Administrator

Administrator

  • ዓምና  በተፈጸሙ 10 ሺህ ያህል ጥቃቶች፣ ከ18 ሺህ በላይ ሰዎች ሞተዋል
  • 6ሺህ 362 ሰዎች የሞቱባት ኢራቅ ቀዳሚነቱን ይዛለች

        በአለማችን የሚፈጸሙ የሽብር ጥቃቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ በመምጣት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱንና ባለፈው የፈረንጆች አመት ብቻ ከ18 ሺህ በላይ የተለያዩ አገራት ዜጎች ለህልፈት መዳረጋቸውን ስካይ ኒውስ ዘገበ፡፡
የአለማቀፉን የሽብርተኝነት አመልካች ጥናት ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ እ.ኤ.አ በ2013 ብቻ በአለማችን የተለያዩ ክፍሎች 10ሺህ ያህል የሽብር ጥቃቶች የተፈጸሙ ሲሆን፣ በጥቃቶቹ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከአንድ አመት በፊት ከነበረው  በእጥፍ ያህል መጨመሩንም ጠቁሟል፡፡በአመቱ በሽብር ጥቃቶች በርካታ ዜጎች የሞቱባት ቀዳሚ የዓለማችን አገር ኢራቅ ስትሆን፣ በአገሪቱ 6ሺህ 362 ያህል ሰዎች ከሽብር ጥቃቶች ጋር በተያያዘ ለሞት ተዳርገዋል፡፡
ችግሩ በከፍተኛ ሁኔታ የተስፋፋበቸው ሌሎች የአለማችን አገራት አፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን፣ ሶሪያና ናይጀሪያ ሲሆኑ፣ አይኤስ፣ አልቃይዳ፣ ታሊባንና ቦኮሃራም ደግሞ በአገራቱ አብዛኞቹን ጥቃቶች የፈጸሙ ቡድኖች ናቸው ተብሏል፡፡ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎች በሚታዩባቸው 162 የአለማችን አገራት ላይ የሰራውን አለማቀፍ የሽብርተኝነት አመልካች ጥናት ለሁለተኛ ጊዜ ይፋ ያደረገው፣ ኢንስቲቲዩት ፎር ኢኮኖሚክስ ኤንድ ፒስ የተባለ አለማቀፍ ተቋም ነው፡፡

“ፒካሶ የሚባለው ዋና የጥፋት ዲያቆን ነው፡፡ ከስዕል ጥበብ ውስጥ ምክንያታዊነትን ሙሉ ለሙሉ አውጥቶ አብስትራክት አርት ፈጠርኩ አለ፡፡ ደግሞም ፈጥሯል፡፡ በድህረ-ዘመናዊነት ማፍረስ መፍጠር በመሆኑ ማለት ነው፡፡ ባለ ሦስት አውታሩን ስዕል ወደ ሁለት አውታር፣ ሲሻው ደግሞ አውታር አልባ አድርጐ አቀረበ፡፡”


