Administrator

Administrator

•  ማህበሩ 70 ቢሊዮን ብር ለብድር ማቅረቡ ተነግሯል

የኢትዮጵያ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ማህበር የተመሰረተበትን የ25ኛ ዓመት የኢዮቤልዩ ክብረ በዓል በመጪው ሳምንት በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚያከብር ተገለፀ፡፡

በዝግጅቱ ላይ በአገሪቱ በልማቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተውና የ25 ዓመታት እድሜ ያስቆጠረው የማይክሮፋይናንስ ዘርፍ ኅዳር 18ን “የኢትዮጵያ የብድርና ቁጠባ ቀን” በማለት እንደሚሰይም ተነግሯል፡፡  

በማህበሩ የ25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ በዘርፉ የተሰማሩ የአገር ውስጥና የውጭ ተቋማት እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና የልማት አጋሮች እንደሚሳተፉ የጠቆመው የማህበሩ መግለጫ፤ ክብረ በዓሉ በፓናል ውይይትና ኤግዚቢሽን እንዲሁም ጥናቶች በሚቀርቡበት ኮንፍረንስና ሌሎች ኹነቶች እንደሚከበር አመልክቷል፡፡

ክብረ በዓሉ በመጪው ሳምንት ከህዳር 18-21 ቀን 2016 ዓ.ም፣ ለአራት ተከታታይ ቀናት፣ በሃይሌ ግራንድ ሆቴል ይከበራል፡፡

የ25ኛ ዓመት በዓል አከባበሩን  በተመለከተ በዛሬው ዕለት ረፋዱ ላይ ዳሙ ሆቴል አጠገብ ወደ ፒኮክ መናፈሻ መግቢያ ላይ በሚገኘው የማህበሩ አዳራሽ ፣ የማህበሩ የቦርድና የማኔጅመንት ከፍተኛ አመራሮች ለሚዲያ ባለሙያዎች  መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በዓሉ “ማይክሮፋይናንስ በዲጂታል ዘመን፣ የፋይናንስ አካታችነት ለስራ ፈጠራና ለሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑን ያመለከተው  ማህበሩ፤ ባለፉት ዓመታት በዋናነት የዲጂታል ስርዓት በማስፋፋትና በፋይናንስ አካታችነት ረገድ ጉልህ ስኬት መቀዳጀቱን ጠቁሟል፡፡

የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የዲጂታል ሥርዓት ተጠቃሚ መሆናቸው በተጨባጭ ውጤታማ እንዳደረጋቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በቴክኖሎጂው አማካኝነት  የተደራሽነት ሽፋናቸውን ቀድሞ ከነበረው 35 በመቶ ገደማ ወደ 50 በመቶና ከዚያም በላይ ማሳደጋቸው ተጠቁሟል፡፡  

ከ50 የማህበሩ አባላት መካከል በ30 የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የኮር ባንኪንግ ዲጂታል ሥርዓት መተግበሩን የገለጹት አመራሮቹ፤ በፋይናንስ አካታችነት ረገድም ከባንኮች ይልቅ ተቋማቱ የበለጠ ስኬት መቀዳጀታቸውን ጠቁመዋል፡፡

እስካሁን ድረስ ስድስት የሚሆኑ የማህበሩ አባላት ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን መስፈርት በማሟላት ወደ ባንክ ማደጋቸውንና በሂደት ላይ የሚገኙም እንዳሉ የጠቆሙት አመራሮቹ፤ ተቋማቱ ወደ ባንክ ሽግግር ቢያደርጉም የቀድሞ አገልግሎታቸውን የመስጠት ግዴታ እንዳለባቸው አመልክተዋል፡፡


ማህበሩ የሴቶች ተጠቃሚነትን በማረጋገጥ ረገድም ትርጉም ያለው ሥራ ማከናወኑን የተናገሩት አመራሮቹ፤ በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ለሴቶች ሲቀርብ የነበረው ብድር አነስተኛ ቢሆንም፣ በሂደት እየተሻሻለ መጥቶ በአሁኑ ወቅት የብድሩ መጠን 50-50 (እኩል ለእኩል) ለመሆን መብቃቱን ጠቅሰዋል፡፡  ለሴቶች ተስማሚ የሆነ የብድር አገልግሎት ለመተግበር ጥረት መደረጉንና የሴቶች ተሳትፎም ከዓመት ወደ ዓመት እያደገ  መምጣቱን አክለው ገልፀዋል፡፡

በማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት የሚቆጥቡ ደንበኞች ከ20 ሚ. በላይ እንደሚደርሱ የተነገረ ሲሆን፤ ማህበሩ  ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ለብድር  ማቅረቡን  ለማወቅ ተችሏል፡፡

