Administrator

Administrator

Monday, 06 April 2015 08:19

የፀሐፍት ጥግ

ከሞትክ በኋላ መረሳት የማትፈለግ ከሆነ አንድም ለመነበብ የሚበቁ ነገሮችን ፃፍ አሊያም ለመፃፍ የሚበቁ ነገሮችን ሥራ፡፡ ቤንጃሚን ፍራንክሊን ተሰጥኦ ብቻውን ፀሐፊ አያደርግም፤ ከመፅሐፉ ጀርባ ሰው መኖር አለበት፡፡ ራልፍ ዋልዶ ኢመርሰን ራሱን የማይመግብ አዕምሮ ራሱን ይበላል፡፡ ጎሬ ቪዳል የመፃፍ ክህሎት፤ ሌሎች ማሰብ የሚችሉበትን ሁኔታ መፍጠር ነው፡፡ ኢድዊን ስክሎስበርግ ድድብና ላለማሰብ ምክንያት አይሆንም፡፡ ስታኒስላው ጄርዚሌክ ብዕር የአዕምሮ ምላስ ነው፡፡ ሰርቫንቴስ ስለችሎታዬ ቅንጣት ታህል ጥርጣሬ ኖሮኝ አያውቅም፡፡ መፃፍ እንደምችል አውቅ ነበር፡፡ እየፃፍኩ እንዴት ሆዴን እንደምሞላ ብቻ ነው ማሰብ የነበረብኝ፡፡ ኮርማክ ማክካርቲ ሰው ብዙ በመፃፍ በወጉ መፃፍ ይለምዳል፡፡ ሮበርት ሳውዜይ ከእያንዳንዱ የሰባ መፅሃፍ ውስጥ ለመውጣት የሚፍጨረጨር ቀጭን መፅሃፍ አለ፡፡ ያልታወቀ ፀሐፊ ፀሐፊ ይመሰገን እንደሆነ ለማየት ሌላ የህይወት ዘመን ያስፈልገዋል፡፡ ጆርጅ ሉዊስ ቦርግስ ለራስህ በጣም ቀሽም ፅሑፍ የመፃፍ ዕድል ካልሰጠኸው በጣም ግሩም ፅሁፍ ለመፃፍ ትቸገራለህ፡፡ ስቲቨን ጋሎዌይ አንባቢውን ማሰልቸት ይቅር የማይባል ሃጢያት ነው፡፡ ላሪ ኒቬን

ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ባላገር አንድ የማያውቀው ጫካ አቋርጦ ወደ መንገዱ ሊወጣ ሲጓዝ፤ አንድ የንጉሥ ልጅ በፈረስ ሆኖ ሲንሸራሸር ባላገሩን ያገኘዋል፡፡ ባላገሩ እጅ አልነሳም ልዑሉን፡፡ አልተሸቆጠቆጠም፡፡
ልዑሉ በጣም ገረመው፡፡ በአገሩ ደንብ ንጉሥን አክብሮ ለጥ ብሎ እጅ መንሳት ነበረበት፡፡ ባያውቅ ነው ብሎ በመገመት፤
“እንደምን ዋልክ?” ይለዋል፡፡
“ደህና እግዚሐር ይመስገን” ይላል ባላገሩ፡፡
“ለመሆኑ ንጉሥ ማለት ምን ማለት እንደሆነ ታውቃለህ?”
“አላውቅም” አለ ባላገር፡፡
“እንግዲያው ና ፈረሴ ላይ ውጣ፡፡ አፈናጥጬ ይዤህ እሄዳለሁ፡፡ ንጉሥ ማለት በሄደበት ሁሉ ሰው እጅ የሚነሳው፣ መንገደኛ ቆሞ የሚያሳልፈው የተከበረ ሰው ነው። ስለዚህ ቀስ በቀስ ንጉሥ ምንና ማን እንደሆነ ይገባሃል” አለና ያን ባላገር አፈናጠጠው፡፡
ወደ ከተማ እየተቃረቡ መጡ፡፡
“እንግዲህ አሁን ልብ ብለህ አስተውል” አለ ልዑሉ፡፡
የከተማው ሰው ልዑሉን ሲያይ ወዲያው የሚሄደው ቆመ፡፡ የቆመው ለጥ እያለ እጅ ነሳ፡፡ ልዑል  ዝም ብሎ መንገዱን ይቀጥላል፡፡ ህዝም እየቆመ እጅ እየነሳ ማሳለፉን ቀጥሏል፡፡ ይሄኔ ልዑሉ፡-
“አንተ ባላገር፤ ንጉሥ ማን እንደሆነ አሁን ገባህ?” ሲል የጠቀው፡፡
ባላገሩም፤
“አዎን አሁን ገብቶኛል” አለ፡፡
ልዑሉ ቀጥሎ፤
“ማን ነው ንጉሡ?” አለና ጠየቀ፡፡
ባላገሩም፤  
“እንግዲህ ወይ እኔ ወይ አንተ ነና!” አለና መለሰ፡፡
*       *      *
ስለተፈናጠጡ ብቻ የነገሡ የሚመስላቸው አያሌ አይተናል፡፡ በተሰጣቸው ትርጓሜ - ነገር (Definition) መሠረት ብቻ ጉዳዮችን እየተረጎሙ የሚጓዙ የዋሃንንም አስተውለናል፡፡ ግራ ቀኙን ሳያዩ በተሰመረው መስመር ላይ ብቻ የሚነጉዱ፣ ወቅት የሚለወጥ የማይመስላቸውና ወቅትም የማይለውጣቸው በርካታ መንገዶችን ታዝበናል፡ “ሳይማር ያስተማረንን ገበሬ አንረሳውም” ብለው ሲያበቁ ከተማ ገብተው ከተሜ ሲሆኑ፤ የሚገነቡትን ህንፃ ብቻ ዐይን ዐይኑን እያዩ መሰረታቸውን የረሱ ዕልቆ መሣፍርት የሌላቸው መሆናቸውንም ገርሞን አይተናል፡፡ ጥንት “ሠፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! የረሱህን አልረሳናቸውም” ብለው ጀምረው ከነመፈጠሩም ያላስታወሱት ባለጊዜዎችንም ተመልክተናል፡፡ በህዝብ የሚምል የሚገዘት ፓርቲ፣ ድርጅት፣ ማህበር አገራችን አጥታ አታውቅም!