ስለ ምን ላውራ? ስለ ምንም ነገር ባወራ ከዘመኑ መንፈስ ውጭ አይሆንም አይደል? አንድ ወዳጄ ዘመኑ “ድህረ ዘመናዊነት” (Post modernism) ነው ብሎኛል፤ እኔም አምኜዋለሁ፡፡ አምኜም ለአማኝ አውርቼ አሳምኛለሁ፡፡ እንግዲህ ይህ የሀሳብ ወዳጅ እንደነገረኝ ከሆነ፣ መጀመሪያ የአዳም እና የሄዋንን ታሪክ ከስር መሰረቱ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ የአዳም እና የሄዋን ታሪክ በጣም አጭር ነው፡፡ አንድ መስመር ነው እንዲያውም፡፡ ሄዋን አንገት ናት፤ አዳም ደግሞ እራስ ነው፡፡ ይሄ አጭር ታሪክ ጥንታዊ ነው፡፡ ጥንታዊ እና ሃይማኖታዊ፡፡
ዘመናዊው የሰው ልጅ ታሪክም እንደ ጥንታዊው በጣም አጭር ነው፡፡ ጥንታዊው አዳም እራስ፣ ሄዋን አንገት ነበረች ብያለሁ፡፡ ዘመናዊው ላይ ምንም አዲስ ነገር አልተከሰተም፡፡ ጥንታዊው አዳም ዘመናዊ ሲሆን ጭንቅላቱን መጠቀም ጀመረ፡፡ ጭንቅላቱን መጠቀም ሲጀምር ልቡን መጠቀም ያቆማል፡፡ ልቡን መጠቀም ሲጀምር ደግሞ ተገላቢጦሽ፡፡ የዘመናዊነት አስተሳሰብ በአዳም ጭንቅላት መስራት እና አለመስራት ሁልጊዜ ብቅ የሚል እና ተመልሶ እልም የሚል ነገር ነው፡፡ ልክ እንደ ሀገራችን የመብራት አቅርቦት ብዬ መመሰል አይጠበቅብኝም፡፡ በግሪኮቹ ዘመን ጭንቅላቱን መጠቀም ጀምሮ ነበር ይባላል አዳም፡፡ በኋላ የክርስትና አብዮት ሲቀጣጠል ጭንቅላቱ ተመልሶ ጠፋበት፡፡ ጠፍቶበት ቆይቶ ወደ አስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን አካባቢ መልሶ መብራት መጣለት፡፡ ጭንቅላቱን እና እጁን አጣምሮ ሳይንስን አዋለደ፡፡ ማሽን ሰራ፣ በጭንቅላቱ ውስጥ ብቻ የማይቀር መብራት በጐጆው አበራ፡፡ ፋብሪካው፣ መድሃኒቱ፣ መንገዱ፣ ባቡሩ…የዚህ ፈጠራው ማስታወሻ ናቸው፡፡
ይሄ ከላይ የጻፍኩት ሁሉ ወዳጄ ያወራልኝን መሆኑ አይዘንጋ!
ድህረ - ዘመናዊነትስ? አልኩት፡፡
ድህረ - ዘመናዊነት ልብንም ሆነ ጭንቅላትን በአንድ ላይ ለማጣት የሚያደርገው ሙከራ ነው አለኝ፡፡ ምሳሌ እንዲሰጠኝ ጠየቅሁት፡፡
ምሳሌውን ከፈላስፎቹ ነው የጀመረልኝ…ሳይንስ በተወለደበት ግርግም ውስጥ ሰበአ ሰገሎቹ ስጦታ ይዘው ለሰው ልጅ መጡ፡፡ ይዘው የመጡት እጅ መንሻ ግን ከርቤ፣ ወርቅ እና እጣን አልነበረም፤ አለኝ፡፡
የሰበአ ሰገሎቹ ስም ሰረን ኪርከርጋርድ፣ ማርቲን ሀይደርጋር እና ፍሬድሪክ ኒቼ ናቸው፡፡ ይዘው የመጡት ስጦታ…ሳይንስ ወይም የልጅነት ልምሻን የሚከላከል ክትባት አልነበረም፡፡ አቀጭጮ የሚገድለውን መጽሐፍ ነው ያበረከቱለት፡፡ ሳይንስ ቀጭጮም አልሞተም፤በልጅነት ልምሻ ተጠቅቶ በዱላ እየተደገፈ በህይወት መኖረ ቀጠለ፡፡
ከሳይንስ ጋር የጓደኛዬ ትረካም ቀጥሏል፡፡
ሳይንስ የሚኖረው ምክንያታዊነት እስካለ ድረስ ነው፡፡ ምክንያታዊነት በጭንቅላት ነው የሚሰራው፡፡ ምክንያታዊነት በሃይማኖት ወይንም በልብ ወይንም በስሜት አይሰራም፡፡ ድህረ - ዘመናዊነት በማይሰራው እንዲሰራ፣ በሚሰራው እንዳይሰራ የማድረጊያ ፍልስፍና ነው፡፡ አንገትን ጭንቅላት፣ ጭንቅላትን አንገት ሲደረጉ ነው ወይ የማይሰራው እንዲሰራ የሚሆነው፡፡ አልኩት፡፡ እኔ የሴቶችን ከጓዳ ወደ መስክ መውጣት ለማለት ፈልጌ ነው፡፡
ሴት እና ወንድ ሁለቱም ጭንቅላት፣ ሁለቱም አንገት አላቸው፤ልዩነታቸው በአንገት እና በጭንቅላት ሊመሰል አይችልም፡፡ ሴቶች የወንዶችን የቀድሞ ሃላፊነት መጋራታቸው እንዲያውም ምክንያታዊ-- ሳይንሳዊ ነው፡፡ እኔ የምልህ ሌላ ነው፡፡ እኔ የምልህ በደንብ እንዲገባህ ወደ ጥበባቱ ብናተኩር ይሻላል፡፡
ቅድም የጠቀስኳቸው ሰብዓ ሰገሎች፣ ፈላስፎች ወይንም ጠንቋዮች ምክንያታዊነትን የሚያጣጥል ፍልስፍና በምክንያታዊ መሳይ አቀራረብ፣በተወለደው ልጅ ደም ውስጥ ረጭተው ዞር አሉ፡፡ የተረጨው መርዝ መስራት የጀመረው…እንደ ሁልጊዜውም መጀመሪያ በተጨባጭ የታየው ጥበበኞቹ ላይ ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ የድህረ-ዘመናዊነት ምረዛ ሰለባዎች፣ በሃያኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነው ወደ አለም መድረክ የመጡት፡፡ ስማቸውን ታውቃቸዋለህ? እነ ፒካሶ፣ እነ ገርትሩድ እስታይን፣ እነ ጄምስ ጆይስ…ምናምን ናቸው፡፡ ይዘን መጣን የሚሉት የጥበብ ዘይቤ…ኪውቢዝም፣ ዳይዝም…ስትሪም ኦፍ ኮንሸስነስ…ጂኒ ቁልቋል…ጂኒ ጃንካ… ፒካሶ የሚባለው ዋና የጥፋት ዲያቆን ነው፡፡ ከስዕል ጥበብ ውስጥ ምክንያታዊነትን ሙሉ ለሙሉ አውጥቶ አብስትራክት አርት ፈጠርኩ አለ፡፡ ደግሞም ፈጥሯል፡፡ በድህረ-ዘመናዊነት ማፍረስ መፍጠር በመሆኑ ማለት ነው፡፡ ባለ ሦስት አውታሩን ስዕል ወደ ሁለት አውታር፣ ሲሻው ደግሞ አውታር አልባ አድርጐ አቀረበ፡፡
ለስነጽሑፉ ደግሞ ጄምስ ጆይስ አለልህ፡፡ የሰውን የውስጥ የሃሳብ አፈሳሰስ አሳያለሁ ብሎ በእውን ህልም የሚያዩ ገፀ ባህሪዎች ቀረፀ፡፡ መጽሐፉን እስካሁን በቅጡ የሚረዱት ጥቂት ሰዎች ናቸው፡፡ በኋላ የመጨረሻ ስራውን አወጣ፡፡ Finnigans wake ይባላል፡፡ በዓለም ላይ የመጨረሻው ከባድ የልብ ወለድ ድርሰት መሆኑ ይነገርለታል፡፡ ከባድ የተባለው ከደራሲው በስተቀር ለማንም በግልፅ ስለማይገባ ነው፡፡ የራሱን አዲስ ቃላት እየፈጠረ፣ አንድ አረፍተ ነገር የሚያክሉ ቃላትን ያለ ክፍተት አንድ ላይ እያጠባበቀ … መግለፅ ሳይሆን መደበቅን ለአንባቢ አበረከተ፡፡ … ይኸው አበርክቶቱ የድርሰት ቁንጮ መሆኑ ይሰበካል … የድርሰትን ምክኒያታዊነት ሙሉ በሙሉ ኢ - ምክኒያታዊ ማድረግ ነው ግቡ፡፡ ግቡ ተሳክቶለታል፡፡
 ቅድም ልብን በጭንቅላት ስለ መቀየር አንስቼብሀለሁ፡፡ ድህረ ዘመናዊነት ልብም ጭንቅላትም አይደለም፡፡ ሁለቱንም አፈራርሶ፣ ከፍርስራሹ ከሁለቱም ውጭ የሆነ ነገር መፍጠር ነው፡፡ ልብን እምነት፣ ጭንቅላትን እውነታ ልንላቸው እንችላለን፡፡ ድህረ-ዘመናዊነት ጭንቅላትን እና ልብን እንደ መሳሪያ ተጠቅሞ .. መሳሪያውን መልሶ ለማፍረስ የሚደረግ የትዕቢት እንቅስቃሴ ነው … አለኝ እና ከንዴቱ መለስ አለ፡፡ እናም ቀጠለ፡፡
ወደ ሀገራችን ስትመጣም ጥበቡ በዚሁ ደዌ የተመታ ነው፡፡ ግን ደዌው ምክንያታዊነትን አይገድለውም፡፡ ምክንያቱም አበሻ ምክንያታዊነት በጭንቅላቱ ውስጥ ወይንም በልቡ ውስጥ የሚገኝ ባለመሆኑ ነው፡፡  የአበሻ ምክንያታዊነት የሚገኘው በባህሉ ውስጥ ነው፡፡ ባህል ደግሞ መቼ እንደተሰቀለ የማይታወቅ  ርቆ ያለ ማስጠንቀቂያ ነው፡፡ ማስጠንቀቂያው የፈለገ ርቆ ቢሰቀልም … ግልፅ ሆኖ ባይነበብም… መስራቱ ግን አይቀርም፡፡ ማስጠንቀቂያውን “የአበሻ ጨዋነት” ብለን ብንጠራው የራቀ ስያሜ አይመስለኝም፡፡ ማስጠንቀቂያው ከላይ “የአበሻ ጨዋነት” … ዝቅ ሲል ደግሞ በደቃቅ ፅሁፍ “የአበሻ ነብራዊ ዥንጉርጉርነት” ነው፡፡
ዥንጉርጉርነቱን በምሳሌ ላሳይህ፡-
በአንድ ቀለሙ ድህነትን የሚያከብር ህዝብ ነው… በሌላ በኩል ባለፀጋነትንም ይመኛል፡፡ በአንድ በኩል ክርስቲያን ነው-- በሌላ በኩል አዶ ከብሬ አለበት፡፡ ክታብ እና መስቀሉን አቻችሎ የሚኖር ህዝብ ነው፡፡ ሰም እና ወርቅ አለው፡፡ በጨዋነት ሰምና ወርቁን እየደበቀ እና እየገለፀ አንድ ላይ ያስተናግዳል፡፡ ቋንቋው  ራሱ የሰም እና የወርቅን ባህርይ በውስጡ ያቀፈ ነው፡፡ ስለዚህ የአበሻ ምክንያታዊነት የፈረንጆቹን አይደለም፡፡ የአበሻ ሃይማኖት የአውሮፓዊያኖቹን አይመስልም፡፡ ከውጭ መስሎ ቢገኝ እንኳን ከውስጥ ግን እነሱን አይደለም፡፡ አበሻ የራሱ አንገት እና የራሱ ጭንቅላት ባለቤት ነው፡፡ በአንገቱ አዟዙሮ ቢያይም በጭንቅላቱ አዟዙሮ ቢያስብም … ከዥንጉርጉርነቱ እና ከጨዋነቱ አያፈነግጥም፡፡
እና ምን እያልከኝ ነው? አልኩት፡፡
አበሻ ዘንድ ሞደርኒዝምም ሆነ ፖስት ሞደርኒዝም አይገባም፡፡ ሳይንስን በግርግሙ ስላላዋለደ … ሳይንስን አይነጠቅም፡፡ ድሮውኑ ያልነበረ ነገር አይጠፋም፡፡ ሳይንስን ያዋለዱት ሳይንስን ሲያከብሩ አብሮ ያከብራል፡፡ የሳይንስን ምክንያታዊነት ሲያዋርዱ ያዋርዳል፤ ግን የሚያዋርደው እነሱን ለማገዝ እንጂ ራሱን ለማርከስ አይደለም፡፡ የሚያከብረውም ሆነ የሚያደንቀው በሰም ደረጃ ያለውን ነው፡፡ ወርቁን ግን አያስነካም፡፡ አበሻ ዥንጉርጉርነት እና ጨዋነት ባህሉ ነው፡፡ ሳይንስም ሃይማኖትም ለሱ እነዚህ ናቸው፡፡
ስለዚህ … ሰለሞን ደሬሳ ቅርፃዊነት ብሎ ሲነሳ .. ወይንም አንቶኔ ኢንስታሌሽን አርት ብሎ ብቅ ሲል … ከራሱ ጥፋት ወይንም ልማት ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌላቸው … በደመነብሱም ቢሆን አውቆ ነው፡፡
የአበሻ ጨዋነት እና ዥንጉርጉርነት በድህረ-ዘመናዊነት አይነካም፡፡ አበሻ ሞደርን ከመሆኑ አስቀድሞ post modern ሊሆን ይችላል፡፡ አለም የያዘውን ፋሽን ይይዛል፡፡ ስለ ማንነት ቀውስ ሲነሳ፣ የቀውሱን መገለጫዎች ተላብሶ ወየው! ይላል፡፡ የጨዋነቱ አካል ነው ይኼም፡፡
አበሻ እንደ ፒካሶ ሙሉ ለሙሉ ሊያምፅ አይችልም፡፡ ምክንያታዊነት ላይ ለማመፅ መጀመሪያ ሳይንሳዊ ማንነት ያስፈልጋል፡፡ ሳይንሳዊ ማንነት ያላቸው፣ ሳይንሳዊ ፈጠራዎች ሲልኩለት ይቀበላል፡፡ ሳይንሳዊ ማንነትን ለማጥፋት የሚቀሰቅሱትንም ይተባበራል፡፡ ዘመናዊ ልብወለድን እና ዘመናዊ ትያትርን ይመለከታል፡፡ እነሱ በሰሩት መልክ ይሰራል፡፡ ባፈረሱት መንገድ ያፈርሳል፡፡ ወርቁን ግን አያስነካም፡፡ ዘመናዊ ልብወለዱን እያጻፈ፣ ባህላዊውን ተረቱን በዥንጉርጉር ልቡ የወርቅ ማህደር ውስጥ ይዞ ይቀጥላል፡፡ ባህላዊው ተረትና ምሳሌ በዘመናዊነት ውስጥ አልተፈጠረም፡፡ በድህረ-ዘመናዊነት ውስጥም አይለወጥም፡፡ ባህላዊው አበሻ ከፍልስፍና ውስጥ የተፈጠረም አይደለም፡፡ የፈረንጆቹ ምክንያታዊነት በጥቂት ፈላስፎች የተፈጠረ ነው፡፡ በመሆኑም በጥቂት ኢ-ምክኒያታዊ ፈላስፎች ተመልሶ ሊናድ ይችላል፡
ከአበሻ ጨዋነት ጋር የሚጋጭ ፍልስፍና ይዞ የሚመጣ ወዮለት፡፡ በአበሻ ዥንጉርጉርነት ጉራማይሌ ባህሉ ውስጥ የሚጋጨው ፍልስፍና፣ ከነብሩ ዥንጉርጉሮች መሀል አንዱ ይሆናል፡፡ የአበሻ ጨዋነት አንድ ኢላማ ስላልሆነ አንድ ተኳሽ አይመታውም፡፡ በነብር ቆዳ ላይ ያሉትን ነጠብጣቦች በአንድ ተኩስ መምታት አይቻልም፡፡ የነብሩ ህልውና ያለው በነጠብጣቦቹ ላይ ነው፡፡
ስለዚህ---አንተ ምክንያታዊነትን ነው የምትደግፈው ወይንስ ፖስት ሞደርኒዝምን? ቁርጡን ጠየቅሁት፡፡ የምደግፈው አበሻነቴን ነው፡፡ በአበሻነቴ ውስጥ ሁለቱም የሉም፡፡ ግን እንደ ፋሽን ፖስት ሞደርኒዝም ወደ እብደት ያጋደለ ሲመስለኝ ወደ ምክንያታዊነት እመለሳለሁ፡፡ ምክንያታዊነት አላፈናፍን ብሎ ችክ ሲልብኝ ደግሞ ወደ ሀይደርጋር ወይንም ወደ ኤግዚዝቴንሻሊዝም እመለሳለሁ፡፡ ኤግዚዝቴንሻሊዝም ራሱ ፖስት ሞደርኒዝም የገራው ኮሚኒዝም መሆኑን አትዘንጋ---፡፡ ብሎ ንግግሩን ቋጨልኝ፡፡ ግን የነገረኝ ሁሉ ራሴ መስማት የምፈልገውን በመሆኑ፣ ከሱ ወርጄ ንግግሩን የራሴ አደረግኋቸው፡፡  