የኢትዮጵያ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ማህበር ባለፉት 25 ዓመታት ስኬት ብቻ አይደለም የተቀዳጀው፤ ቀላል የማይባሉ ተግዳሮቶች እንዳገጠመውም የማህበሩ አመራሮች በመግለጫቸው ላይ ተናግረዋል፡፡

ከተግዳሮቶቹም መካከል የፋይናንስ እጥረት በቀዳሚነት ተጠቅሷል፡፡ የተጀመረውን ኮር ባንኪንግ ተግባራዊ ለማድረግ ማህበሩ ከፍተኛ የፋይናንስ ችግር ገጥሞት ነበር ያሉት አመራሮቹ፤ የውጭ ምንዛሬ በፈለግነው ጊዜና መጠን ባለማግኘታችንም ተቸግረን ነበር ብለዋል፡፡  ሆኖም ማህበሩ ችግሩን ከተቋማቱ  ጋር በጥምረት በመስራት ለመፍታት እንደተቻለ ተጠቁሟል፡፡

የመሰረተ ልማት ችግር ሌላው የገጠማቸው ተግዳሮት እንደነበር የጠቆሙት የማህበሩ አመራሮች፤ የኢንተርኔትና የኤሌክትሪክ ሃይል መቆራረጥ ሥራቸውን እያስተጓጎለባቸው ይቸገሩ እንደነበር ጠቁመው፣ ከፍተኛ አቅም ያለው ጄነሬተር በመጠቀም አገልግሎታቸውን ያለማቋረጥ ማቅረብ መቻላቸውን አስረድተዋል፡፡

ከሁሉም በላይ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማቱ ትልቅ ተግዳሮት የሚያበድሩት ካፒታል ማነስ  መሆኑን በይፋ የገለፁት የማህበሩ አመራሮች፤ በዚህ ረገድ መገናኛ ብዙኃን ስለማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትና አገልግሎታቸው ለህብረተሰቡ በቂ መረጃ በመስጠትና ግንዛቤ በማስጨበጥ ትልቅ አስተዋጽኦ ሊያበረክቱ እንደሚችሉ ጠቁመው፣ እግረ መንገዳቸውን በመግለጫው ላይ ለተገኙት የመገናኛ ብዙሃን ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Wednesday, 22 November 2023 21:26

addisadmassnews.com Issue1244

Wednesday, 22 November 2023 20:21

እነሆ ድልድዩን !

እነሆ ድልድዩን !
ይህንን መጽሐፍ አንብቤ እንዳጠናቀቅኩ በሃሳቤ " የሰው ልጅ ስልጣን ላይ ሆኖ ባበበበት ወቅት (በተወደደበት ጊዜ ) ያቺ ጊዜ ሳታልፍ ለተተኪው ትውልድ ስልጣኑን ቢያስረክብ በታሪክ ውስጥ ዘላለማዊ ይሆናል ። ታላቅነቱንም ምንጊዜም ትውልድ ይመሰክርለታል። እርሱም ካደለው ይህንን በህይወት ቆሞ ያያል ።" በማለት አብሰለሰልኩ ።
የመጽሐፉ ርእስ " ዘውድ ያልደፋው ንጉሥ " ደራሲው ደረጀ ተክሌ ወልደ ማሪያም ሲሆን በ452 ገጽ ተጠርዞ  በ500 ብር ገበያ ላይ ውሏል።
ባለታሪኩ ጸሐፌ ትእዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ ናቸው ። ከ1893 - 1968 ዓም እዚህ ምድር ላይ ያኖረዋል ።በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ከፍተኛ ባለስልጣን ነበሩ ። እኝህ ድንቅ ሰው ምን እንደከወኑ ደረጄ ማለፊያ በሆነ ትረካ ያወጋናል እና መጽሐፉን ገዝቶም ሆነ ፈልጎ ማንበቡን ለእናንተ ልተው ። እኔ ስለጀግናው ቀደም ብሎ መረጃ ቢኖረኝም ደረጀ መረጃዬን ጥብስቅ ስላደሰገልኝ ላመሰግነው እወዳለሁ ። ጸሐፌ ትእዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ለጃንሆይ ምን ብለዋቸው ነው ከላይ በጥቅስ ያስቀመጥኩትን አባባል ያልኩት ? ጸሐፌ ትእዛዝ የጥንቱን ትውልድ ከአዲስ ትውልድ ያገናኙ ድልድይ ነኝ ይላሉ ። ... የእንግሊዝን መንግስት የኢትዮጵያ ሞግዚትነት አምክነው አገራችንን ነፃነቷን እንድትጎናጸፍ ካደረጉ አርቆ አሳቢዎች መካከል አውራውም ናቸው ። ...
መልሱን ከመጽሐፉ ታገኙታላችሁ ።
ሰላም በምድራችን ላይ ይስፈን !

