢቋረጥም በሌጎስ የሚቀጥል በመሆኑ አመልካቾች ወደዚያ መጓዝ ይኖርባቸዋል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

የቦስተን ፓርትነርስ መስራችና የኩሪፍቱ ሪዞርትስ እና ስፓ ባለቤት ኢትዮጵያዊው ባለሀብት ታዲዮስ በለጠ፣ በኬንያ የቱሪዝም ዘርፍ ትልቅ ኢንቨስትመንት ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አስታወቁ።
ባለሀብቱ በኬንያዋ የወደብ ከተማ ሞምባሳ ከሀገሪቱ ባለሀብቶች ጋር በመተባበር ግዙፍ የውሃ ፓርክ (Water Park) ለማቋቋም ማቀዳቸውን ይፋ ያደረጉ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና ትልቁ የውሃ ፓርክ እንደሚሆን በኬንያ መገናኛ ብዙኃን የወጡ ዘገባዎች አመልክተዋል።
ይህ ትልቅ የኢንቨስትመንት ብስራት ይፋ የሆነው፣ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በናይሮቢ ያዘጋጀውን የኢትዮጵያን የቱሪዝም መስህቦች የማስተዋወቅ መድረክ ተከትሎ ነው። ሚኒስቴሩ በዚሁ መድረክ ላይ ለኬንያውያን ባለሀብቶች፣ ለአስጎብኝ ድርጅቶች፣ ጋዜጠኞች እና የሶሻል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ማብራሪያ የሰጠ ሲሆን፣ በቀጣይም የኬንያ አስጎብኝዎችንና የሜዲያ አካላትን ወደ ኢትዮጵያ በመጋበዝ የሀገሪቱን የቱሪዝም ሀብቶች ለማስጎብኘት ማቀዱን አስታውቋል።
[ዋዜማ]-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አማካሪና የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ የሕወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በሚስጢር መገናኘታቸውን በመግለጽ ከባድ ክስ ሰንዝረዋል። ጌታቸው ረዳ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፣ ደብረጽዮን ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር የተገናኙት የጦር መሣሪያ ድጋፍ ለመጠየቅ እንደነበር ገልጸዋል።
እንደ ጌታቸው ገለጻ፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ለሕወሓት ሊቀመንበር በሰጡት ምላሽ በኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት ላይ ድጋሚ ጦርነት ከከፈታችሁ በኋላ አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርግላችኋለን ማለታቸውን ተናግረዋል። ሆኖም ግን ይህ ምስጢራዊ ስብሰባ መቼ እና የት ቦታ እንደተካሄደ ጌታቸው ረዳ በጽሑፋቸው ላይ የጠቀሱት ነገር የለም።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይን አስመልክተው ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት፤ በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በቦረና ወረዳ በሚገኘው ግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. በተፈጸመ አሰቃቂ ጥቃት የመናንያን መነኮሳይያት ሕይወት በግፍ መጥፋቱን፣ በርካቶች መቁሰላቸውን እና የገዳሙ ንዋየ ቅዱሳት መውደማቸውን በከፍተኛ ሐዘን ገልጸዋል። ከዚህም በተጨማሪ በሐድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአምልኮ ሥፍራ በኃይል መፍረሱና በምእመናን ላይ ጥቃት መድረሱ ፍጹም ተቀባይነት የሌለው እና የተወገዘ ተግባር መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ቅዱስነታቸው ራሳቸውን ለመከላከል ምንም ዓይነት ቁሳዊ ዝግጅት በሌላቸው ንጹሐን መናንያን ላይ እጅን ማንሣት በእግዚአብሔር ዘንድ የተከለከለና በታሪክ ፊት የሚያሳፍር መሆኑን ጠቁመው፣ ጥቃቱን የፈጸሙ አካላት ለፍትሕ እንዲቀርቡ እና የገዳማትና አድባራት ደኅንነት እንዲጠበቅ ለሚመለከታቸው አካላት ጥሪ አስተላልፈዋል። ሕዝበ ክርስቲያንና መላው ኢትዮጵያውያን የጥቃት ሰለባ ከሆኑት ወገኖች ጋር በመንፈሳዊም ሆነ በሰብአዊ ድጋፍ አብረው እንዲቆሙም አባታዊ አደራቸውን አስተላልፈዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በንግድ ፖሊሲው ላይ ባደረገው አዲስ ክለሳ ከዋና ዋና የንግድ አጋሮቹ በሚገቡ ምርቶች ላይ አዲስ የገቢ ንግድ ታሪፍ መጣሉን ይፋ አድርጓል።