          ሰባተኛ ክፍል እያለን እንዲህ ሆነ፡፡ አንድ አርብ የክፍል ቤስት ጓደኛዬ የሆነው ልጅ ደብተሬ ውስጥ ደብዳቤ እንዳስቀመጠና ቅዳሜንና እሁድን አስቤበት ሰኞ ምላሽ እንደሚጠብቅ ነገረኝ፡፡ ልጁ ባይጽፍልኝም እንደምንዋደድ ራሳችንም እናውቃለን፡፡ አብረን እናጠናለን፣ አብረን እንረብሻለን፣ አብረን እንጫወታለን፡፡
ክፍል ውስጥ የራሱ መቀመጫ ቢኖረውም አብዛኛውን ጊዜ የኔ ወንበር ላይ ነበር የሚገኘው፡፡ ቤቶቼ ያውቁታል፤ ይወዱታል፡፡ ከዚህ ያለፈ ምን ማድረግ እንደሚቻል አላውቅም፡፡ ብቻ ለደብዳቤው መልስ ይፈልጋል፡፡ በመርህ ደረጃ 12 ሳልጨርስ ጓደኛ ብሎ ነገር በጊዜው ለኔ ስህተት ነው፡፡ በዚህ ምክንያት መልሴ ሳይጠይቀኝ የታወቀ ቢሆንም የተጨነኩት ከዚህ በኋላ ምን አይነት ግንኙነት ሊኖረን ነው ብዬ ነበር፡፡ እንደፈራሁት መፈራራትና መተፋፈር ጀመርን፡፡ ቀስ እያልንም ተራራቅን፡፡
በዚህ መሃል ማን ቢቀበለኝ ጥሩ ነው….ይሄንን ሁኔታ ያየና የተከታተለ ሌላ የክፍል ልጅ ለአባቱ እንዲህ አላቸው “…ፌቨን ጐበዝ ተማሪ ትወዳለች፡፡
ወደፊት እሷን ማግባት ስለምፈልግ ካሁኑ በትምህርቴ መጐበዝ እፈልጋለሁ፡፡ ለዚህ ደግሞ እሷ የማጠናከሪያ ትምህርት የምትማርበት ቦታ አስመዘግበኝ፡፡”
ይሄን እንግዲህ አባቱ ለአባቴ “ልጅህ ልጄን ጐበዝ ልታደርግልኝ ነው” ብለው ነግረውት የሰማሁት ነው፡፡ እሱ ግን ለኔ ምንም አላለኝም ነበር፡፡ ልጅት ሆዬ ሁኔታውን መከታተል ጀመርኩ፡፡ በርግጥም ልጁ የክፍል ውስጥ ተሳትፎው ጨመረ፡፡ የቤት ስራዎችን ጠንቅቆ ይሰራ ጀመር፡፡ አባቱ የልጄ የወደፊት ሚስት ብለው ይሁን ወይ እንደ ባለውለታቸው ቆጥረውኝ ብቻ…ባገኙኝ ጊዜ ሁሉ ፍሽክ ፍሽክሽክ ብለው ሰላምታ ይሰጡኛል፡፡ ስመውም አይጠግቡኝም ነበር፡፡ ታዲያ እኔ በማየው ነገር እየገረመኝ፣ ዮሲንም እየወደድኩት፣ አባቱ እየተደሰቱ፣ ዮሲ ዓላማውን ለማሳካት መንገዱን እየጠበጠበ ባለበት ወቅት የኢትዮ - ኤርትራ ግጭት በመጀመሩ ተለያየን፡፡
ዮሲን አደንቀዋለሁ፡፡ ሚስት ሁኚኝ አላለኝም፤ ራሱን ለብቁ ባልነት ማዘጋጀት ግን ጀምሯል፡፡ እንዲህ አይነቱን ማን አይወድም? እኔ እወዳለሁ!
ዮሲ ከሄደ በኋላ ልቤን ያስደነገጠ ሳይገኝ አመት አለፈ፡፡
ኛ ክፍል ላይ እንደገና ተረታሁ፡፡ ልጁ እንደሚወደኝ ነገረኝ፤ እንደምወደው ነገርኩት፡፡  በጣም አስብለት ነበር፡፡ ትዝ ከሚሉኝና ተቃውሜውም የማላውቀው ነገር ደብተሬ ላይ እየተፈላሰፈ የሚጽፈው ነገር ነው፡፡ ሁለት ገጽ፣ ሶስት ገጽ ይጽፋል (ስለ ፍቅር፣ ስለ ይቅርታ፣ ስለ ጓደኝነት…) አልገነጥለውም፡፡ ግን ያንን ደብተሬን ለማንም አልሰጥም፡፡ ቲቸርም የደብተር ማርክ ሲሞሉ አስተውለውት አያውቁም፡፡ የ9ኛ ክፍል የCivic ደብተሬ፣ የሱን ጥራዝ ነጠቅ ሃሳቦች እንደያዘ ማን አወቀ? ከኔና ከራሱ በቀር፡፡
ዮሲ አሁን የት እንዳለ አላውቅም፡፡
ከዚህኛው ልጅ ጋር እንኳን ከብዙ አመት በኋላ ፌስቡክ ላይ ተገናኝተን አወራን፤ መለያየታችንን ኮነንን፡፡ የአንድ የቆንጅዬ ልጅ አባት ሆኖ አገኘሁት፡፡ እኔ፤ ሆዴዴዴዴን እስኪያመኝ ቀናሁ፡፡ ሚስቱ በጣም ፉንጋ ናት አይደል? “Say” አዎ በናታችሁ!
*   *   *
የመጀመሪያ ደብዳቤ የደረሰኝ 7ኛ ክፍል ሆኜ ነው፡፡ የፃፈልኝ ልጅ በጣም ቀጭን ሲሆን ስሙ ብርሃኑ ይባላል፤ ግን ሉሲ ብሬ የሚል ቅጽል ስም ነበረው፡፡ ዳር ዳሩን በአበባ ባጌጠ ወረቀት ላይ አስቂኝ ፅሁፍ ሰጠኝ “እንደ እንጀራ ለምትርቢኝ እንደ ውሀ ለምትጠሚኝ ውድ ፍቅሬ…” ይልና በመጠማትና በመራብ ዙሪያ ትንተና ይሰጣል፡፡ ከጓደኞቼ ጋር በመሆን ወር ሙሉ ሳቅንበት፡፡ እሱም ሰኔ 30 ጥርሴን እንደሚያስለቅመኝ ዝቶ ተለያየን (እኔ በጣም ወፍራም ስለነበርኩ ማች አናደርግም ብዬ ነው)
ሁለተኛ ደግሞ እዛው 7ኛ ክፍል ሁለተኛው አጋማሽ ላይ ነው የደረሰኝ፡፡ ልጁ ሰፈር፣ ትምህርት ቤት ያስቸገረ ነውጠኛ፤ በጉልበቱ የሚያምን አይነት ነበር፡፡ ደብዳቤው የተፃፈው እንደነገሩ ነው “እወድሻለሁ ስትወጪ ጠብቂኝ” ይላል፡፡ አላመነታሁም፤ ጠበቅሁት፡፡ ምን እንዳወራን ባላስታውስም ሰፈር ድረስ ሸኘኝ፡፡ የቤታችን በር ጋ ስደርስ “ጓደኛዬ ነሽ፤ ከዚህ በኋላ ከሌላ ሰው ጋር እንዳላይሽ” ኧረ ማስጠንቀቂያ! ቤት ደግሞ ጓደኛ መያዜ ከተሰማ እገደላለሁ “እኔ ጓደኛህ መሆን አልፈልግም” አልኩት፡፡ “አስቢበት” ብሎ ጥሎኝ ሄደ፡፡ ጓደኛዬን ሳማክራት፣ ቤተሰቦቼ ሳያውቁ ጓደኛ እንዳደርገው አስማማችኝ፡፡ በበነጋታው በር ላይ ጠብቆ “እእ..” አለኝ፤ ትንሽ አመንትቼ “እሺ” አልኩት፡፡ እናም በክብር ያቺን አመት ጨረስኩ፡፡ ሰኔ ሰላሳም ሳልመታ አለፈ ግን ማርያምን ምንም አላደረግንም፡፡
ተወዳጅ መኮንን
*   *   *
ስምንተኛ ክፍል ሆኜ ነው፡፡ የሰፈሬ ልጅ ደብዳቤ ፅፎ ላከልኝ፡፡ ደብዳቤውን ያመጣው ትንሽ ልጅ ነበር፡፡ በወቅቱ ለወንድ ልጅ ካለኝ ፍርሃት የተነሳ ደፋር ነበርኩ፡፡ ፍርሃት በጣም ደፋር ያደርጋል ያሉት ለካ ወደው አይደለም፡፡
የተላከው ልጅ ከቤት አስጠርቶኝ “ለእሷ ብቻ ስጥ” ተብሏል መሰለኝ፣ ደብቆ ሰጠኝ፡፡ ገለጥ አድርጌ ሳየው ገባኝ፡፡ የልብ ቅርፅ ተስሎበታል፡፡ በአረንጓዴና በቀይ እስክርቢቶ በሚያምር የእጅ ፅሁፍ ተጽፏል፡፡ (የልጁ እጅ ፅሁፍ ማማር እራሱ ግርም ይለኛል) የወረቀቱ አስተጣጠፍ እንኳን በጣም ልዩ ነበር፡፡