ከትምህርት ባሻገር ሁለንተናዊ የሰብዕና መገንቢያና የተሻለ የትምህርትና የሥራ አካባቢ ለመፍጠር ባህል ማዕከሉን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

ማዕከሉ በየሳምንቱ ማክሰኞ የኪነ-ጥበብ ምሽት ዳግም ማዘጋጀት እንደሚጀምር የባህል ማዕከሉ ኃላፊ ተስፋዬ እሸቱ ገልጸዋል፡፡

ቅዳሜ፣ ማክሰኞና ሐሙስ ደግሞ ፊልም የሚያሳይ ሲሆን፤ በቀረቡት ፊልሞች ላይ በወር አንድ ጊዜ ውይይት ይደረጋል ብለዋል።

ባህል ማዕከሉ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰርከስ ማኅበር ጥምረት ጋር በጋራ መሥራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነትም ተፈራርሟል።

Wednesday, 22 November 2023 11:49

ምርጥ አባባሎች:-

ምርጥ አባባሎች:-

" የትልቅ ሰውን ትልቅ ስራ ሌሎች ይናገሩለታል እንጂ እርሱ አይናገርም።"

(የህልም ዣት)

" የምትወደው ሁልጊዜ ሲለይህ የሚያስረሳህ እንጂ የሚያስታውስህ ነገር አትፈልግ፤ ያለዚያ ህይወትህ የስቃይ ህይወት ይሆናል።"

(ፍቅር አስክ መቃብር)

" ሰው ባለመብት የሚያደርገው የሚፈፅመው ተግባር ነው፤ ተግባሩን ሳይፈጽም በመብቱ የተጠቀመ ሁሉ ባለዕዳ ነው።"

(ወንጀለኛው ዳኛ)


የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

የ“ፍትሕ መጽሔት” ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ዛሬ ኅዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም. በጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ከጠበቆቹ ጋር ቀርቧል።
ፍርድ ቤቱ በዛሬው ዕለት ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፣ በባለፈው ቀጠሮ ፣ የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጠበቆች፤ “የጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት፣ የዐቃቤ ሕግን የይግባኝ ቅሬታና የፍርድ ቤቱን ውሳኔ ሲሰጠን ገጽ አጉድሎ ስለሆነ የተሟላ መልስ መስጠት ባለመቻላችን፣ መልሳችን እንድናሻሽል ይፈቀድልን” በሚል አቤቱታ አቅርበው ነበር፡፡
ዐቃቤ ሕግም በበኩሉ፤ “በዚህ አቤቱታ ላይ እኔም አስተያየት መስጠት አለብኝ” ብሎ ተከራክሯል፡፡
ጠበቆቹም፤ “እኛ ስህተት ሠራ ያልነው ፍርድ ቤትን ነው፡፡ ስህተቱን እንዲያርምም የጠየቅነው ፍርድ ቤቱን ነው፡፡ ከዐቃቤ ሕግ ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም፡፡ ስለዚህም ዐቃቤ ሕግ ስለማይመለከተው ጉዳይ አስተያየት እንዲሰጥ ሊፈቀድለት አይገባም፤” በሚል ተከራክረዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም፤ “ዐቃቤ ሕግ አስተያየት ይስጥ ወይስ አይስጥ ብሎ ትእዛዝ ለመስጠት ዳኛ ስለሚጎድል ለህዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም  ቀጠሮ ስጥተናል፤” ማለቱ ይታወሳል፡፡
በአቶ ሸምሱ ሲርጋጋ የመሀል ዳኝነት (ሰብሳቢነት)፣ በሀፊዝ አባጀማል እና መሀመድ አህመድ የግራና ቀኝ ዳኝነት ጉዳዩን ያየው ፍርድ ቤትም፣ “ዐቃቤ ሕግ አስተያየት መስጠት ይገባዋል” ሲል የሰጠው ትእዛዝ ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም በችሎት በንባብ ተሰምቷል፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በሰጠው አስተያየት፤ “የተሰጠው ትእዛዝ  ፍጹም ስህተት ነው፡፡ ይሄ የፍርድ ቤቱን ተአማኒነት ገና ከመነሻው ጥርጣሬ ውስጥ የሚጥል ነው፡፡ ችሎቱ፣ ዐቃቤ ሕግ የሚጠይቀውን ሕገ-ወጥ ጥያቄ በሙሉ እየተቀበለ የሚሄድ ከሆነ ታዲያ፣ እንዴት ነው ነፃና እውነተኛ ፍትሕ የሚገኘው?” ሲል ቅሬታውን ገልጿል፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ  ያነጋገርናቸው አንዳንድ የሕግ ባለሙያዎችም፤ “ዐቃቤ ሕግ አስተያየት ይስጥ” ተብሎ መታዘዙ አግባብነትና ተቀባይነት የሌለው መሆኑን በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ፣ የዐቃቤ ሕግን አስተያየት ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም  በቢሮ በኩል ከተቀበለ በኋላ፣ የጋዜጠኛ ተመስገን ጠበቆች ያቀረቡት የመልስ ማሻሻያን በተመለከተ ውሳኔ ለመስጠት ለታኀሣስ 11 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
 የቴሌግራም ቻናልችንን  በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
https://t.me/AdissAdmas