የፖለቲካ አየር የኢኮኖሚውን ንፋስ መከተሉ በዓለም ታሪክ እንግዳ ነገር አይደለም። የኢኮኖሚ ብሶት ወደ ፖለቲካ ምሬት መለወጡና የፖለቲካ ጥያቄን መውለዱም ሁለንተናዊ ዕውነታ ነው፡፡ ይሄ የቆረቆረው ፓርቲ፣ ድርጅት፣ ቡድን ወዘተ… ጥያቄውን አንግቦ መነሳቱና መልስ መሻቱ አይቀሬ ነው፡፡
ከጭፍን ጥላቻ ውጪ ይሄን ጥያቄ ማንሳት ዲሞክራሲያዊ መብት ነው፡፡ መብቱን የሚያውቅ፣ የገባውና የሚገባውን የሚያውቅ ዜጋ ያላት አገር የታደለች ናት! ይህንን ዕድል ለመጠቀም የሚችል ንቃተ ህሊናው የበለፀገ ዜጋ ሀገሩን በቅጡ ይታደጋታል ተብሎ ይገመታል፡፡ እንዲህ ያለ ዜጋ የገዛ ዐይኑን ጉድፍ ሳያነፃ ከወንድሙ ዓይን ጉድፍ አወጣለሁ ብሎ አይፍረመረምም፡፡ ራሱን ከሙስና አያድንምያላፀዳ ዜጋ፤ አገሩን ከሙስና አያድንም፡
ራሱን ዲሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ያላደረገ ታጋይ፤ ዴሞክራሲያዊና ፍትሐዊ ሥርዓትን እገነባለሁ ቢል ሐሳዊ ታጋይ ከመሆን አያልፍም፡፡ ራሱ ህገ - ወጥ የሆነ ኃላፊ፤ የህግ የበላይነትን ያስከብራል ብሎ ተስፋ ማድረግ ከእባብ ዕንቁላል እርግብ መጠበቅ ነው፡፡
የምርጫ ወቅት ላይ ብቻ ስለ ኢ-ወገናዊነት የሚሰብክ ሰሞነኛ ወይም የወረት መንገደኛ ፍሬው በቀላሉ አይጐመራም፡፡ ጧት የተነሳ ብቻ ነው የማታ አዝመራው የሚሰምርለት፡፡
ፀሐፍት እንደሚሉት፤
“የምርጫ ወቅት ሙስና፡- Fake የይስሙላ ፓርቲዎችን ተወዳዳሪ አስመስሎ ከማቅረብ፣ እስከ ድምጽ ስርቆት ሊሄድ ይችላል፡፡
“በዚህ ምክንያት ነው በብዙ የአፍሪካ አገሮች ምርጫ ከመነሻው እስከ መድረሻው በውዝግብ የታጀበ የሚሆነው!”
ይሄን ልብ ብሎ ያልተገነዘበ ዜጋ ቡድን፣ ድርጅት ለራሱም አይሆን፤ ለአገሩም አይበጅ፡ ይልቁንም ነቅቶ መጠበቅ፤ ድምፁን እንዳያጣ፣ እንዳይጭበረበር፣ ያግዘዋል፡፡ ያ ካልሆነ ህዝባዊ ገዥነቱን የሚያረጋግጥበትን ዋና አቅሙን፣ ሠረገላ ቁልፉን አጣ ማለት ነው፡፡ የሚከበርና የሚፈራ ህዝብ የሚኖረው መብቱን የሚያውቅና የሚያስከብር ሆኖ ሲገኝ ነው፡፡ መብቱን ሲሸራርፉበት እምቢ! ማለት ሲችል ነው፡፡ በደልን፣ ግፍን እያየ ዝም ሳይል ሲቀር ነው፡፡ የፖለቲካ ሙስናን አልቀበልም ማለት ሲችል ነው፡፡ አስተዳደራዊ ብልሹነትን አሻፈረኝ ማለት ሲችል ነው! ቢሮክራሲያዊ እንቅፋቶችን አልቀበልም ማለት ሲችል ነወ፡፡ ባላስደሰተኝ ነገር አላጨበጭብም ማለት ሲችል ነው፡፡ እስከዛሬ ባየናቸው የተቃውሞ ጉዞዎች ውስጥ አማራጭ የትግል ስልቶችን ሳይቀይሱ በአንድና አንድ ግትር ስልት ብቻ እንጓዝ ብለው ብቸኛ መንገድ የመረጡ ሰዎች ቢያንስ መጨረሻቸው አያምርም፡፡ ሁለተኛም ሶስተኛም መጓዣ መንገዶችን ገና በጠዋት ማዘጋጀት ይገባቸዋል፡፡ ፈረንጆቹ “ፕላን ቢ”፣ “ፕላን ሲ” እንደሚሉት ነው፡፡ በአማርኛ “ሁለት ባላ ትከል፤ አንዱ ቢሰበር ባንዱ ተንጠልጠል” እንደማለት ነው!