በአንዴ ከድንጋጤም ድፍረትም ከየት እንደመጣ እንጃ! (አትንኩኝ ነው ነገሩ) ወረቀቱን አጣጥፌ ብጭቅ ብጭቅ አደረግሁትና፤ (ውይ ክፋቴ)
“ሲርብህ ብላው ብላሃለች በለህ” ብዬ መልሼ ሰጠሁት፡፡
አቤት…ከዚያ ወዲያ አኔም ሳላናግረው፣ እሱም ቀና ብሎ ሳያየኝ፣ ከዚያ ሰፈር ወጣሁ፡፡ በጣም ትልልቆች ሆነን እንኳን አላናግረውም ነበር፡፡
ሁለተኛውና የመጨረሻው 9ኛ ክፍል ስማር በዕረፍት ሰአት ደብተሬ ውስጥ ያገኘሁት፣ ማንነቱንና ምንነቱን ያልገለፀ ሰው በሙንጭርጭር ጽሑፍ የፃፈልኝ ደብዳቤ ነው፡፡ “መነን ት/ቤት መታጠፊያው ላይ ጠብቂኝ” የሚል ቀጠሮ ሁሉ ነበረው፡፡ (ማን እንደሆነ ሳይታወቅ!) ወይ ጊዜ፤ እንዴት ይሮጣል!
ሮሚ
*   *   *
የደረጃ…የስፔሻል ክላስ ተማሪ…ማፍቀር መፈቀር የማይታሰቡ ነገሮች…መሸ ነጋ ደብተሬ ላይ የምቸከል…ስለ ፍቅር ሲወራ “እኔ አላማ አለኝ፤ እንዲህ አይነት ነገር አላደርግም” ምናምን የምል… አካባጅ ነበርኩ፡፡ ከመምህሮቼ ጋር ጥብቅ ግንኙነት ስላለኝ ተማሪዎችም ደፍረው አይቀርቡኝም፡፡ እና ደብዳቤ ምናምን አልተጻፈልኝም (አሁን ቆጨኝ!)
ሁሌም አመሻሽ ላይ ከእህቶቼ ጋር የሃይማኖት ትምህርት ለመከታተል ቤተክርስቲያን እንሄዳለን፡፡ ትምህርት አልቆ ማታ ወደ ቤት ስንመለስ፣ ከመድሃኒያለም እስከ ሃያ ሁለት ጫፍ ዎክ እናደርጋለን፡፡ (በዚያ መስመር ብዙ ሰው ዎክ ያደርጋል) አንዳንዴ የማንገዛውን ቡቲክ ገብተን እንጠይቃለን… ሃሃሃ…
እዚያ አካባቢ የቀበሌ መዝናኛ ፑል ቤት አለ፡፡ ሁሌ በር ላይ የሚቆሙ ፍንዳታዎች ነበሩ፡፡ አንደኛው ላይ አይኔ አረፈና ተከየፍኩበት፡፡ ታዲያ የማየው ከሩቁ ነው፡፡ ቁመናውን እንጂ ጠጋ ብዬ ፊቱን አይቼው አላውቅም፡፡ እሱም በጨለማ ነው፡፡ በመንገድ መብራት ድብዝዝ ብሎ ነበር የሚታየኝ፡፡ ቆንጅዬ፤ ጠይም እንደሆነ ያስታውቃል፡፡ ዛሬ ፊቱን ማየት አለብኝ ብዬ ከሩቅ አስቤ እሄድና ልክ መቶ ሜትር ሲቀኝ አንገቴን አቀረቅራለሁ፡፡ ድፍረቴ ኦና ይሆናል፡፡ መቼም አጠገቡ ቆሜ እንደማላወራው አውቀዋለሁ፡፡ በሩቁ ብቻዬን ነበር ያፈቀርኩት፡፡ ለእህቶቼም እንኳን አልነገርኩም፡፡ አንድ ቀን ብቻዬን ወደ ቤተክርስትያን ስሄድ ከኋላዬ ደረሰብኝ፡፡ ነፍሴ ተርበተበተች፡፡
“ሃይ… ሰላም ነው” አለኝ ስሜን ጠርቶ፡፡ ስሜን መጥራቱ ቢያስደስተኝም አንደበቴ ተለጉሞ ዝም አልኩት፡፡
“ከኋላ በጣም ታምሪያለሽ” አለ፤ ቀጠለና፡፡ አስቀያሚ ብሎ የሰደበኝ መሰለኝ፡፡ ተናደድኩበት፡፡
“እንትን ጋራጅን ታውቂዋለሽ? እዛ ነው ምሰራው” አለኝ
“እግር ኳስ ተጫዋችና ጋራጅ ሰራተኛ እወዳለሁ” አልኩት፡፡ በኋላ “ለምን አልኩት” ብዬ ፀፀተኝ፡፡
“እንትናንስ ታውቂዋለሽ?” (ባለጋራጁን ማለቱ ነው)
“እንጃ ብዙ አላውቀውም” አልኩት፡፡
“ስልክ ቁጥሯን ተቀበልልኝ ብሎ ነው”
“ይሄ ትልቁ ሰውዬ?” አልኩት ድንገት በመገረም፡፡
“ኧረ ትልቅ አይደለም፤ አንቺ ስለማታውቂው ነው፡፡ ስልክ ከሌላት እኔ እገዛላታለሁ ብሏል…” ለድለላ ስራ እንደመጣ ሲገባኝ ኩምሽሽ አልኩ፡፡ አግኝቼ ያጣሁት መሰለኝ፡፡
አጋጣሚ እየጠበቀ ያናግረኝ ጀመር፡፡ እኔም እሱን ለመሳብ ይረዱኛል ያልኳቸውን ፍልስፍናዎች አዘንብበት ጀመር፡፡ ስለ ሰውየው ትተን፣ ስለ ራሳችን ማውራት ጀመርን፡፡
“እነንትና እኮ ዱሩዬ ናቸው፤ ለምን ከነሱ ጋ ትቆማለህ?” እለዋለሁ፡፡ ቀስ እያለ ያስረዳኛል፡፡
“አስፓልቱ ሰው ይበዛበታል… ውስጥ ለውስጥ እንሂድ” እያልን ከህዝብ ተገንጥለን ለብቻችን መሄድ ጀመርን፡፡ ቀጥሎ አንገትና ወገብ ተቃቅፎ መሄድ መጣ፡፡
እያለ …እያለ…እያለ… ሃሃሃ… ይበቃችኋል፡፡
*   *   *
የመጀመሪያው የፍቅር ደብዳቤ የደረሰኝ 5ኛ ክፍል እያለሁ ነበር፡፡ ስሙን የማልጠቅሰው፤ በረባሽነቱና ተጫዋችነቱ በጣም የሚታወቅ የክፍሌ ልጅ ነበር፡፡ በጣምም ደፋርና ጆሊ ነገር ነበር፡፡ የክፍላችን ወንዶች በሙሉ ጓደኞቹ ነበሩ፡፡ ትምህርት ቤታችን ውስጥ እሱን የማያውቅ ተማሪ አልነበረም፡፡ እናቱም አስተማሪያችን ነበሩ (ለድፍረትና ረብሻው አግዞት ይሆናል)
የሆነ ሆኖ አንድ ቀን “የቤት ሥራ አልሰራሁምና ደብተርሽን አውሽኝ” ይለኝና ደብተሬን ሰጠሁት፡፡ እኔ ደግሞ አታምኑኝም ይሆናል እንጂ ያኔ በጣም አይናፋርና ዝምተኛ ነበርኩ፡፡ ደብተሬን ከትምህርት ስንለቀቅ ግቢው በር ላይ ጠብቆ መለሰልኝ፡፡ እቤት ደርሼ ደብተሬን ስገልጥ፣ ዳር ዳሩ ላይ በአበባና ቢራቢሮዎች ያጌጠ፣ ሽቶ ሽቶ የሚሸት ወረቀት አገኘሁኝ፡፡ ከልጁ የተፃፈልኝ የ“እወድሻለሁ” ደብዳቤ ነበር፡፡ የተፃፉትን እያንዳንዱን ቃላት አላስታውሳቸውም፡፡ አንብቤው ለእህቶቼዋ አስነበብኩት፤ ለጓደኛዬም፡፡
ጓደኛዬ፤ “ታዲያ ምን ብለሽ ልትመልሽለት ነው? እሽ እንዳትይው፣ ረባሽ ነው፤ ከፈለግሽው ግን ይሁን” አለችኝ፡፡ መመለስ እንደሚገባኝ እራሱ አልገባኝም ነበርና ዘጋሁት፡፡ ልጁ በሶስተኛ ወይ በአራተኛ ቀን የተቀመጥኩበት ዴስክ ጋ መጥቶ “ምነው ደብዳቤዬን ሳትመልሽልኝ?” ብሎ ሲጠይቀኝ “አልፈልግም፤ ይኸው ደብዳቤህ” ብዬ ሰጠሁት፡፡ “እምቢ አልሽ አይደል፣ ቆይ ብቻ ሰኔ 30 ላግኝሽ” ብሎ ፎከረብኝ፡፡ እንዳለውም ሰኔ 30 ከጓደኞቹ ጋር መንገድ ላይ ጠብቆ እየፎከረ ሊመታኝ ሲያስፈራራኝ፣ እህቶቼና ጓደኛዬ ደፈር ብለው፣ ተለማምጠውና አባብለው ከመደብደብ አስጥለውኝ ነበር እላችኋለሁ፡፡
ሜሪ ፈለቀ