የባንኩ  የሃብት መጠን  83 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል

 ሕብረት ባንክ የ25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ ክብረ በዓሉን በዛሬው ዕለት በይፋ ያበሰረ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት የባንኩ የሃብት መጠን  83 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታውቋል።

 አጠቃላይ ካፒታሉ 9. 3 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም  60 ቢሊዮን ብር ብድር እና 64 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ እንዳለው የገለጸው ባንኩ፤ በየዓመቱ ከ25 እስከ 30 በመቶ እድገት እያስመዘገበ  መምጣቱንም ጠቁሟል።

ባንክ ባለፉት 25 ዓመታት የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ መዝለቁ የተገለፀ ሲሆን፤ ከ15 ዓመታት በፊት ሞባይል ባንኪንግን፣ ኤስኤምኤስ ባንኪንግ በሚል በመጀመር ቀዳሚ ባንክ እንደሆነ ተመልክቷል፡፡

በተጨማሪ ባንኩ የኮር ባንኪንግ ሲስተም በራሱ ሰራተኞች መተግበሪያ በማበልፀግ በኢትዮጵያ ብቸኛው ባንክ መሆኑም ተነግሯል፡፡  

ባንኩ የተመሠረተበት የ25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ ክብረ በዓል፣ ዓመቱን በሙሉ በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚያከብርም ተጠቁሟል።

*ኩባንያው በቅርቡ በ3 የአፍሪካ አገራት የዳታ ማዕከሎቹን ይከፍታል

በሰባት የአፍሪካ አገራት የሚንቀሳቀሰው  ራክሲዮ የዳታ ማዕከል ኩባንያ፣ በአዲስ አበባ አይሲቲ ፓርክ የገነባው ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የዳታ ማዕከሉ  በይፋ ሥራ መጀመሩን አበሰረ፡፡

በዓይነቱ ልዩ መሆኑ የተነገረለት የራክሲዮ ኢትዮጵያ የዳታ ማዕከል፣ በይፋ ሥራ መጀመሩን የማብሰሪያ ሥነስርዓት ዛሬ ጠዋት ረፋዱ ላይ በአይሲቲ ፓርክ የተከናወነ ሲሆን፤ በሥነሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ አምባሳደሮች፣ የፋይናንስ ተቋማት ሃላፊዎች፣ የቴክኖሎጂ ዘርፉ መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

ራክሲዮ ኢትዮጵያ በይፋ ሥራ መጀመሩን አስመልክቶ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ “በኢትዮጵያ ዋና ከተማና የአገሪቱ የኢኮኖሚ ማዕከል በሆነችው አዲስ አበባ የሚገኘው አዲሱ የራክሲዮ ደረጃ III ዕውቅና የተሰጠው ዘመናዊ የዳታ ማዕከል፣ ከምንጊዜውም በላይ እያደገ ለመጣው የመንግሥትና የግል ተቋማት የዳታ ማዕከል አገልግሎት ጥያቄዎች፣ አስተማማኝና የማይቆራረጥ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መፍትሄ በማቅረብ መልስ የሚሰጥ ይሆናል፡፡” ብሏል፡፡

ማዕከሉ፤ 800 ራኮችና እስከ 3 MW የአይቲ ሃይል፣ ደህንነቱ በተጠበቀ የዳታ ማዕከል አገልግሎት ለመስጠት፣ ሙሉ በሙሉ ምትክ ያለው ያለማቋረጥ የሚሰራ የአይቲ መሰረተ ልማቶች  ዝግጁ አድርጓል - ሲል አክሏል ኩባንያው በመግለጫው፡፡

በኢትዮጵያ የራክሲዮ ዳታ ማዕከል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ በዕውቀቱ ታፈረ ባደረጉት ንግግር፤ “ይህ አገልግሎት በአዲስ አበባ መጀመሩ ለራክሲዮና ለአገራችን በዲጂታል መሰረተ ልማት ረገድ መሰረት የሚጥል ነው፡፡ አገልግሎቱ በኢትዮጵያ የምጣኔ ሃብት ዕድገት ውስጥ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ሲሆን፤ በተለያዩ አካባቢዎች የሚከናወኑ የንግድ ሥራዎችንና የመንግሥት ኤጀንሲዎች የሥራ እንቅስቃሴን ከማፋጠንም ባሻገር፣ አህጉራዊና ዓለማቀፍ አገልግሎትና የይዘት አቅራቢዎችን ወደ ኢትዮጵያ ለመሳብ አጋዥ እንደሚሆን እናምናለን፡፡” ብለዋል፡፡

