Administrator
አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ “ጸረ-ኢትዮጵያ ጥምረት”ፈጥራለች መባሉን አስተባበለች
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የመካከለኛው ምሥራቅና አፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ፣ አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ በምታደርገው እንቅስቃሴ ወደ “ጸረ-ኢትዮጵያ ጥምረት” አጋድላለች የሚሉ ዘገባዎችን “ሐሰተኛ፣ የተሳሳተና አላስፈላጊ ውጥረት የሚፈጥር” ሲሉ አጣጥለውታል።
በቅርቡ በካይሮ ከግብፅ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ባደረጉት ስብሰባ በቀጠናው ትኩረት ቢስቡም፣ አሜሪካ የምትከተለው ዲፕሎማሲ ተቀናቃኝ ጎራ ከመፍጠር ይልቅ ከሁሉም አጋሮች ጋር ግጭትን በመከላከልና ዘላቂ ሰላምን በማረጋገጥ ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል።
አማካሪው በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ዩናይትድ ስቴትስ የጋራ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ ከኢትዮጵያም ሆነ በመላው የአፍሪካ ቀንድ እና የቀይ ባሕር አካባቢ ከሚገኙ ሀገራት ጋር አብራ እንደምትሠራ አረጋግጠዋል።
የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አማች የሆኑት ቡሎስ ከአገራቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ባደረጉት ውይይት የሁለትዮሽ ግንኙነትንና የቀጠናውን ሁኔታ መምከራቸውን የገለጹ ሲሆን፣ የትራምፕ አስተዳደርም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከኤርትራ ጋር የነበረውን ግንኙነት ለማደስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ተመላክቷል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
መንገድ በጭቃ ያበላሸው ድርጅት 55 ሺህ ብር ተቀጣ
በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 አሮጌ ቄራ አካባቢ የሚገኘው TNT Construction የግንባታ ፕሮጀክት ተሽከርካሪዎች መንገድን በጭቃ በማበላሸታቸው 55 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት ተጣለባቸው።
ድርጅቱ ድርጊቱን ከፈጸመ በኋላ በወቅቱ የነበረውን ዝናብ ተገን በማድረግ ተሽከርካሪዎቹን ለመሰወር ቢሞክርም፣ የአራዳ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤት ከልደታ ትራፊክ ማኔጅመንት ጋር በመተባበር ባደረገው ክትትል ተሽከርካሪዎቹን በመለየት ቅጣቱን ለመጣል ችሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለሥልጣን ተቋማት ሥራቸውን ሲያከናውኑ የኮሪደር ልማቶችን፣ የመንገድ መሠረተ ልማቶችንና አረንጓዴ ስፍራዎችን በጥንቃቄ የመጠበቅ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስቧል። በተጨማሪም ወቅቱ የክረምት በመሆኑ ለማህበረሰቡ አደጋ የሚያስከትሉ እና የመሠረተ ልማት ጥበቃን ችላ የሚሉ አካላት ላይ ሕግ የማስከበር እርምጃው በተጠናከረ ሁኔታ እንደሚቀጥል ገልጿል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
አየር መንገዱ ከትኬት ሽያጭ የተሠበሠበ ገንዘቡን ከሦስት አገራት ማውጣት አለመቻሉን አስታወቀ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከትኬት ሽያጭ የሰበሰበውን ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሬ ከኤርትራ፣ ሞዛምቢክ እና ሩሲያ ማውጣት አለመቻሉን ገለጸ። የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው የተቋሙን የሥራ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፣ በተለይም ከኤርትራ ያገኘውን ገንዘብ ለማስወጣት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካ ተናግረዋል።