Saturday, 22 November 2014 12:39

የፀሃፍት ጥግ

 ጥሩ ተራኪ ግሩም የማስታወስ ችሎታ ያለውና ሌሎች የላቸውም ብሎ ተስፋ የሚያደርግ ነው፡፡
አይርቪን ኤስ. ኮብ  (አሜሪካዊ ተረበኛና ጋዜጠኛ)
* በስኬት ሱስ ሙሉ በሙሉ ተይዣለሁ፡፡
ስቲንግ
(እንግሊዛዊ የሮክ አቀንቃኝና የዘፈን ግጥም ፀሐፊ)
* ከምሠራው ነገር ጀርባ ሁሉ የዓይን ጥቅሻ አለ፡፡
ማዶና (የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝና የፊልም ተዋናይ)
* ግጥም የተመጠነ ንግግር እንደሆነው ሁሉ ዳንስም የተመተረ እርምጃ ነው፡፡
ፍራንሲስ ቤከን (እንግሊዛዊ ፈላስፋ፣ በሳል ፖለቲከኛና የህግ ባለሙያ)
* ሙዚቃ ማቀናበር ከመጪው ዘመን ጋር በፍቅር እንደመቅለጥ ነው፡፡
ሉካስ ፎስ  (ትውልደ ጀርመን፣ አሜሪካዊ  አቀበናባሪ፤  ኮንዳክተርና ፒያኖ ቀማሪ)
* ጎበዝ አቀናባሪ አይኮርጅም፤ ይመነትፋል እንጂ፡፡
አይጎር ስትራቪንስኩ
(ትውልደ ሩሲያ አሜሪካዊ አቀናባሪ)
* ሁሉም ሰው መማር ከመጀመሩ በፊት አርቲስት ነው፡፡ ሁሉም ሰው መማር ካቆመ በኋላ አርቲስት ይሆናል፡፡
ታባን ሎ ሎዮንግ (ሱዳናዊ ገጣሚና ደራሲ)
* እግዚአብሔር ምድርን ፈጠረ በሰባተኛው ቀን ግን እረፍት ላይ ሳለ፣ ድንገት ተነሳና እንዲህ አለ፡፡
ሁሉንም ነገር ፈጥሬ ረሳሁ ሁለት ነገሮች  የፒካሶን አይንና እጆች
ራፌል አልበርቲ  (ስፔናዊ ገጣሚ)
* ታላላቅ የሙዚቃ ቀማሪዎች ታላላቅ መንታፊዎች እንደነበሩም አንርሳ፡፡ ከማንም ከየትም ሳይሉ ዘርፈዋል፡፡
ሰፓብሎ ካሳልስ (ሙዚቃ ቀማሪ)
* እብደትን በጥቂቱ መሞከር ሰዓሊን
አይጎዳውም፡፡
አዩ ክዌይ አርማህ (ጋናዊ ፀሐፊና የትምህርት ሊቅ)
* የእኔ ስራ የማውቀውን መሳል አይደለም፤ የማየውን እንጂ፡፡
ጄ.ኤም.ደብሊው ተርነር (እንግሊዛዊ ሰዓሊ)

በቅርቡ ለገበያ የዋለው የዕውቁ ድምፃዊ አብነት አጎናፍር “አስታራቂ” የተሰኘ አልበም ከትላንት በስቲያ ዝነኛ አርቲስቶች፣ ተጋባዥ እንግዶች፣ የአርቲስቱ ወዳጆችና አድናቂዎች በተገኙበት ተመረቀ፡፡ የአብነት “አስታራቂ” ሦስተኛው አልበሙ ሲሆን 14 ዘፈኖች ተካተውበታል፡፡  

በደራሲ ደሞዝ ጐሽሜ ተፅፎ ለንባብ የበቃው “ሶስተኛው ኪዳን” ልብወለድ መፅሀፍ ትናንት ምሽት በብሔራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ተመረቀ፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ በሐምሌ 2003 ዓ.ም የታተመው መጽሐፉ፤ ሁለተኛው እትም ባለፈው መስከረም የወጣ ሲሆን ጭብጡ በኢትዮጵያ መንፈሳዊ ስልጣኔ ላይ የሚያጠነጥን ነው ተብሏል፡፡
በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ የመጽሐፍ ዳሰሳና ውይይትም ተካሂዷል፡፡ የምርቃት ሥነስርዓቱን ያዘጋጀው ኢጋ ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን እንደሆነ ታውቋል፡፡