ዋና ሥራ አስኪያጁ በማከልም፤ “የማዕከላችን ደረጃ III ዓለማቀፍ የምስክር ወረቀት፣ እኛ  እየሰጠን ያለው የአገልግሎት ጥራት መጠን ማሳያ ሲሆን፤ ለደንበኞቻችን ደግሞ ለማናቸውም ንብረቶቻቸው ከፍተኛ ደህንነት አስተማማኝ ማረጋገጫ የሚሰጥ ነው፡፡” ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል፡፡

የዳታ ማዕከሉ በይፋ ሥራ መጀመሩን ያበሰሩት የራክሲዮ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሮበርት ሙሊንስ በበኩላቸው፤ “ይህንን በዓይነቱ ልዩና የመጀመሪያ የሆነ ወሳኝ መሠረተ ልማት በኢትዮጵያ ተግባራዊ በማድረጋችን እጅግ ኩራት ይሰማናል፡፡ የኢትዮጵያን ቀጣይ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና የዲጂታል አካችነት ጅምር ግቦችን የሚደግፍ እንደሆነ ሙሉ እምነታችን ነው፡፡ ብለዋል፡፡

ሮበርት ሙሊንስ አክለውም ሲናገሩ፤ “ይህ ጊዜ ለእኛ እንደ ኩባንያ እጅግ በጣም ደስተኛ የሆንበት ነው፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት በኡጋንዳ እንደዚሁ ተመሳሳይ ማዕከላችንን ከጀመርን በኋላ፣ ራክሲዮ ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ ሁለተኛው ማዕከላችን  መሆኑ ነው፡፡ እ.ኤ.አ. እስከ 2024 የመጀመሪያ አጋማሽ ድረስ ተመሳሳይ ማዕከሎችን  በሞዛምቢክ፣ በአይቮሪኮስትና በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የምንከፍት ይሆናል፡፡” ብለዋል፡፡

ዛሬ ረፋድ ላይ በአይሲቲ ፓርክ የተገነባው የራክሲዮን ኢትዮጵያ የዳታ ማዕከል በይፋ ሥራ መጀመር ከተበሰረ በኋላ፣ የዕለቱ እንግዶችና ባለድርሻ አካላት እንዲሁም የሚዲያ ባለሙያዎች  የዳታ ማዕከሉን ጎብኝተዋል፡፡

“--በሙድ የመተረክ ዘዬ፣ ዶ/ር ፍራንክልን የረዳቸው ይመስለኛል። የሥነ-ልቡና እና ሥነ-አዕምሮ ይዘት ያለውን ድርሰት በጊዜው በነበረው ሙድ ላይ ተመርኩዘው የእስረኞችን ሁኔታ፣ ችግርና መፍትሄ ለመተንተን ጠቅሟቸዋል የሚል ዕምነት አለኝ። እዚህ ላይ ሙድ/ሁኔታ ለአንድ ርዕሰ-ጉዳይ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው
መዘንጋት የለብንም