“ሉዓላዊነት” በሚል ሰበብ፣ አገር ውስጥ “በዜጎች ላይ ያሻኝን ብፈፅም ማንም አያገባው” ብሎ መዝመት አስቸጋሪ ሆኗል
“አሜሪካ፣ አውሮፓ ገብቻለሁ” ብሎ፣ በዘፈቀደ “የኤምባሲ አጥሮችን በመጣስ” ላይ ያተኮረ የተቃውሞ ስትራቴጂ አያዋጣም
እንግዳ ቁጥር 1
   “በመንግስት የሰፈራ ዘመቻ ከእርሻ ማሳዬ ተፈናቅያለሁ” የሚሉ አንድ የጋምቤላ ገበሬ፤ ከአዲስ አበባው የአራት ኪሎ ቤተመንግስት እስከ ለንደኑ የዌስትሚንስተር ፓርላማ ድረስ፣ “ቁንጮ ፖለቲከኞችን የሚያጨቃጭቅ አሳሳቢ ጉዳይ ይሆናል” ብሎ ማን ጠበቀ? እንዴትስ የ10 ቢሊዮን ብር ጥያቄ ሊሆን ይችላል? ለመንግስት፣ ፈፅሞ ያልተጠበቀ ትልቅ ፈተና እንደሚሆንበት አያጠራጥርም፤ “ዱብዳ” ነው። ለአንዳንድ ተቃዋሚዎች ደግሞ፣ ያልታሰበ ሲሳይ ነው፤ “በተዓምር የተገኘ መና”። በእውን እንዲከሰት ይቅርና በህልማችን እንዲመጣ ያልጠበቅነው ድንገተኛ ነገር ነው በማለት፤ እንደ “ዱብዳ” ወይም እንደ “ተዓምር” ቢቆጥሩት አይገርምም። ግን ለምን ድንገተኛ ሆነባቸው? ዘመኑን እለት በእለት እየተከታተሉ፤ ዓለምን ከዳር እስከ ዳር እየቃኙ፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሁኔታዎችን ለማናገናዝብ በቂ ጥረት አላደረጉም ማለት ነው።
እንግዳ ቁጥር 2
አሜሪካ ዋሺንግተን የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላይ ባነጣጠሩ የዳያስፖራ ተቃዋሚዎችና በኤምባሲው የፀጥታ ሰራተኞች መካከል አምባጓሮ የተፈጠረ ጊዜ ታስታውሳላችሁ? የፀጥታ ሰራተኛው የማስጠንቀቂያ ጥይት እንደተኮሰ፤ ተቃዋሚዎች ግቢውን ጥሰው በመግባት ባንዲራ እንዳወረዱ... ወዘተ የወቅቱ ትልቅ መነጋገሪያ ነበር። በዚሁ አላቆመም። በዋሺንግተንም ሆነ በአውሮፓ መዲናዎች፣ ተመሳሳይ ጀብዱ ለመፈፀም እንዳቀዱ የገለፁ አንዳንድ የዳያስፖራ ተቃዋሚዎች፣ “ሁነኛና አስተማማኝ የተቃውሞ ስትራቴጂ” የተገለጠላቸው ያህል ፈንጥዘዋል። ለብዙዎችም አሳማኝ ሆኖ ታይቷቸው ነበር። መንግስት በበኩሉ ከፍተኛ ስጋት እንዳደረበት፣ በወቅቱ ካወጣቸው መግለጫዎች መታዘብ ይቻላል።
እንደተጠበቀውም፣ በአሜሪካ እንደታየውን ክስተት ወዲያውኑ ለመድገም የወሰኑ የዳያስፖራ ተቃዋሚዎች፣ በስዊድን የኢትዮጵያ ኤምባሲን ጥሰው ለመግባት እንደሞከሩ ሲዘገብ ሰማን። ከዚያስ? ከዚያማ ኤምባሲ ጥሶ የመግባት ወሬ፣ እንደ ሰደድ እሳት ሲግለበለብ እንዳልሰነበተ ድንገት እልም ብሎ ጠፋ። ይሄውና ድምፁን ሳንሰማ ወራት ተቆጠሩ። ምን ተፈጠረ? ያ አንዳንድ የዳያስፖራ ተቃዋሚዎች የተዘመሩለትና መንግስት የሰጋበት፣ “የተቃውሞ ስትራቴጂ” ድንገት ኩምሽሽ ብሎ መጥፋቱ፤ ለተቃዋሚዎቹ “ዱብዳ”፣ ለመንግስት ደግሞ “ተዓምር” ሆኖ ሊታያቸው ይችላል። የዘመኑንና የአለምን ሁኔታ ባያገናዝቡ እንጂ፤ ነገሩ ድንገተኛ ባልሆነባቸው ነበር። እንዴት በሉ።
የኤምባሲው አምባጓሮ በተፈጠረበት ሰሞን፣ እዚያው ዋሺንግተን ውስጥ የአገሪቱን ፖለቲከኞች ዘንድ አሳሳቢ የነበሩ ሁለት ጉዳዮችን ብቻ ማስታወስ በቂ ይመስለኛል። አንደኛው፣ የፕሬዚዳንቱ ቤተመንግስትን ለአደጋ ያጋለጠ ድርጊት ነው - የኋይት ሃውስን አጥር ጥሶ የገባ ተጠርጣሪ፣ የፀጥታ ሰራተኞች፣ አነፍናፊ ውሾች፣ የጥበቃ መቆጣጠሪያ መሳሪያዎች ሳያግዱት፣ የፕሬዚዳንቱ ቢሮና መኖሪያ ቤት ወደሚገኝበት ህንፃ ገብቶ ከኮሪደር ኮሪደር ሲዟዟር እንደተያዘ በአገሪቱ የሚዲያ ተቋማት ሲዘገብ ምን የተፈጠረ ይመስላችኋል? የፖለቲካ ማዕበል።
ዋሺንግተን ቀውጢ ሆነች። ቀደም ሲል ሳይታወቁ የቆዩ ሌሎች የፀጥታ ጥበቃ ድክመቶች ከተደበቁበት እየፈለፈሉ የሚያወጡ ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች፣ ነገሩን የዋዛ አላዩትም። የአገሪቱ ኮንግረስ (ፓርላማ) በበኩሉ፣ ባለስልጣናትንና ባለሙያዎችን እያስጠራ በጥያቄ ለማፋጠጥ ጊዜ አልፈጀበትም። የቤተመንግስት የፀጥታ ኤጀንሲ ዳሬክተር፣ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከስልጣናቸው ተሰናበቱ። አሸባሪነት በገነነበት ዘመን፣ አጥር ተጥሶ የፀጥታ ሲፈጠር፣ እንደዋዛ አይታይም። በዚያ ላይ፣ በዋሺንግተን የኤምባሲዎችን ፀጥታ የመጠበቅ ሃላፊነት የማን ቢሆን ጥሩ ነው? የቤተመንግስት ፀጥታ ኤጀንሲ ነው፣ የኢንባሲዎችን ፀጥታ የሚቆጣጠረው። የኋይትሃውስ አጥር ተጥሶ፣ ከፍተኛ የፖለቲካ ቅሌት የወረደበት ይሄው ኤጀንሲ፤ እንደገና በየኤምባሲው ሌላ የፀጥታ አደጋ እንዲከሰት ፈቃደኛ የሚሆን ይመስላችኋል? የማይመስል ነገር!