Saturday, 22 November 2014 12:33

ማህሌት

የሆነ ያልገባው ነገር አለ፡፡ ስለ ህይወቱ? … ስለ እናቱ? በተለይ ስለ አባቱ? … በጥቂቱ ደግሞ ስለ ትምህርቱ፡፡ እንደ ድሮው አይደለም እሱነቱ፡፡ “ኤሊየን” ስለመሆኑ እንደ ድሮው ከዚህ ስምንት አመት በፊት አያምንም፡፡ እንኳንስ… አፍ አውጥቶ መናገር፡፡
የአስራ አንደኛ ክፍል ትምህርት እንደሚወራለት ከባድ አይደለም፡፡ ትንሽ አስተማሪዎቹ የሚሉትን መስማት ብቻ ነው የሚጠበቅበት፡፡ ደብተር ይዞ አያውቅም፡፡ አስተማሪ ተብዬዎቹ የሚያወሩትን ሰምቶ ፈተና በተባለው ወረቀት ላይ ሲደግምላቸው ይደሰታሉ፡፡ ሲደሰቱ “አንደኛ” ወጥተሃል ይሉታል፡፡
ዘጠነኛ ክፍል እያለ እንደዚያ አስደስቷቸው ነበር፡፡ አመቱን ሙሉ እነሱ የሚሉትን እንደ “ፓሮት” ደገመላቸው፡፡ አመቱን ሙሉ፡- ማለትም ሁለት ሴሚስተር ያህል “አንደኛ” ነህ አሉት፡፡ “አንደኛ” እና “አንተ ነህ” አሉት፡፡ ስሙ እና እውነተኛ ማንነቱ የጠፋው ሲመስለው፤ አስረኛ ክፍል አስተማሪዎቹ የሚሉትን መድገም አቆመ፡፡ “አንተ አይደለህም” ቢሉትም  አልጣሉትም፡፡ “ወደቀ” ብለው አሾፉበት እንጂ ሰርተፍኬቱ ላይ “ወደቀ” ብለው አልፃፉበትም፡፡
ዘጠነኛ ክፍለ ፊት ወንበር መጀመሪያ መደዳ ነበር የሚቀመጠው፡፡ አስረኛ ክፍል መጨረሻ መደዳ ተቀምጦ “ሮበርት ሉድለምን” እያነበበ፣ በደረጃ መጨረሻ እየወጣ አመቱን ጨረሰ፡፡ መጨረሻ መደዳ የሚቀመጡት ፊት የሚቀመጡትን እንደ “ባንዳ” እንደሚቆጥሯቸው የተረዳው ከእነሱ መሀል ሲቀመጥ ነበር፡፡ ፊት ወንበር የሚቀመጡት ኋላ ያሉትን ምን ብለው እንደሚጠሯቸው ግን በመሀላቸው ሳለ አልነገራቸውም፡፡
ከኋለኛው መደዳ ረድፈኞች ወደ አስራ አንደኛ ክፍል ያለፉት የተወሰኑት ናቸው፡፡ ከተወሰኑት መሀል ማህሌት አንዷ ናት፡፡ በመጀመሪያው ሴሚስተር ከሮበርት ሉድለም መፅሐፍ ማህሌትን ወደ ማጥናት አደገ፡፡ የእሷን ትኩረት ለመሳብ ሲል መሆን አለበት… ኋላ መደዳ ተቀምጦ ፊት ተቀማጮቹ የሚታሙበትን ነገር ማድረግ ጀመረ፡፡ ማጥናት፤ በአጭር ቋንቋ አስተማሪው የሚያዘውን ሁሉ ማድረግ፡፡ የሚደግመውን መድገም፡፡ ተመልሶ ፓሮት ሆነ፡፡
አስተማሪዎች ይገርሙታል፡፡ እነሱ ያሉትን ሁሉ አንድ ሳያስቀር ኮፒ አድርጎ የሚገለብጠውን ልጅ የፈተና ወረቀት ሲያርሙ፣ የእስክሪብቷቸው የቀይ ቀለም ጭነት ራሱ ይለሰልሳል፡፡ የሚወዱትን ልጃቸውን ጭንቅላት የሚያሹ ነው የሚመስሉት፡፡ “መቶ ከመቶ”፣ “ስልሳ ከስልሳ”… “ኤክሰለንት”… በ“Very Good” እና በ“Excellent” መትረየስ ወረዱበት፡፡ “አንተ ነህ” አሉት፡፡
ከማህሌት ጋር ለመተዋወቅ ቀላል ነበር፡፡ ያው ምክኒያት አያስፈልግም፡፡ “እቺን ነገር አሳየኝ!” “ያቺን ነገር አሳየኝ?”…
ስሙ አስተማሪዎቹ እንደሚጠሩት “አንተ ነህ” ሳይሆን...፣ ሚልኪ እንደሆነ አስረግጦ ነገራት፡፡ የተለያየ ቦታ፣ የተለያዩ ሰዎች የሚያወጡለት ስም እንዳለ ግን ደበቃት፡፡ የዛሬ አስር ዓመት ገደማ በነበረበት ሰፈር “Ace” እያሉ እንደሚጠሩት፣ ጥሪውን ግን ሰፈር ሲቀይር እንደተለወጠ መናገር ዋጋ የለውም፡፡ አባቱ የሚጠራው ስምም አለ፡፡ መውደድ ሰጥቶ መቀበል ነው፡፡ አይን ስለ አይን፣ ጥርስ ስለ ጥርስ፡፡
አሁን ከማህሌት ጋር ሚልኪ በሚለው ስሙ ነው መቀራረብ የፈለገው፡፡ መታወቂያው ላይም ስም አለው፡፡ በሱም ስም ሰዎች ይጠሩታል፡፡ ሁሉንም ጥሪ አቤት ብሎ ይቀበላል፡፡ ከነብሱ አንደበት ራሱን የሚመራበትን ስም ግን በአፉ ለራሱ እንኳን ቢሆን ጮክ ብሎ አይደግምም፡፡ ጉልበቱ የት እንደሚገኝ እንደ መግለፅ ይመስለዋል፡፡ ሳምሶን ጉልበቱን ፀጉሩ ላይ አስቀምጦ፣ ፀጉሩ እንደ በግ ሲሸለት፣ በግ እንደመሰለው …. እሱም ስሙን ምላሱ ላይ አስቀምጦት፣ ምላስ ያላቸው ሁሉ በእሱ ጉልበት እጣ ፈንታቸውን እንዲሸከሙ አይፈቀድላቸውም፡፡
ከማህሌት ጋር ተግባባ፡፡ ከማህሌት ጋር ሲቀራረብ፣ ከራሱም ማንነት ጋር ሆነ፡፡ አስተማሪዎች ማን እንደሆነ እየደጋገሙ ከሚደሰኩሩለት ራቅ ያለ ሶስተኛ ማዕዘን ላይ የተቀመረ መሆኑ ለራሱ ይሰማዋል፡፡ ቢሰማውም ይሄንን ሶስተኛ ማንነቱን ወደደው፡፡ ከወትሮው የሦስት መአዘን አቋሙ ጋር የሚስማማ ነገር ስላለው፡፡
በፊት እናቱ ከአባቱ ጋር አንድ ላይ በሚኖሩበት ጊዜ፣ እሱ የእናቱንም ሆነ አባቱን ወይንም አባቱ እሱን እንደሚያየው ወይንም እናቱ እሱን በምታየው አንፃር ራሱን ተመልክቶ አያውቅም፡፡ ሁሌም ሶስት መአዘን ይይዛል፡፡
በዚያ የልጅነት ዘመን ጎረቤቱ ያሉት እዮብ እና ናትናኤል ምርጥ ጓደኞቹ ነበሩ፡፡ ሁለቱም እሱን እንደሚያዩት .. የራሱን እይታ አመቻችቶ አያውቅም፡፡ የእዮብ እና የናትናኤል አባት ኢንጂነሩ በጣም ያደንቁት ነበር፡፡ “Ace” የሚለውን ለእነሱ እይታ የሚሆን ስም አውጥተው እንዲፀድቅ አድርገዋል፡፡ እነሱ እሱን እንደሚያዩት እንጂ እሱ እነሱን መልሶ እንደሚያያቸው… በማየት እና በመታየት መሀል ትልቅ ክፍተት እንዳለ አይገነዘቡትም ነበር፡፡ እነሱ እሱን ለመካብ የሚሰጡትን ስም እንጂ እሱ እነሱን ለማድነቅ ያወጣላቸውን ስያሜ አያውቁትም፡፡ እነሱ በሚያዩበት አለም ሁሉንም ብያኔ ለመስጠት የሚያስችል ንግስና እንዳላቸው፣ እሱም በራሱ ዓለም ውስጥ ለሚታዩት ነገሮች ብያኔ የመስጫ ልዕልና መጎናፀፉ ይረሳቸዋል፡፡
ከማህሌት ጋር ሲሆን አፍቃሪ እና ተፈቃሪ … ከመምህሮቹ ጋር ሲሆን ተማሪና አስተማሪ … ከእናቱ ጋር ሲሆን በአንድ ጊዜ ልጅ እና ወላጅ መሆን እንደሚችል ማንም አይገነዘብለትም፡፡ አብዛኛው ሰው የሚታየው አሀዳዊ መንገድ ብቻ ነው፡፡ የራሱ መንገድ፡፡ የራሱ ፍላጎት መንገድ፡፡ ኤስ ግን ሶስት መንገድ በአንድ ጊዜ ይታየዋል፡፡
በማህሌት ላይ የሚያየው መንገድ የዚህን ባህርይ የተላበሰ ነው፡፡ አንደኛው መንገድ እሱ እሷን ለማፍቀር፣ ጓደኛ ለመሆን፣ አብሮ ለመሰንበት የሚያሳየው ፍላጎት የሱ ፈቃድ ነው፡፡ ሁለተኛው ማህሌት ከሱ የምትፈልገው፣ እንዲሆንላት የምትመኘው፣ የሷ እምነት፣ እሱን በመቆጣጠር የሚፈጠረው መንገድ ነው፡፡ ሶስተኛው ከሁሉም ውጭ የሆነው ነው፡፡ ሁሉንም መሆን እና አለመሆን በአንድ ላይ የሚችለው መንገድ ነው፡፡ ይህ መንገድ እንደ እውነተኛው ስሙ እውነተኛው “ህቡዕ” ምንነቱ አድርጐ ይቆጥረዋል፡፡
የማህሌት መንገድ እና የእሱ መንገድ፤ ከዚያ ሶስተኛው መንገድ፡፡ ማህሌትን እያስጠናት እሱ ደግሞ እሷን ያጠናት ጀመር፡፡ እሷም እያጠናች እንደምታጠናው ያውቃል፡፡ ሁለቱንም ጥናቶች ከውጭ ሆኖ ሶስተኛው መአዘኑ ላይ ይቆምና ይከታተላል፡፡ ሲከታተል አስተማሪዎቹን፣ ተማሪዎቹን እናቱን፣ ህይወቱን አንድ ላይ ጠቅልሎ ነው፡፡
የማህሌትን ውጤት ዝቅ ካለበት ከፍ ሲል እያየ፣ የራሱን ከፍ ካለበት እንዲወርድ ፈቀደ፡፡ የአስተማሪዎቹ እይታ ስለሱ ወይንም ስለሷ …  ስለ እሷና እሱ መርገብገቡ ከማይርገበገበው መአቀፋዊ ምዘናው ላይ ሆኖ እንደገና ይለካል፡፡
ከአስተማሪዎቹ መሀል አንደኛው… ግጭት ለመፍጠር ከመንጋው መምህርነት ወጥቶ ወደነሱ ግንኙነት ተጠጋ፡፡ አስተማሪው የባይሎጂ ትምህርት የሚሰጥ ብቻ ሳይሆን ለትምህርቱ ሰውየውም የተሰጠ መሆኑ በስፋት ይነገርለታል፡፡ የሚነገርለትን ያለ ይሉኝታ ከመናገርም ሰውየው ራሱ አይቦዝንም፡፡ ለትምህርቱ ባሳየው ተነሳሽነት ብዙ ሽልማቶችን ሰብስቧል፡፡ ባዮሎጂ ህይወትን የሚያጠና በመሆኑ፣ አስተማሪው ከህይወት አይነቶች መርጦ ቆንጆ ሴቶችን መመርመር ይወዳል፡፡ የወደደውን ይመረምራል፡፡ ማህሌት የቆንጆ ሴቶችን መስፈርት የምታሟላ “እስፒስመን” ናት፡፡