መነሻ:- ድርሰትን መተርጎም የተለመደ
እና የሚበረታታ ሲሆን፤የትርጉም ሂደቱ ከዋናው መጽሐፍ ላይ ከቀጥታ ትርጉም (equivalent
translation) ይልቅ በአገባብ/ በሁኔታ በመወሰን (contextual/ context-based translation) አንቀጽ-በአንቀጽ መተርጎም ይመከራል። ብሎም፣ የአንቀጾቹ ስብስብ (ወደ essay ከፍ ያሉ አንቀጾች) በessay መልክ ሲሆኑ የሚሰጡትን ትርጉም/ እንድምታ ማጤን ተገቢ ነው። ይህ ማለትአንቀጾቹ በessay ተጠቃለው/ተዋህደው የሚሰጡትን መልዕክት ከዋናው መጽሐፍ ፍሬ-ሀሳብ ጋር ማመሳከር አግባብ ነው እንደማለት ነው።
በትርጉም ሥራ ውስጥ፣ የመጀመሪያው (የዋናው) ድርሰት ማሕበረሰብ ታሪክ፣ ባሕል፣ ዕምነት… ወዘተ. የሚተረጎምለትን ሕዝብ ታሪክ፣ ባሕል፣ ዕምነት… ሊጫን፣ ወይም ሊጣረስ ይችላል። ስለሆነም፣ ለሕዝቡ/ለአንባቢው ባመቸ መልክ (ዋናው ሃሳብ ሳይሸራረፍ) እየተኩ መተርጎም ይመከራል። እዚህ ላይ፣ ‹‹ዘርህ እንደ ምድር አሸዋ ይብዛ›› የሚል የወንጌል ቃል፣ አሸዋ በሌለባቸው፣ በረዶ በመላባቸው
አካባቢዎች ‹‹ዘርህ እንደ ምድር በረዶ ይብዛ›› ተብሎ ተተክቶ ተተርጉሞ አይተናል። (ግን ‹‹ዘርህ እንደ ምድር በረዶ ይቅለጥ›› ማለት አይቀልም ነበር?) በአገራችን የተነበቡ የትርጉም ሥራዎች ከመጀመሪያው ድርሰት ላይ ትረካዎችን፣ ወይም የትረካ ክፍሎችን የመቆራረጥ/ የመሸራረፍ አባዜ ይታይባቸዋል። ይኼ ጉዳይ የድርሰቱን ሙሉ ሃሳብ እንዳንረዳው ያደርገናል። ለምሳሌ፣ ‹‹ፍቅር እስከ››
መቃብር ላይ የተተረከውን የሰብለንና የበዛብህን ውብ ጾታዊ መቧጠጥ/ንክኪ ቆርጠን ወደ ሌላ ቋንቋ ብንተረጉም የዚያ ቋንቋ ተናጋሪ የድርሰቱን ሙሉ ጭብጥ እንዳይረዳው ያደርጋል። የ‹‹ለምንን ፍለጋ›› በረከቶች:- “Man’s Search for Meaning”: - ትርጉም ድርሰቱ በጀርመን ውስጥ የነበረ የእስር ቤት ታሪክ ሲሆን፣ ባለ ታሪኩ (ቪክቶር ፍራንክል - የአዕምሮ ሕክምና ዶክተር ናቸው) ከሌሎች ታሳሪዎች ጋር የነበራቸውን ቆይታ፣ ያሳለፉትን ፍዳ፣ ገጠመኞች…. ወዘተ. ያሠፈረበት ድርሰት ነው።
ሲግመንድ ፍሮይድ፣ ለአዕምሮ መታወክ መንስኤው ከወሲብ ጋር በተገናኘ የሚከሰት ደስታ-ቢስነት ነው ይላል። ቪክቶር ፍራንክል ደግሞ፣ የአዕምሮ መታወክን ከፈቃድ ትርጉም (the will to meaning) ጋር ያያይዛል። ደራሲው ምንም እንኳን የግል የእስር ታሪኩን ቢያትትም፣ በዙሪያው የሚስተዋለውን የአዕምሮ ዝቅጠት (ለምሳሌ፣ በእስረኞቹ ዘንድ ሕይወትን ለማቆየት ሲባል ዝቅ ያሉ/ተራ የሆኑ ጉዳዮችን በማምሰልሰል፣ በማለም፤ ስለ