ምን ይሄ ብቻ! ከኤምባሲ ጋር በተያያዘ፣ የአሜሪካ መንግስት ሌላ ተጨማሪ ራስ ምታት አለበት። ከ30 ዓመታት በፊት በኢራን እና በሊባኖስ ምድር የአሜሪካ ኤምባሲዎች ላይ የደረሰውን ጥቃት ስለማይረሱት ብቻ አይደለም። ከዚያ በኋላም ኬንያና ታንዛኒያ ውስጥ ትልልቅ ጥፋቶችን አስተናግደዋል። ይሄ አልበቃ ብሎ፤ በሊቢያ የአሜሪካ አምባሳደርን ጨምሮ የበርካታ አሜሪካዊያንን ሕይወት የቀጠፈው ጥቃት፣ እንደ እሳት እያንገበግባቸው እንደሆነ ለመረዳት ከባድ አይደለም። በኮንግረስና በፕሬዚዳንታዊ የምርጫ ዘመቻ ሳይቀር ላይ እንደ ትኩስ ጉዳይ ፖለቲከኞችን ዛሬ ድረስ ሲያጨቃጭቅ መስማት ትችላላችሁ!
“Benghazi Attack” ብለው የሰየሙትን ጥቃት፣ ኮንግረስ ውስጥ አራት ቋሚ ኮሚቴዎች ባለስልጣናትን፣ ምስክሮችንና ባለሙያዎችን እየጠሩ ለበርካታ ወራት በየፊናቸው ምርመራ ማካሄዳቸውንም አትርሱ። ይህም አልበቃም፤ ጉዳዩን የሚያጣራ ራሱን የቻለ ኮሜቴ እንዲቋቋም በኮንግረስ ስለተወሰነ፤ ይሄውና እስከዛሬ ምርመራው አለመቋረጡን ስትመለከቱ፤ ምን ያህል አክብደው እንደሚያዩት መገንዘብ ትችላላችሁ። ደግሞስ፣ በሊቢያ፣ በግብፅ፣ በቱኒዚያ እና በበርካታ አገራት ውስጥ፣ ለአሜሪካ መንግስት የኤምባሲዎች የፀጥታ ጥበቃ፣ እረፍት የማይሰጥ ስጋት እንደሆነ አናውቅም እንዴ? ለአውሮፓ መንግስታትም እንዲሁ ያሳስባቸዋል። ምናለፋችሁ? የአሜሪካና የአውሮፓ መንግስታት፣ ኤምባሲዎቻቸውን የፀጥታ ጥበቃ የሚነካ ነገር በቸልታ ወይም በዋዛ እንዲታለፍ አይፈልጉም። በዋና ከተሞቻቸው ውስጥ የሚገኙ የሌሎች አገራት ኤምባሲዎችም ላይ፣ ምንም አይነት ስጋት እንዲፈጠር አይፈቅዱም።
ምን ለማለት ፈልጌ ነው? ይህንን የዘመናችንና የአለምን ሁኔታ የሚያገናዝብ ሰው፤ “ኤምባሲዎች ላይ ያነጣጠረ የተቃውሞ ስትራቴጂ” ከአንድ ሰሞን ሆይሆይታ በኋላ፣ ድምፁ እልም ብሎ ቢጠፋ፤ “ዱብዳ” ወይም “ተዓምር” ሆኖ አይታየውም ለማለት ነው።                                  
ወደ ደቡብ አፍሪካ ቪዛ አስመታለሁ በማለት ሰዎችን አጭበርብረዋል ተብለው የተከሰሱ፣ የባሌስትራ ቁርጥራጭ ወርቅ ነው ብለው ብሔራዊ ባንክን አታልለዋል ተብለው የተከሰሱ፣ ሚስታቸውን ደብድበው ገድለዋል ተብለው የሚፈለጉ ሦስት ተጠርጣሪዎች፣ ከደቡብ ሱዳን፣ ከአረብ አገር እና ከጀርመን ተይዘው እንደመጡ ታውቃላችሁ።
ቀደም ብዬ ያነሳሁት የእርዳታ ጉዳይም፣ ከበድ ያለ ጉዳይ ነው። ብዙዎች ከባድነቱን ለማመን ይቸገሩ ይሆናል። ነገር ግን፣ የጋምቤላው ገበሬ፣ “ከእርሻ ማሳዬ በመንግስት የሰፈራ ዘመቻ ተፈናቅያለሁ፤ የእንግሊዝ መንግስት ለሰፈራ ዘመቻው እርዳታ በመስጠት ስለተሳተፈ ይጠየቅልን” በማለት በለንደን ያቀረቡት ክስ የዋዛ አይደለም። በስደት ኬንያ የሚገኙት እኚሁ ገበሬ በጠበቃቸው ባቀረቡት ክስ፣ የካሳ ክፍያ ቢጠይቁም፣ ጉዳዩ በዚህ ብቻ አላበቃም። እንግሊዝ ለኢትዮጵያ መንግስት የሚሰጠው እርዳታ፣ ከላይ እስከ ታች ተመርምሮ መጣራት እንደሚኖርበት ፍ/ቤቱ ተናግሯል። እርዳታው ቀላል እንዳይመስላችሁ። ከአሜሪካ በመቀጠል፣ ለኢትዮጵያ ዋነኛዋ እርዳታ ሰጪ የሆነችው እንግሊዝ፣ በየአመቱ ወደ 10 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ እርዳታ ትለግሳለች። በአንድ ገበሬ ክስ የተነሳ፣ የሃያሏ አገር መንግስት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲውን እንዲመረምር የፍርድ ቤት ጫና ሲመጣበት አስቡ። ከዚሁ ክስ ጋር ተያይዞ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በየአመቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬና እርዳታ የሚኛገኝበት ትልቅ ምንጭ ስጋት ላይ ሲወድቅ ይታያችሁ።
አስቸጋሪ ነው። መንግስት እንደዘወትሩ፤ “ይሄ የኒዮሊበራሎች ዘመቻ ነው” በማለት ለመከራከር ቢያስብ እንኳ፣ አመቺ አይደለም። ሶሻሊስቶች፣ አሜሪካንና እንግሊዝን ለማንቋሸሽ በሚዘወትሩት የፕሮፓጋንዳ ስልት፣ “የኒዮሊበራሎች ሴራ ነው” የሚል አባባል እያስተጋባ፣ አንድ ተራ ገበሬ ያቀረቡትን ክስ ለመከላከል ቢሞክር ትዝብት ላይ ከመውደቅ ያለፈ ውጤት አያገኝም። ይሄኛው የፕሮፓጋንዳ ስልት አላዋጣ ሲል፤ በአገራችን ባህል እንደተለመደው፣ “ይሄ የአንድ ግለሰብ ጉዳይ ነው” በማለት መንግስት ነገሩን ለማጣጣልና ለማስተባበል ቢሞክርስ? ይሄም አያዋጣውም። እንዲያውም በተቃራኒው፤ “እንዲህ አይነት ማስተባበያ፣ የመንግስትን ጥፋተኝነት ከማረጋገጥ አልፎ፣ ሰዎች ላይ ለሚደርስ ጉዳት ደንታ ቢስ መሆኑንም ያሳያል” የሚል ምላሽ ነው የሚያጋጥመው። የእያንዳንዱ ሰው መብት መከበር አለበት የሚለው መሰረታዊ የነፃነት አስተሳሰብ፣ በአሜሪካና በአውሮፓ አሁንም ድረስ ጠንካራ ነዋ።
በተቃራኒው፣ የእንግሊዝ መንግስትን ምላሽ ተመልከቱ - “ለሰፈራ ዘመቻ እርዳታ አንሰጥም። ለኢትዮጵያ መንግስት የምንሰጠውን የእርዳታ ትብብር፣ በየጊዜው እንመረምረዋለን። ወደፊትም እንመረምረዋለን። ውጤታማ ያልሆኑትን እየሰረዝን፣ ውጤታማ የትብብር መስኮችን በማጠናከር ነው የምንሰራው” ብሏል የእንግሊዝ መንግስት። እንግዲህ፤ በርካታ ነገሮች እንደድሮ ስላልሆኑ፤ የአገራችን መንግስት የዘመናችንንና የዓለምን ሁኔታ በማገናዘብ፣ የእንግሊዝን አይነት ምክንያታዊ አካሄድ ከወዲሁ ቢለማመድ አይሻለውም ትላላችሁ?
በሚዲያ ነፃነት ዙሪያም፣ ከዘመኑ ጋር ለመራመድ፣ ገና ሊለማመዳቸው የሚገቡ ቁምነገሮች አሉ። የቴሌቪዥን ጣቢያ ስርጭትን ለብቻው በሞኖፖል የያዘው የአገራችን መንግስት፤ በርካታ ሬድዮ ጣቢያዎችን እየተቆጣጠረና አዳዲስ ጣብያዎችን እየገነባ ቢሆንም፣ ለሁለት ለሦስት የግል የኤፍኤም ሬድዮ ጣቢያዎች ፈቃድ መስጠቱ በጎ ጅምር ነበር። በእርግጥ፣ ከ15 አመት በፊት የወጣው የብሮድካስት አዋጅ ላይ፣ ለሬዲዮ ብቻ ሳይሆን ለቴሌቪዢንም ጭምር፣ የግል የስርጭት ጣቢያ ለማቋቋም የሚያስችል ፈቃድ እንደሚሰጥ ይዸነግጋል። ግን ተግባራዊ አልሆነም። ወደፊትም ተግባራዊ አይሆንም ተብሏል። የማሰራጫ ጣቢያ ማቋቋም የሚችለው መንግስት ብቻ እንደሚሆንና፣ ለግል ድርጅቶች ቻናል እንደሚያከራይ የሚገልፅ አዲስ ረቂቅ ህግ ተዘጋጅቷል። እስቲ አስቡት። በዛሬው የቴክኖሎጂ ዘመን፣ እንደ ድሮው መንግስት ሁሉንም ነገር በሞኖፖል ተቆጣጥሮ ሊቀጥል ይፈልጋል? ለነገሩ፣ ከሬድዮና ከቴሌቪዢን በተጨማሪ፣ የጋዜጣ ስርጭትንም ካልተቆጣጠርኩ ብሎ አዲስ ህግ ወይም መመሪያ እንደሚያዘጋጅ ሲገልፅ ከርሞ የለ!