በተሰጠው ክፍለ ጊዜ በጥቁሩ ሰሌዳ ላይ የሚፅፈውን ፅፎ ወይንም የሚያብራራውን አብራርቶ … ትንፋሽ ለመውሰድ የሚያመራው ወደ ማህሌት አቅጣጫ ነው፡፡ ደብተሯን ያገላብጣል፡፡ ደብተሯን በእጁ፣ መልኳንና ተክለ ሰውነቷን በአይኑ፡፡ ስህተት ሊያገኝባት ይታትራል፡፡ የሚፈልገውን ባያገኝም በአለባበሷ ላይ እንደ አባት ይሆንና ተግሳፅ ይሰጣል፡፡ እንደ አባት የጀመረው ምክር እንደ አጎት ይመስልና እንደ መሸታ ቤት ተስተናጋጅ ሆኖ ይጨርሳል፡፡ በተለያየ ጊዜ ቢሮ ጠርቷት ከባዮሎጂ ጋር በጣም ስለሚገናኙ የፆታዊ ባህሪዎች በጥያቄ መልክ አቅርቦለታል፡፡ አቅርቦልኛል ብላዋለች ኤስን፡፡
ሰው ሰማም አልሰማም፣ ሰውየው ለልጅቱ አንዳች ጥላቻ አለው፡፡ ተንጠራርተው የሚደርሱበትን ነገር እንደሚጠሉ ሰዎች ይመስላል… ማህሌትን ሲያያት የሚያሳየው መንገሽገሽ፡፡
“ንፍጥ” የሚል ስድብ ወደሷ አቅጣጫ ይሰነዘራል፡፡ የባዮሎጂ ተራ አስከባሪ በመሆኑ፣ ለትምህርቱ አምልኮት ያላቸው የፈተናውን ወንዝ ለመሻገር ይስቁለታል፡፡ ኤስ በዚህ ሁሉ ውስጥ የተመልካች ስፍራውን ይዞ ይታዘባል፡፡ መታዘብ ባበዛ ቁጥር ለምን ወደ አንዳች አቅጣጫ እያደገ መሆኑ እንደሚሰማው ለራሱም ማስረዳት አይችልም፡፡
ከእለታት በአንዱ ቀን በሰሌዳው ላይ የተለቀለቀውን ጽሑፍ ተማሪዎቹ እንደ እርግብ በእስክሪብቶው መንቁራቸው እየለቀሙ ሳሉ… እህሉን ያፈሰሰላቸው መምህር ወደ ማህሌት መቀመጫ ሄዶ፣ እለታዊ ጉንተላውን አከናወነ፡፡ በመቀጠል ነጭ ጋውኑን አንዘርፍፎ ከእሷ አንድ ረድፍ በቀደመው ወንበር ላይ ተቀምጦ፣ አስተማሪው የራሱን ጽሑፍ በተማሪ አይን ከኋላ ሆኖ መገምገም ጀመረ፡፡
ኤስ እንደ ሌሎቹ የተፃፈለትን ሁሉ አይለቅምም፡፡ ከሮበርት ሉድለም ወደ ጄምስ ካለቬል ድርሰት አድጓል፡፡ “ሾ ጋንን” እያነበበ ነው፡፡ አስተማሪው ሲያነብ ያየዋል ግን አይተናኮለውም፡፡ “አንተ ነህ” የሚለው ማዕረጉ፣ የሌላው ተማሪ ግዴታ እንዳይመለከተው መንገድ ሰጥቶታል፡፡ ግን ይህ የባዮሎጂ መምህር ስህተት ቢያገኝበት ሊጥለው እንደሚፈልግም ያውቃል፡፡ ከመከባበር ይሁን… ከመገማገም የመጣ መፈራራት በመሃላቸው ሰፍኗል፡፡ ኤስ ከማህሌት ጐን መቀመጡ የአስተማሪው የቀድሞ ፍቅር ወደ “ቆይ ጠብቅ” ሲቀየርበት ይታወቀዋል፡፡
ኤስ እና ማህሌት ከተቀመጡበት መደዳ ፊለፊት የተዘረፈጠው የባዮሎጂ አዋቂ በፈዘዘበት አንድ ነገር ተከሰተ፡፡ ኤስ ልጅ በነበረበት ወቅት አንድ ነገር ከመከሰቱ ጥቂት ቅጽበት ቀደም ብሎ የሚከሰተውን ነገር ያውቀው ነበር፡፡ ለምሳሌ አስተማሪ በሰሌዳው ላይ የሚያሰፍረውን ጽሑፍ ጥቂት ቀደም ብሎ ሰፍሮ ይታየው ነበር፡፡ ግን ይህ ችሎታውን ሳያዳብረው፣ ከሰው ተወራርዶ ሳይረታበት፣ በራሱ ውስጥ እንደያዘው እድሜው ከፍ እያለ ሲመጣ ቀስ በቀስ ችሎታው ጠፋበት፡፡
ጠፍቶበት ቆይቶ ልክ በዛች ቅፅበት አስተማሪው ከፊለፊቱ የእነሱን ዴክስ ተደግፎ በተቀመጠበት፣ ያ የተዘነጋ ችሎታው ድንገት ተከሰተለት፡፡ ማህሌት ቀጥላ የምታከናውነው ተግባር ታየው፡፡ ታየው፤ ግን ነገሩን ከመከሰት ለማቆም ምንም እርምጃ አልወሰደም፡፡ ሶስተኛው መአዘን ላይ ያቆመው ዋነኛው ሚዛን፣ የተከሰተውን ተግባር መግታት ይችል የነበረውን የእሱን እጅ ከውስጥ ያዘበት፡፡ Kay sera sera
ማህሌት ከሰሌዳው ላይ መገልበጧን ድንገት አቆመች፡፡ በፈጣን ትልልቅ ፊደል ለአስተማሪው እንዳይሰማው አድርጋ፣ ከጀርባ በነጩ ጋውን ላይ “የሰው ንፍጥ” ብላ ፃፈች፡፡
*    *    *
የትምህርት ጊዜ አለቀ፡፡ ሰውየውም የእውቀት ማቀበያ መሳሪያዎቹን (ቾክ እና ዳስተር) አንከብክቦ ወደሚቀጥለው ክፍሉ አመራ፡፡
ተቀያሪው አስተማሪ አንድ እግሩ አጠር የሚል፣ ጮክ ባለ ድምጽ የአማርኛን ሰዋሰው የሚያስጨብጥ ሰው ነበር፡፡ አስጨብጦ ሲጨርስ ረዘም ካለው እግሩ አጠር ወዳለው ወርዶ እረፍት ይወስዳል፡፡ መናገር ሊጀምር ሲል እንደገና ከአጭሩ ወደ ረጅሙ ይወጣል፡፡ ሁሉም አስተማሪዎች ቅጽል ስም አላቸው፡፡ ቅጽል ስሞች በአብዛኛው የሚወጡት ፊት መደዳ ከሚቀመጡት ተማሪዎች አይደለም፡፡ ጭቆና ከላይ ወደ ታች እንደሚበረታው፣ ቅጽል ስም ደግሞ ከታች ወደ ላይ የሚስፈነጥር ፍላፃ ነው፡፡ ፍላፃው ግን በተወረወረበት አካል ጆሮ ውስጥ ብዙውን ጊዜ አይገባም፡፡ እኩል እግር የሌለውን አስተማሪ “ሲትሮይን” በሚል ስም ነው ኋለኞቹ የሚጠሩት፡፡
ሲትሮይን፤ ትምህርቱን አስተላልፎ ለማብቃት ሁለት የቁመት ማጠር እና የማስረዘም ያህል ጊዜ ሲቀሩት፣ የክፍሉ በር በእርግጫ በመሰለ ሀይል ተመትቶ ተከፈተ፡፡ የባዮሎጂው መምህር የሹራብ ሰደርያ እና ጉርድ ሸሚዝ እንጂ ነጩን ጋውን አልለበሰም፡፡
ነጩ ጋውን እንደ ኤግዚቢት በዩኒት ሊደሩ እጅ ተይዟል፡፡ ዩኒት ሊደሩ በጣም ረጅምና በጣም ጥቁር አስፈሪ ሰው ነው፡፡ እውቀት ባያንሰውም ችግርን በዱላ በማስከበር ተፈሪነትን ያተረፈ ሰው ነው፡፡ ከዱላ ላለፈ እንቢ ባይነት… (ለምሳሌ ሌባ) ሽጉጥ አውጥቶ ሲያባርር ያዩ ተማሪዎች፣ በዚያች ቅጽበት እዚያው ክፍል ውስጥ ነበሩ፡፡
ነጩ ጋውን በሰሌዳው አናት ላይ ግማሽ በተመታች ሚስማር ላይ ተሰቀለ፡፡ ዩኒት ሊደሩ ወደ ኤግዚቢቱ እጁን እየቀሰረ…
“ማን ይሄንን ጽሑፍ እንደፃፈ ሳታወጡ…ትምህርት በዚህ ክፍል አይቀጥልም፡፡ አሁን እዚሁ ይሄንን የፃፍክ ግለሰብ ራስህን ካጋለጥክ፣ ግለሰቡ ብቻህን ከዚህ ትምህርት ቤት ትወጣለህ፡፡ ካልሆነ ሁላችሁንም አንድ ላይ…”
ተጠበቀ፤ ማንም መናገር አልቻለም፡፡ ለወትሮው አይኑ ከማህሌት ላይ የማይነቀለው ባዮሎጂ መምህር ወደ ማህሌት አቅጣጫ ለቅጽበት እንኳን አልተመለከተም፡፡ ማህሌት በጠረጴዛው ስር የኤስን እጅ ጭምቅ አደረገችው “ጉዴ ፈላ” ማለቷ ይሁን ወይንም “ከዚህ አውጣኝ” ግልጽ አልሆነለትም፡፡
የተማሪው አፍ ነጭ ሆኗል፡፡ ትምህርት ማለት እውቀት ብቻ ሳይሆን የህልውናም ብቸኛ መንገድ ነው፡፡ ከትምህርት ቤት መባረር ማለት ከምድረ ገጽ መሰረዝም ማለት ነው፡፡ አይኖች በጥርጣሬ እርስ በራስ ተያዩ፡፡ ባዮሎጂ አስተማሪው ሌላ ክፍል እንዳልተፃፈበት ሲትሮይን ለሚባለው አስተማሪ ማስረጃ እየጠቀሰ ነው፡፡
“አታወጡም?” ለመጨረሻ ጊዜ ዩኒት ሊደሩ ጠየቀ፡፡ መልስ ጠፋ፡፡ የሰዉ ፊት ሁሉ የጦጣ መስሏል፡፡
“የሁላችሁም የአማርኛ ደብተር ሰብስቡ” አለ ዩኒት ሊደሩ፡፡ ኤስ የአማርኛ ደብተሩ እንደ መጽሐፍ ንባቡ ባይገፋለትም የራሱን ደብተር ከላይ፣ የማህሌትን ከስር አድርጐ አስረከበ፡፡ ማህሌት በጠረጴዛው ላይ ተደፍታ እያለቀሰች ነው፡፡ እያለቀሰች ስለነበረች፣ ሚልኪ በደብተሮቹ ላይ የሰራውን ነገር አልተመለከተችም፡፡
ክፍሉ ተዘግቶ እያንዳንዱ ደብተር በጋውኑ ላይ ከሰፈረው እጅ ጽሑፍ ጋር በጥንቃቄ እየተመሳከረ ተመረመረ፡፡ ዩኒት ሊደሩ፣ ባለ ጥቃቱ ባዮሎጂ አስተማሪ እና ሲትሮይን ለብዙ ፔሬዶች ተማሪው ባለበት ደብተሮቹን ሲያተራምሱ ቆዩ፡፡ በስተመጨረሻ አንድ ደብተር ነጥሮ ወጣ፡፡ ሦስቱም አስተማሪዎች ወንጀለኛው የዚያ እጅ ጽሑፍ ባለቤት መሆኑን መቶ ፐርሰንት ተስማሙበት፡፡ የተማሪው ስም ተነበበ፡፡
ኤስ ስሙ እስኪጠራ አልጠበቀም፡፡ ዝግጁ ሆኖ ነበር፡፡ “አቤት” ብሎ ተነሳ፡፡ የማህሌት ፊት ምን እንደሚመስል ለማየት መጓጓቱ ለእሱ ብቻ ነው የሚታወቀው፡፡ “ኤስ” በዩኒት ሊደሩ እየተገፈተረ ከክፍሉ ወጥቶ ሄደ፡፡
ከሄደ በኋላ ማንም አይቶት አያውቅም፡፡ አንድ አመት ተቀጥቶ ይመለሳል ብለው ጓደኞቹ ቢያስቡም ሳይሆን ቀረ፡፡ ማህሌት ሚስጥሯን ይዛ እንደተብሰለሰለች ትምህርቷን ጨረሰች፡፡ እንዲያውም ማለፊያ ውጤት አግኝታ የንግድ ስራ ትምህርት ቤት ተቀላቀለች፡፡