ምግብና ስለ መጠጥ አብዝቶ በመጨነቅ)
የሚፈጠረውን የሥነ-ልቡና እና የሥነአዕምሮ ድቀት ፍቅረኛን በማለም፣ በጥበብ በመደሰት፣ የተፈጥሮ ጸጋን በማድነቅ፣ ጀንበርን/ብርሃንን በመናፈቅ፣ ውበትን በማድነቅ… ወዘተ. መቅረፍ እንደሚቻል ይገልጻል። ከአዕምሮ ዝቅጠት (mental regression) ለመላቀቅ (በአራዶች አባባል ‹ለመፋታት›) ፍቅር፣ ብርሃን፣ ውበት፣ ጥበብ፣ ተፈጥሮ… ወዘተ. አዎንታዊ ፋይዳ እንዳላቸው ተገልጿል።
የምሳሌያዊ አነጋገር፡- በትርጉም ሥራዎች ላይ ትኩረትን ከሚሹ ጉዳዮች አንዱ የምሳሌያዊ አነጋገር ነው። በድርሰት ውስጥ አንድን ሃሳብ፣ ወይም ትረካ በምሣሌያዊ አነጋገር፣ በዘይቤአዊ ንግግር፣ በፈሊጥ፣ በተረት… መግለጽ ነገሩን ለማግዘፍና ግልጽ ለማድረግ ይረዳል። ተርጓሚው የምሣሌያዊ አነጋገርን የተጠቀመ ሲሆን፣ ይኼም ለአንባቢው ባሕል እና ልምድ በቀረበ መልኩ ነው። ለምሳሌ፣ ‹‹የተቸገረ እርጉዝ ያገባል››፤
ገጽ 21 ላይ መጥቀስ ይቻላል።የግርጌ ማስታወሻዎች፡- ይኼ ነጥብ የትርጉም ሥራው ልዩ መገለጫው ይመስለኛል። በትርጉም መጽሐፉ
ውስጥ የተካተቱ የኅዳግ ማስታወሻዎች (በተርጓሚው የተጨመሩ)፣ አንድን ቃል ከማብራራት እስከ አንድን ርዕሰ-ጉዳይ በሰፊው እስከ መተንተን ይደርሳሉ። የዚህ ፋይዳ በትረካው ውስጥ የተነሱ፣ ምናልባት ግርታን/ የግንዛቤ ችግርን ሊፈጥሩ ለሚችሉ ቃላትና ርዕሰ-ጉዳዮች አንባቢ ሰፋ ያለ ማብራሪያ እንዲያገኝ ይረዳል። ብሎም፣ የኅዳግ ማስታወሻዎቹ ከዋናው የመጽሐፉ ጭብጥ ያፈነገጡ አይደሉም።
ለማሳያ፣ ገጽ 18፣ 22፣ 32፣ 35፣ 51፣ 78…
ላይ በኅዳግ ማስታወሻ የተካተቱ ገለጻዎችን መመልከት ይቻላል። ይኼ ሙከራ እንደ አርአያ ተቆጥሮ ሌሎች ደራሲዎች በትርጉም ሥራዎቻቸው ላይ ቢሞክሩት ጠቃሚ ነው የሚል ሃሳብ አለኝ።የሙድ ዓይነት ጸሐፊ፡- አንድን ጉዳይ/ ታሪክ በቁመናው ልክ ከመዘክዘክ፤ በወቅቱ የነበረውን ሙድ መተረክ ለድርሰት ሀሳቡ ግዝፈትን ይሰጣል። ለአብነት ያህል፡- አንኮበር ተጉዘን የአጼ ምኒልክን ቤተመንግሥት እየጎበኘን ነው እንበል፤ ‹‹የንጉሠነገሥቱን ሲናድር አይተን ተደመምን፤ ነካንም›› ከምንል ‹‹የንጉሠ-ነገሥቱን ሲናድር ለመንካት ተራኮትን›› ብለን ብንገልጽ ግዝፈት ይኖረዋል። ደራሲው፣ (ከሞላጎደል) ታሪኮቹን/ገጠመኞቹን በሙድ ለመግለጽ ክሯል፤ በጊዜው የነበሩ ሁኔታዎች የጫሩበትን ሥሜቶች በምስል መልክ ተርኳል።
ምሳሌ እንጥቀስ፡- ‹‹የጠፈር አለንጋዎች እርቃን ገላዎችን ሲገርፉ ሰማን።…. ቀጥሎ ለመላጨት ወደ ሌላ ክፍል ተነዳን።›› ገጽ 28፤ በማለት የእስረኛውን ውርክብ እና የካፖዎቹን ያፈነገጠ አሠራር ተርኳል። በሙድ የመተረክ ዘዬ፣ ዶ/ር ፍራንክልን
የረዳቸው ይመስለኛል። የሥነ-ልቡና እና ሥነ-አዕምሮ ይዘት ያለውን ድርሰት በጊዜው በነበረው ሙድ ላይ ተመርኩዘው የእስረኞችን ሁኔታ፣ ችግርና መፍትሄ ለመተንተን ጠቅሟቸዋል የሚል ዕምነት አለኝ። እዚህ ላይ ሙድ/ሁኔታ ለአንድ ርዕሰጉዳይ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው መዘንጋት የለብንም። ሙዶች/ሁኔታዎች ጉዳይን የመገንባት/ ወደ-ጉዳይነት የማደግ አቅም አላቸው። የጉዞና የሥነ-ልቡና እንዲሁም
የሥነ-አዕምሮ ድርሰቶች በሙድ መልክ ሲተረኩ ሃሳቡ ይገዝፋል ብዬ አምናለሁ። ደራሲው ከሙድ በመነሳት የተለያዩ መላምቶችን ማስቀመጥ ይችላል።እዚህ ላይ የተርጓሚው ድርሻ የሚናቅ አይደለም፤ የትርጉሙ መልክ ታሪኮቹን
በጥሬው መዶለት ሳይሆን፣ በጊዜው የነበሩ ሙዶችን/ሥሜቶችን በውብ ቋንቋ እያስደገፉ መተረክ ነው። እሰይ የሚያሰኝ ነው።
ንድፍ/methodology እና መቃን/
frame-work፡- በቀለም ትምህርት መስክ፣ ጥናታዊ ጽሑፍን ለማስኬድ ሁነኛ/ትክክለኛ ንድፍ፣ ብሎም መቃን እንደሚያስፈልግ ይታወቃል። ለአብነት፡- survey design, experimental design, correlational design, causal comparative/ex-postfacto design, case-study design…
ወዘተ. ተጠቃሽ ናቸው። እንዲሁም፣ ንድፍና መቃን ድርሰትን በአግባቡ ለማስኬድ ይረዳሉ።
ለማሳያ፡- ታሪክ፣ ፍልስፍና፣ ሥነልቦና፣ ሥነ-አዕምሮ… ወዘተ. በድርሰት ዓለም የተለመዱ ንድፍና መቃን ናቸው። ለጥቁምታ፡- ራሻዊያን ጸሐፊዎችን ብንመለከት፣ በድርሰቶቻቸው በሚስሉት ገጸ-ባሕሪይ በኩል የአንድን ፍልስፍናዊ ኅልዮት ሕልው መሆን፣ ወይም ውድቀት ለማሳየት ይሞክራሉ። ድርሰቱ በፍሬድሪክ ኒቼ ኅልዮት (theory)፣ ‹‹የሚኖርለት ለምን ያለው (ለ-ጠበቅ ተደርጋ ትነበብ) ሰው፣
ማንኛውንም እንዴት ይቋቋማል›› መሠረት ያደረገ ሲሆን፤ ባለታሪኩ በኅልዮቱ ልክ ከከበበው ጨለማ ወደ ብርሃን ይሸጋገራል። መውጫ፡- ‹‹ለምንን ፍለጋ›› ከታሪካዊ ዘገባ ይልቅ፣ የሙድ ጽሑፍ እንደሆነ ይሰማኛል። በትርጉም ሥራው ላይ በስፋት የተካተቱ የግርጌ ማስታወሻዎች ወገግታን ይፈጥራሉና ሌሎች ተርጓሚዎች ፈለጉን ይከተሉት እላለሁ። ከዚህ በዘለለ፣ ያለአግባብ የተጣመሩ ቃላት በትርጉም
ሥራው ላይ ሠፍረዋል። (ጥምር ቃላት፡-
ለምሳሌ ‹‹ሥጋ›› እና ‹‹ቤት›› የሚሉ ቃላት ሲጣመሩ - (ሥጋ-ቤት) - ትክክለኛ ፍቺ ያለው ቃል እንደሚፈጥሩ ይታወቃል፤ ነገር ግን በ‹‹ለምንን ፍለጋ›› ውስጥ በርካታ ቃላት ያለግብራቸው ተጣምረው ተገኝተዋል /ምናልባት በድንገት/።
 በንባብ ወቅት መታከትን ሊፈጥሩ እና ትርጉም ሊያዛቡ ይችላሉ። ‹ከልጅ ልጅ ቢለዩ› ነውና፣ ይኼ ሃቲት ንጡል ሳይሆን፤ ዋናውንና ትርጉሙን ሥራ በወፍ-በረር
የማየት ሙከራ ነው።