እንዴት ነው ነገሩ? ብዙ ነገሮች እንደድሯቸው እንዳልሆኑና ብዙ ነገሮች እንደተቀየሩ አልገባውም ማለት ነው? በመላ አገሪቱ በየቀኑ የሚሰራጨው የግል ጋዜጣና መፅሔት ስንት ቢሆን ነው? ምናልባት 10ሺ? እና የእነዚህን ጋዜጦች ስርጭት ለመቆጣጠር ይፈልጋል።
እስቲ ሁላችሁም፣ የመንግስት ሃላፊዎችም ጭምር፣ የየራሳችሁን ግቢ እና ጎረቤቶቻችሁን ይመልከቱ። ምን ይታያችኋል? የሳተላይት ቴሌቪዥን ዲሽ! ዲሽ የተከሉ ሳይሆን ያልተከሉ መቁጠር ይሻላል። ከግቢ ወጣ ብለው የየሰፈራቸውን ግራና ቀኝ ሲቃኙስ፣ በየጣሪያው ወደ ሰማይ ያንጋጠጡ ዲሾች አካባቢውን እንዳጥለቀለቁት አያዩም? ለዚያውም በትላልቅ ብቻ ሳይሆን በትናንሽ ከተሞችም ጭምር ነው። ይህ ብቻ አይደለም።
የቅርብ ጊዜ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ወደ ሁለት ሚሊዮን የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ኢንተርኔትን ይጠቀማሉ። አንዳንዱ ሰሞነኛ የሆሊውድ ፊልሞችንና እለት በእለት በአሜሪካ የሚሰራጩ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎችን በትኩሱ ከኢንተርኔት እየሸመጠጡ ይኮመኩማሉ። አዳዲስ ሙዚቃዎችን ያፍሳሉ። አንዳንዱ ደግሞ፣ ዘመን የማይሽራቸው ትልልቅ መፃህፍትን በገፍ ያካብታል። ወይም በየእለቱና በየሳምንቱ እየታተሙ በአለም ገበያ ቁንጮውን ቦታ የሚይዙ መፃህፍትን ከኢንተርኔት እየበረበረ ያከማቻል። አንዳንዶቹ ብልጦች፣ ለሙያቸው የሚጠቅሙ መጻሕፍትን፣ ጥናቶችንና የስልጠና ቪዲዮዎችን ይሰበስባሉ። በእርግጥ፣ እንዲህ አይነት የኢንተርኔት ተጠቃሚ ኢትዮጵያዊያን ሲደማመሩ፣ በቁጥር ጥቂት ሊሆኑ ይችላሉ። አብዛኛው ተጠቃሚስ?መጀመሪያ ላይ በዲቪ ሎተሪ አነሳሽነት ነው ብዙ ሰው የኢሜይ ደንበኛ የሆነው። ቀጥሎም በስካይፒ እና በዩቱብ። ከዚማ ፌስቡክ እና ረቀቅ ያሉ ሞባይሎች መጡና አዳሜ ወደ ኢንተርኔት ሰተት ብሎ እንዲገባ ሰበብ ሆኑለት። ዛሬ፤ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን፣ ኢንተርኔት ከዘወትር ሕይወታቸው ጋር እያዋሃዱት ነው። በየፊናቸው፣ ከመቶ ሺ እስከ ዘጠኝ መቶ ሺ የሚደርሱ ተከታታይ ደንበኞችን ለማፍራት የቻሉ በርካታ ዌብሳይቶችና የፌስቡክ ገፆች እንደተፈጠሩ ብቻ ማየት በቂ ይመስለኛል።
እንዲያም ሆኖ፣  መንግስት ዛሬም በጣት የሚቆጠሩት ጋዜጦችና መፅሔቶችን በአይነቁራኛ ከማየትና ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጣር ከመጣጣር አልተቆጠበም። ዘመኑ የኢንተርኔት እንደሆነ ጠፍቶት ነው? ወይስ፣ ኢንተርኔትን መቆጣጠር፣ ጋዜጣና መፅሔትን እንደመቆጣጠር ቀላል ስላልሆነ? በእርግጥ አንዳንድ ዌብሳይቶች ኢትዮጵያ ውስጥ በቀላሉ እንዳይታዩ መሰናክልና አጥር መዘርጋት አይከብድም። ነገር ግን፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የፌስቡክ ደንበኞች ዘንድ የሚደርሱ መረጃዎችን፣ ፅሁፎችን፣ ምስሎችንና ቪዲዮዎችን ለመቆጣጠር መሞከር ግን አስቸጋሪ ነው። ብዙ ገንዘብና ብዙ ጊዜ ማባከን ነው ትርፉ። እንደ ቻይና እንኳ መሆን አይቻልም። እንደ ሰሜን ኮሪያ አገሬውን ከአለም ነጥሎ በመቆለፍ አፍኖ መያዝም አያዛልቅም። ለጊዜው የአገራችን መንግስት በኢንተርኔት አለም ውስጥ ብዙም የአፈና አማራጮች የሉትም። ያው፤ የልማድ ነገር ሆኖ፣ የፈረደባቸው የግል ጋዜጦችና መፅሔቶችን ማስጨነቁን ግን አያቋርጥም - ትርጉም የለሽ ቢሆንም። ውጤት ለሌለው ነገር ጊዜውንና ገንዘቡን ያባክናል። ከዚህ ይልቅ፤ ለስልጡን የሚዲያ ነፃነት ቢጣጣርና ቢለማመድ አይሻለውም?