አየር መንገዱ የተያዘበትን ገንዘብ ለማስመለስ በኤርትራ ፍርድ ቤት ክስ መስርቶ የነበረ ቢሆንም፣ ጉዳዩ በፖለቲካዊ ሁኔታዎች ምክንያት ሊሳካ እንዳልቻለ አቶ መስፍን አብራርተዋል። በአሁኑ ወቅት በአገራቱ የተያዘው ይህ ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሬ በአየር መንገዱ የፋይናንስ እንቅስቃሴ ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል።
አሜሪካ በ24 የአፍሪካ ከተሞች የቪዛ አገልግሎት ልታቋርጥ ነው
ዩናይትድ ስቴትስ ከነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአስመራ፣ ጁባ፣ ሃራሬ፣ ባማኮ እና ደርባን ጨምሮ በ24 የአፍሪካ ከተሞች በሚገኙ ኤምባሲዎቿና ቆንስላዎቿ የምትሰጠውን መደበኛ የቪዛ አገልግሎት እንደምትገታ አስታወቀች።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እንዳስታወቀው፣ ይህ ውሳኔ የደህንነት ፍተሻዎችን ለማጠናከር፣ የመንግሥት ወጪን ለመቀነስ እና የቪዛ አሰጣጥ ሂደቱን ወጥ ለማድረግ ያለመ ነው። በዚህም ምክንያት በእነዚህ አገራት የሚገኙ አመልካቾች ለቱሪስት፣ ለንግድ፣ ለሥራ እና ለቋሚ ነዋሪነት ቪዛዎች በተመደቡ ቀጠናዊ ማዕከላት ለመጠቀም ይገደዳሉ።
ሆኖም ውሳኔው የኤምባሲዎቹን መዘጋት የሚያስከትል ባለመሆኑና ቀደም ሲል የተሰጡ ጸንተው የሚሠሩ ቪዛዎች ላይ ተጽዕኖ የማያደርግ መሆኑ ተገልጿል። መደበኛ የቪዛ አገልግሎቶች በአዲስ አበባ፣ ሌጎስ፣ ናይሮቢ፣ ካምፓላ፣ ኪጋሊ፣ ጆሃንስበርግ እና ጂቡቲን ጨምሮ በዋና ዋና ቀጠናዊ ማዕከላት ባልተቋረጠ ሁኔታ የሚቀጥሉ ይሆናል። ለምሳሌ ያህል በናይጄሪያ አቡጃ ይሰጥ የነበረው አገልግሎት ቢቋረጥም በሌጎስ የሚቀጥል በመሆኑ አመልካቾች ወደዚያ መጓዝ ይኖርባቸዋል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas
የኩሪፍቱ ባለቤት በምሥራቅ አፍሪካ ግዙፉን የውሃ ፓርክ በኬንያ ሊገነቡ ነው
"ደብረጽዮን ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጋር በሚስጢር ተገናኝተዋል!"
በደቡብ ወሎ ገዳም ላይ በተፈጸመ ጥቃት መነኮሳይያት በግፍ መገደላቸውን ፓትርያርኩ አወገዙ
የትራምፕ አዲስ ታሪፍ ሰባት የአፍሪካ ሀገራትን ኢላማ አደረገ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በንግድ ፖሊሲው ላይ ባደረገው አዲስ ክለሳ ከዋና ዋና የንግድ አጋሮቹ በሚገቡ ምርቶች ላይ አዲስ የገቢ ንግድ ታሪፍ መጣሉን ይፋ አድርጓል።
በዚህ አዲስ ውሳኔ መሠረት 12.5 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ ከተጣለባቸው ሀገራት መካከል አልጄሪያ፣ አንጎላ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ የተካተቱ ሲሆን፣ እርምጃው አሜሪካ የዓለም አቀፍ ንግድ ማዕቀፏን ዳግም ለመቅረጽ የምታደርገው ጥረት አካል እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ አዲስ አሰራር በተለይም የነዳጅ፣ የጨርቃጨርቅ እና የምግብ ምርቶችን ወደ አሜሪካ በሚልኩት በእነዚህ የአፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል። ውሳኔው የአሜሪካን የአገር ውስጥ አምራቾች ለመጠበቅ እና የንግድ ሚዛን እጥረትን ለመቀነስ ያለመ ነው ቢባልም፣ በዓለም አቀፍ የንግድ ትስስር እና ኤክስፖርት ላይ አዲስ ፈተና ደቅኗል።
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