ኢትዮጵያ ወደከፋና የለየለት የእርስበርስ ጦርነት እንዳትገባ፣ በአገሪቱ ሰላም ለማስፈን የሚቻልበትን መንገድ በማፈላለግ፣ ከከፋ አደጋ ትታደጋት ዘንድ ለአሜሪካ ጥሪ ቀረበ። ጥሪውን ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ያቀረቡት በአሜሪካ የሚገኙ የኢትዮ-አሜሪካን ሲቪል ማህበራት
ናቸው።
ማህበራቱ በአሁኑ ወቅት ደብዳቤውን ለፕሬዚዳንት ባይደን ለመፃፍ የተነሳሱበትን ምክንያት ሲያስረዱም፤ በአገሪቱ በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ያለው የእርስበርስ ጦርነት በአለማቀፍ ማህበረሰብ፣ በአሜሪካ መንግስትም ሆነ በሌሎች ተፅዕኖ ማሳደር በሚችሉ አካላት ሁሉ ታውቆ በዲፕሎማቲክ መንገድ ጦርነቱን ለማስቆም እንዲችሉ ለማድረግ ታልሞ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
በፊደራል መንግስቱና በአማራ ከልል ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች መካከል ያለው ውጥረት ተባብሶ የትጥቅ ትግል ማስከተሉን ያወሳው የማህበራቱ ደብዳቤ፤ ይህ ችግር አፋጣኝ መፍትሄ ካላገኘ ወደ የእርስበርስ ጦርነት በማደግ ኢትዮጵያን ወደ ማተራመስና ለአፍሪካ ቀንድ ትልቅ ስጋት መጋረጡ አይቀሬ ኢትዮጵያ ወደከፋ የእርስበርስ ጦርነት እንዳትገባ አሜሪካ ትታደጋት ዘንድ ተጠየቀ መሆኑን አመልክቷል፡፡ አሜሪካ ይህንን ጦርነት የማስቆምና ሰብአዊ መብቶችን የመጠበቅ የሞራል ግዴታ እንዳለባትም ተጠቁሟል፡፡  

አሁን በአገሪቱ በስራ ላይ ያለው ብሄር ተኮር ፊደራሊዝም ሀገሪቱን በፍጥነት ከቁጥጥር ውጪ ወደሚሆን ሁከት እየከተታት እንደሆነም ማህበራቱ በደብዳቤያቸው መጠየቃቸውን የዘገበው ዶቼቪሌ የዜና አውታር አሜሪካ ተቀባይነት ያለው መንግስታዊ ሽግግር በማመቻቸት ለኢትዮጵያ አዲስ ህገ መንግስት የሚዘጋጅበት ሂደት እንድትደግፍ ጥሪ ማቅረባቸውን ገልጿል፡፡

Page 4 of 678