ለመቄዶንያ 500ሺ ብር አበረከተ

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የክፍያ ካርድ ያስተዋወቀው ዳሽን ባንክ፤ አሁን ደግሞ የአሜሪካ ኤክስፕረስ ካርድ፣ የሞባይልና ኤጀንሲ (ውክልና) አገልግሎት በቅርብ እንደሚጀምር ተገለፀ፡፡
የአሜሪካ ኤክስፕረስ ካርድ ከፍተኛ ገንዘብ የሚያንቀሳቅሱ ሀብታሞች የሚጠቀሙበት “ፕሪስቲጂየስ ካርድ” ነው ያሉት  የዳሽን  ባንክ የፕሮሞሽን ዋና ክፍል ኃላፊ አቶ እስጢፋኖስ በፍቃዱ፤ ከውጭ የሚመጡ ሀብታሞች ካርዱን ስለሚጠቀሙ ለውጭ ምንዛሬ ዕድገት ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል፡፡ በቪዛ ካርድ እንዳደረግነው ሁሉ፣ የአሜሪካን ኤክስፕረስ ብራንድ ያላቸውን ካርዶች አምርተን ከጥር ጀምሮ ለህዝቡ እናድላለን ያሉት ኃላፊው፣ ካርዱ በአሜሪካ የሚያስገኛቸውን ጥቅሞች እዚህም ያስገኛል ብለዋል፡፡
አንድ ሰው በአሜሪካ በኤክስፕረስ ካርዱ ፒዛ ገዝቶ በመብላቱ ብቻ 40  ዶላር ሊመለስለት ይችላል፡፡ እዚህም የካርዱን አገልግሎት በሚሰጡ ማዕከላት ለምሳሌ እንደ ካልዲስ ወይም ሌላ ካፌ ፒዛ በልቶ፣ ወተት ወይም ማኪያቶ ጠጥቶ ካርዱን ሲሰጣቸው 40 ብር ሊመልሱለት ወይም የመቶ ብር ዕቃ ገዝቶ 80 ብር ሊመለስለት እንደሚችል አስረድተዋል፡፡
ዳሽን ባንክ ከትንሽ እስከ ትልቅ የፕላቲንየም፣ የብርና የወርቅ ብራንድ ያላቸው አሜሪካን ኤክስፕረስ ካርዶች ያዘጋጀ ሲሆን እንደ ግለሰቡ ፍላጐት የ100ሺ፣ የ300 ሺና የ500 ሺና ብር ካርድ ሊዘጋጅለት እንደሚችል ታውቋል፡፡
ዳሽን ባንክ፣ በአገራችን ያልነበረ አዲስ የሞባይልና ኤጀንሲ (የውክልና) አገልግሎት በሚቀጥለው ታህሳስ ወር ለመጀመር ዝግጅት ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡ ሞባይልና  ኤጀንሲ ማለት፣ ዳሽን ባንክ ቅርንጫፍ በሌለው አካባቢ አገልግሎት የሚሰጥ በማህበረሰቡ የተወደደና የተመረጠ ወኪል ማለት እንደሆነ አቶ እስጢፋኖስ ገልፀዋል፡፡
ዳሽን ባንክ ቅርንጫፍ በሌለው ትንሽ ከተማ ማህበረሰቡ የሚወደውና የሚያምነው ነዳጅ ማደያ፣ ሱፐርማርኬት፣ ወይም ከሌላ ድርጅት ጋር ውክልና ይፈራረማል፡፡ ውሉ የተሰጠው ድርጅት የተወሰነ ገንዘብ (200ሺ፣ 300 ሺ፣… ብር) እንዲያሲዝ ይደረጋል፡፡ ከዚያም፣ አዲስ አበባ፣ ጎንደር፣ መቀሌ፣ ጂማ፣ ሐዋሳ፣ ድሬደዋ፣ …. ያለ የዳሽን ባንክ ደንበኛ፣ ሞባይልና ኤጀንሲ ወዳለበት ቀበሌ ገበሬ ማኅበር፣ መንደር ወይም ትንሽ ከተማ፣ … ለሚኖር ዘመድ ወይም የንግድ ባልደረባ፣ … እንዲሰጠው ገንዘብ ዳሽን ባንክ ያስገባል፡፡
ባንኩም፣ ለላኪው፣ ተቀባይ ገንዘቡን የሚቀበልበትን ሚስጢራዊ ቁጥር ወይም ኮድ ይሰጠዋል፡፡ ከዚያም ለሞባይልና ኤጀንሲው (ወኪሉ) ደውሎ፣ እንዲህ ዓይነት ኮድ ለሚያቀርብልህ ሰው ወይም ድርጅት፣ ይህን ያህል ብር ክፈለው የሚል መልእክት ያስተላልፍና ወኪሉ ካስቀመጠው ገንዘብ ላይ የከፈለው ገንዘብ እንዲቀነስ ይደረጋል፡፡ በመጨረሻም፣ ወኪሉ ለሰጠው አገልሎግት ባንኩ ኮሚሽን ይከፍለዋል በማለት አስረድተዋል፡፡
በሌላ በኩል የዳሽን ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከልን “ብቸኛ የዓመቱ ምርጥ በጐ አድራጐት ድርጅት” በማለት የ500ሺ ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን የማዕከሉ መሥራችና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢንያም በለጠ አስታወቁ፡፡
መቄዶንያ በአሁኑ ወቅት 715 አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማንን በተለይም የአልጋ ቁራኛ የሆኑ፣ ለመመገብም ሆነ ለመፀዳዳት የሰው ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች ከወደቁበት ጐዳና በማንሳት፣ የምግብ፣ የልብስ፣ የሕክምና፣ የተሟላ ቤተሰባዊ ፍቅርና እንክብካቤ እያደረገ መሆኑን አቶ ቢንያም ጠቅሰው፤ ዳሽን ባንክ ለሦስት ዓመታት በተከታታይ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡
ባንኩ ባደረገላቸው ድጋፍም የብዙ ወገኖችን ሕይወት ማትረፋቸውን ገልፀው፤ ሌሎች ባንኮችና ድርጅቶች አርአያውን ተከትለው ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
በድርጅታችን የአንድ ሰው የቀን ወጪ 20 ብር ነው ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ የ715 ወገኖች የቀን ወጪ 14,300 ብር፣ የወር ወጪ 429ሺህ ብር፣ የዓመት ደግሞ 5 ሚ. 219 ሺ 500 ብር ይሆናል ብለዋል፡፡ ዳሽን ባንክ ዘንድሮ ለማዕከሉ ባደረገው ድጋፍ፤ ተጨማሪ 70 ሰዎችን ከጐዳና ማንሳታቸውን ጠቅሰው፤ በተረጂ ወገኖች ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በቅርቡም “ዓለም ገነት ቆርቆሮ ፋብሪካ” ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል 500ሺ ብር የሚገመት የዓይነት ድጋፍ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

አዋሽ ኢንሹራንስ ኩባንያ በአገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው አዲስ የኢንሹራንስ ሶፍትዌር አሰርቶ ስራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ፡፡ ኩባንያው በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ ውጤማታና ቀልጣፋ አገልግሎት ለደንበኞቹ ለመስጠት፣ የተቀናጀ የጠቅላላ መድን የመረጃ ሥርዓት (General Insurance Information System - Glls) ሶፍትዌር ማሰራቱን የጠቀሱት የኩባንያው ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ከሚሴ፤ ሶፍትዌሩን የሰራው የህንዱ ኩባንያ ኢንፎዥን፣ አማካሪው ደግሞ አገር በቀሉ ናሽናል ኮንሰልቲንግ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ ዛሬ የደረስንበት ስኬት በሀገሪቷ የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ የተሟላ የቴክኖሎጂ መፍትሄ በመፍጠር ረገድ እንደ መልካም መነሻ ይታያል ያሉት ሥራ አስኪያጁ፤ በየክልሉ ያሉት ቅርንጫፎቻችን በሙሉ ይህንን አዲስ ሶፍትዌር ስለሚጠቀሙና የመረጃ ሥርዓቱ በኔትዎርክ የታገዘ በመሆኑ፣ የኩባንያው የሥራ አመራሮች የእያንዳንዱን ቅርንጫፍ ዝርዝር ሥራ በመከታተል ተገቢውን ድጋፍ በፍጥነት ይሰጣሉ ብለዋል፡፡ በመረጃ ሥርዓቱ አማካይነት ሪፖርቶችን በአጭር ጊዜ ውስጥ በማግኘት መረጃና ዕውቀት ላይ የተመሰረተ የማኔጅመንት ውሳኔ መስጠት እንደሚቻል ገልጸው፤ በውል ሰነዶች ውስጥ ያሉ መረጃዎች ሁሉ በሲስተሙ ውስጥ ስለተጠቃለሉ የሁሉም  ደንበኞች የውል፣ የካሣ፣ የጠለፋ ዋስትና፣ የገበያ ልማትና የፋይናንስ መረጃዎች በቀላሉ የሚናበቡ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
በውላቸው መሰረት ሶፍትዌሩን የሰራውና አማካሪው በየጊዜው ማሻሻያ እንደሚያደርጉና ይሄም ለኩባንያው ራዕይ መሳካት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት የገለፁት ሥራ አስኪያጁ፤ በዚህም “ግንባር ቀደምና ተመራጭ መድን ሰጪ መሆን” የሚለውን የኩባንያችንን ራዕይ እናሳካለን ብለዋል፡፡ ለሶፍትዌሩ 2.5 ሚሊዮን፣ ለሃርድዌሩ ደግሞ 3 ሚሊዮን ብር ወጪ መደረጉንም ገልጸዋል፡፡  

ከአገር ውጭ የሚደረጉ ጉዞዎችንና የትምህርት ክፍያ ማረጋገጫ ዋስትናዎችን መስጠት እንደጀመረ የገለፀው ኢትዮ ለይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር፤ ይህም አገልግሎቱን የተሟላ ለማድረግ እንደሚያስችለው የድርጅቱ ኃላፊዎች ከትናንት በስቲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ፡፡
በአገሪቱ የኢንሹራንስ ገበያ ውስጥ አዳዲስ አሠራሮች ናቸው ከተባሉት ከእነዚህ የመድን ዋስትናዎች በተጨማሪ የህክምና፣ የዕድሜ ልክ፣ የኢንዶውመንት፣ የብድር ዕዳ ማስወገጃ፣ የእሳት ቃጠሎና የመብረቅ፣ የአበባ እርሻ፣ የሠራተኞች ጉዳት ካሳ፣ የምሕንድስና መድንና ሌሎች የዋስትና ዓይነቶችንም ለአገልግሎት ማቅረቡን አስታውቋል፡፡
በጥቅምት ወር 2001 ዓ.ም ከብሔራዊ ባንክ በተሰጠው ፍቃድ መሰረት ሥራ የጀመረው አክስዮን ማህበሩ፤ በአሁኑ ወቅት 58ሺ አክሲዮኖችን ለሽያጭ ማቅረቡንና የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት ሚሊዮኖችን ለማገልገል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጿል፡፡ በ
ቅርቡ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ሁለት ቅርንጫፎቹን በመክፈት የቅርንጫፍ ቢሮዎቹን ቁጥር ወደ 15 ከፍ ለማድረግ ማቀዱንም ኃላፊዎቹ ገልፀዋል፡፡