በዚህ አዲስ ውሳኔ መሠረት 12.5 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ የተካተቱ ሲሆን፣ እርምጃው አሜሪካ የዓለም አቀፍ ንግድ ማዕቀፏን ዳግም ለመቅረጽ የምታደርገው ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።

ይህ አዲስ አሰራር በተለይም የነዳጅ፣ የጨርቃጨርቅ እና የምግብ ምርቶችን ወደ አሜሪካ በሚልኩት በእነዚህ የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። ውሳኔው የአሜሪካን የአገር ውስጥ አምራቾች ለመጠበቅ እና የንግድ ሚዛን እጥረትን ለመቀነስ ያለመ ነው ቢባልም፣ በዓለም አቀፍ የንግድ ትስስር እና ኤክስፖርት ላይ አዲስ ፈተና ደቅኗል።

የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

በአንድ ሳምንት አምስት ቴአትሮችን እየሰራ ስላለው ብርቱው ተዋናይ ትእዛዙ ታዬ ጥቂት መረጃ አድርሼ ነበር። እሱን ተንተርሶ ተጨማሪ ሀሳብ አርቲስት መርዕድ ተስፋዬ አከለበት። እንዲህ ሲል፦
***
በጣም የሚገርመኝ የትዕዛዙ ልዩ ችሎታ ደግሞ የሌሎች ተዋንያንን ገፀ ባህሪ በአጭር ጊዜ አጥንቶ ተክቶ በመስራት ብዙ ቴአትሮችን ከመዘጋት ታድጓል!!!.....ቁጠሩ እንግዲህ....
ለምሳሌ ለመጥቀስ ያህል:-
1."ህንደኬ" ላይ....ተዋናይ ደረጄ ደመቀን ተክቶ
ሰርቷል፡፡
2."ሶስተኛው ችሎት" ላይ....ተዋናይ ፈለቀ የማር ውሀ አበበ እና ተዋናይ ሱራፌል ተካ የሚሰሩትን ገፀ ባህሪ ተክቶ ሰርቷል፡፡
3."አሉ" ቴአትር ላይ ተዋናይ ሳሙኤል ተስፋዬን
ተክቶ ሰርቷል፡፡
4."መንታ መንገድ" ላይ ተዋናይ ተስፋዬ ገ/ሐናን
ተክቶ ሰርቷል፡፡
5.አሁን በቅርቡ ደግሞ "12ቱ እንግዶች" ላይ ተዋናይ ዳንኤል አሸናፊን ተክቶ ሰርቷል!!!......ይሔኔ እኮ ያልጠቀስኩትም ይኖራል!!!.......ለማንኛውም ትዜ ከትወናውም ውጪ ቴአትርን በብዙ ነገር እየደገፈ ያለ ጎበዝ እና ልበ ቅን ባለሙያ ነው!!!
***
ባለሙያ በቅንነት እንዲህ ማድነቅ ሲችል ደስ ይላል። እናመሰግናለን መርዕድ።
ውድነህ ክፍሌ-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከ«ሰዎች ለሰዎች» ድርጅት ጋር በመተባበር በሀገራችን በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውን የስማርት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባታ በይፋ አስጀምሯል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት፣ የዚህ ኮሌጅ ግንባታ ሲጠናቀቅ ወጣቶችን በማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሪክና ኤሌክትሮኒክስ፣ በኮሚዩኒኬሽንስ፣ በቴክስታይል እና በሲኤንሲ ቴክኖሎጂዎች ላይ ዘመናዊና ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን የሚሰጥ ይሆናል። ፕሮጀክቱ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ወጣቶችን ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት፣ ከንድፈ-ሃሳብ ደግሞ ወደ ተግባር የሚያሸጋግር አዲስ የክህሎት ድልድይ እንደሚሆንም ተመልክቷል።
ሀገርን ማልማትና ከድህነት መላቀቅ በንድፈ-ሃሳብ ብቻ ስለማይቻል ሃሳብ የሚያፈልቁ አዕምሮዎችንና የሚሰሩ እጆችን ያጣመረ ክህሎት መር የሰው ሀይል አስፈላጊ መሆኑን ከንቲባዋ ጠቁመዋል።
Page 4 of 817