ነገሮች እንደድሮ አይደሉም።   

30 ኢትዮጵያውያን ከየመን ጅቡቲ ገብተዋል
    በየመን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላይ የተፈፀመው ጥቃት  በማን እንደተፈፀመ እየተጣራ እንደሆነና  ከየመን ወደ አገራቸው ለመመለስ በኤምባሲው በኩል ከተመዘገቡ ኢትዮጵያውያን ውስጥ 30 ዜጎች  ጅቡቲ መድረሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡ በየመን መዲና ሰንአ የሚገኘው  የኢትዮጵያ ኤምባሲ ላይ ጥቃት መፈፀሙን ተከትሎ ጥቃቱ በማን እንደተፈፀመ እየተጣራ እንደሆነ የገለፁት አቶ ተወልደ፤ በተፈፀመው ጥቃት በኤምባሲው ሰራተኞች ላይ ምንም የደረሰ  ጉዳት የለም ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በየመን የሚገኙ ዜጎች ተመዝግበው ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ባደረገው ጥሪ መሰረት፤ ከተመዘገቡት ውስጥ 12 ሴቶች፣ 11 ህፃናት እና 7 ወንዶች የተካተቱበት አንድ ቡድን ጅቡቲ መድረሱን ቃል አቀባዩ ጠቁመዋል፡፡
የመን ውስጥ በስደተኞች መጠለያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሳኡዲ የአየር ጥቃት ተደብድበው ህይወታቸው አልፏል በሚል የተሰራጩ ዘገባዎችን በተመለከተ አቶ ሙሉጌታ በሰጡት ምላሽ፤ “በኛ በኩል ባደረግነው ማጣራት በዚህ ሁኔታ የሞተ ሰው የለም” ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል፤ የየመኑ የሁቲ አማፂ ቡድን ከኢራን የሚያገኘውን የወታደራዊ ቁሳቁስ ድጋፍ በቀይ ባህር በኩል በማሻገርና ለአማፂያኑ የወታደራዊ ስልጠና ቦታዎችን በአገሯ ላይ በማመቻቸት በተደጋጋሚ ስሟ የሚነሳው ኤርትራ፤ ሰሞኑን ተመሳሳይ ውንጀላ በሳኡዲ የመገናኛ ብዙሀን ተደርጎብኛል በሚል በሰጠችው ምላሽ፤ ውንጀላው መሰረተቢስ እንደሆነ ገልፆ የወሬው ምንጭም የአፍሪካ ቀንድ አገራት ናቸው ስትል አጣጥላለች፡፡
አብዛኛውን የየመን ክፍሎች በመቆጣጠር የአገሪቱን መሪ ከስልጣን ያስወገደው የሁቲ አማፂያን ቡድን፤ ከኢራን ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚደረግለት የሚነገር ሲሆን የሚያገኘውንም ድጋፍ በማስተላለፍና ለወታደራዊ ስልጠና ቦታ በመስጠት ኤርትራ በተደጋጋሚ ስሟ እንደሚነሳ አገር እንደሆነች ይታወቃል፡፡ የመካከለኛው ምስራቅ የሚዲያ የምርምር ተቋም ከጥቂት አመታት በፊት “ኢራን በቀይ ባህር የእንቅስቃሴ አድማሷን እያሰፋች ነው” በሚል ርዕስ  ባወጣው መረጃ፤  ኢራን ለሁቲዎች የምታደርገው የወታደራዊ ቁሳቁሶች ድጋፍ በኤርትራ በኩል እንደሚያልፍ ጠቁሞ ኢራን ሁቲዎችን የምታሰለጥንበት ካምፕ ኤርትራ ውስጥ ከየጊንዳዕ ከተማ በስተምስራቅ ደንጎሎ የሚባል ቦታ እንደሚገኝ አስታውቆ ነበር፡፡ ሰሞኑን የሳኡዲ የመገናኛ ብዙሀን፤ ሁቲዎች ከኢራን ለሚያገኙት ድጋፍ ኤርትራ ትብብር ታደርጋለች ሲሉ ዘግበዋል፡፡
“ዘገባው ከሙያዊ ስነምግባር ያፈነገጠ ነው” በማለት ባለአስር ነጥብ መግለጫ ያወጣው የኤርትራ መንግስት፤ ዜናውን መሰረተ ቢስ ሲል ያጣጣለ ሲሆን የመረጃው ምንጮችም የአፍሪካ ቀንድ አገራት እንደሆኑ ገልጿል፡፡ “ሻባይት” የተባለው የኤርትራ መንግስት ድረገፅ በበኩሉ፤ የዚህ መረጃ ምንጮች አንዳንድ የስለላ ተቋማትና የኢትዮጵያው ህወሓት ነው ብሏል፡፡
የኤርትራ መንግስት ባወጣው ባለአስር ነጥብ አቋም ውስጥ፤ የየመን ጉዳይ የራሷ የውስጥ ጉዳይ ስለሆነ የትኛውንም የውጭ ሀይል በመደገፍ ኤርትራ እንደማትሰለፍ አስታውቋል፡፡
የሳኡዲ መንግሥት በበኩሉ፤ የሁቲ አማፅያን እንቅስቃሴ ለአገሬ ስጋት ናቸው በሚል  በየመን ወታደራዊ ድብደባ እየፈፀመ እንደምገኝ የሚታወቅ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስትም የሳኡዲን አቋም እንደሚደግፍ አስታውቋል፡፡

  • ‹‹የሥነ ምግብ ጥናቱ የትኛውንም ሃይማኖት በተለየ የሚመለከት አይደለም›› /አስተባባሪው/
  • ‹‹ሥጋወደሙን ከምግብ መቁጠር ሃይማኖታዊ ነጻነትንና ሥርዓትን የሚፃረር ነው›› /ምእመናን/

   ከውልደታቸው እስከ ስድስት ወራት ዕድሜአቸው ድረስ ያሉ የአገሪቱ ሕፃናት፣ ከእናቶቻቸው ጡት ወተት ውጭ ተጨማሪ ነገር ስለመውሰዳቸው የዳሰሳ ጥናት ለማካሔድ በሚል ለመረጃ ሰብሳቢዎች የተሰጠው ሥልጠና፣ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሕፃናት ከሚፈጸመው ሥርዐተ ቊርባን አኳያ የሥነ ምግብ ባለሞያዎችን ማከራከሩ ተገለጸ፡፡
በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሥነ ምግብ ዲፓርትመንት ባለፈው የካቲት ወር፣ የሕፃናት ጥቃቅን ንጥረ ምግብ(micro nutrients) እና ተያያዥ የጤና ችግሮችን አስመልክቶ በአገር አቀፍ ደረጃ ስለሚሰበሰቡ መረጃዎች ለሦስት ሳምንት የዘለቀ ሥልጠና በሰጠበት ወቅት፣ ‹‹አንድ ሕፃን እስከ ስድስት ወር ዕድሜው ድረስ ሥጋወደሙን ወይም ቁርባን ከተቀበለ  የእናቱን ጡት ወተት ብቻ እንደተመገበ (exclusive breast feeding) አንቆጥረውም፤ እንደ ተጨማሪ ምግብ ነው የምናየው፤›› በሚል በጥናቱ አስተባባሪ የተነሣው ሐሳብ ብዙዎቹን አጥኚዎች ክፉኛ እንዳከራከረ የሥልጠናው ተሳታፊዎች ይናገራሉ፡፡
አንድ ሕፃን ከልደቱ እስከ ስድስት ወር ድረስ መመገብ ያለበት በበቂ ንጥረ ነገሮች የበለጸገውንና በተስማሚነቱ መተኪያ የሌለውን የእናት ጡት ብቻ እንደኾነ በሕክምና ሳይንሱ ይመከራል፤ ይህም ተጨማሪ ምግብና ፈሳሽ ለመውሰድ የሕፃኑ ጨጓራና አንጀት ዝግጁ ባለመኾኑና ለጤና እክልም እንዳይጋለጥ በሚል እንደኾነ የሚያስረዱት የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስትና ተከታይ ባለሞያዎቹ፣ በሥርዓተ እምነታቸው ዕድሜ እና ጾታ ሳይለይ የአምላክ አማናዊ ሥጋ እና አማናዊ ደም እንደኾነ አምነው የሚቀበሉት ቅዱስ ቊርባን፤ ‹‹ተጨማሪ›› በሚል በሚሰበሰበው መረጃ ለማካተት መታሰቡንና ከሥነ ምግብ አንጻር መታየቱን በጥብቅ እንደሚቃወሙ ተናግረዋል፡፡
በሕክምናው ስድስት ወራት ያልሞላቸው ሕፃናት ሲታመሙ ሽሮፕ ወይም ክኒን እንዲሟሟ ተደርጎ ለተወሰነ ጊዜ መድኃኒት እንደሚሰጣቸውና ይህም ለመዋዕለ ዘመናቸው የተወሰነውን የእናት ጡት ወተት ብቻ የመመገብ ሥርዓት ያፈርሰው እንደኾነ ለአስተባባሪው ጥያቄ ማቅረባቸውን ያስታወሱት ባለሞያዎቹ፣ ‹‹በሐኪም ትእዛዝ ከኾነ ችግር የለውም፤ ሥርዐተ ምግቡን አያፈርሰውም ተብሎ ነው የሚታሰበው፤ ቁርባን ከወሰደ ግን ያፈርሰዋል›› የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ይናገራሉ፡፡ ይህም በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የሚታመንበት የሥርዐተ አመጋገቡ መግለጫ እንደኾነ ተነግሮናል የሚሉት ባለሞያዎቹ፣ ከሚመለከታቸው የሚኒስቴሩ አካላት ለማረጋገጥ ሲጠይቁ ግን ‹‹በዚኽ ጉዳይ መልስ መስጠት አልፈልግም›› እንደተባሉ ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ በሕፃናት ጤና አጠባበቅ ከአህጉሩ በቀዳሚነት ለምትጠቀስበት ስኬቷ፣ በሥርዓተ ሃይማኖቱ በብዙ ሚልዮን ለሚቆጠሩ ሕፃናት የሚፈጸመው ቊርባን ዕንቅፋት ይኾናል ብለው እንደማያምኑ ባለሞያዎቹ ይናገራሉ፡፡ በእምነቱ የተቀደሰ ትውፊት ከስድስት ወራት በፊት ያሉ ሕፃናትንም ቢኾን ማቁረብ ለመንፈሳዊና ሥነ ልቡናዊ ዕድገታቸው የመጨነቅ የጥሩ እናትነት ምልክት መኾኑን የሚያስረዱት ባለሞያዎቹ፣ በብዙ ሚልዮን የሚገመቱት ክርስቲያን ሕፃናት እስከ ስድስት ወራቸው ድረስ የእናት ጡት ወተት ብቻ የማይመገቡበት አንዱ ምክንያት ‹‹ስለሚቆርቡ ነው›› የሚል ድምዳሜ በዳሰሳ ጥናቱ እንደ አንድ ነጥብ ቢቀመጥ ለአገር የሚያሰጠው ገጽታ ከወዲኹ መጤን እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡
በቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ ሥርዓተ ቊርባን፣ ሕፃናት በተወለዱ ከ40 እና ከ80 ቀናቸው ጀምሮ የሚቀበሉትና ከአምላካቸው ጋር ያላቸውን አንድነት የሚያረጋግጡበት የእምነታቸው አክሊልና ፍጻሜ ነው ያሉት ባለሞያዎቹ፣ ከስድስት ወራት በፊት ያሉ ሕፃናትን አመጋገብ ያፈርሳል የሚለው የጥናቱ ውጤት በሒደት የኅብረተሰብ ጤና ትምህርት መርሐ ግብር አካል ተደርጎ ሊሠራበት ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው አልሸሸጉም፡፡ ይህም የሃይማኖት ነጻነትን የሚጋፋ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ዶግማ፣ የምእመናኑን መንፈሳዊ ሕይወት የሚያጠፋና የሚደመስስ፣ እንዲኹም ለባዕድ አስተሳሰብም አሳልፎ የሚሰጥ በመኾኑ ፈጽሞ ተቀባይነት እንደማይኖረውና በጽኑ እንደሚያወግዙት ገልጸዋል፡፡
‹‹መረጃውን ለእናንተ ከነገሯችኹ ሰዎች በላይ ለምንሠራው ሥራ ሓላፊነት ይሰማናል›› ያሉት በኢንስቲትዩቱ የሥነ ምግብ ዲፓርትመንት የሥልጠናው አስተባባሪ ለአዲስ አድማስ በስልክ እንደተናገሩት፣ ጥናቱ የተወሰነ ሃይማኖትን የሚመለከት አይደለም፤ ዓላማውም ምን ያኽል ሕፃናት እስከ ስድስት ወር ድረስ የእናት ጡት ብቻ ወስደዋል የሚለውን ለማወቅ ብቻ በመኾኑ ከሃይማኖት ጋራ የሚያያዝ ትንታኔ የሚሰጠበት አይደለም፡፡
‹‹ለሕፃኑ ከውልደቱ ጀምሮ እስከ ስድስት ወሩ ድረስ ከእናት ጡት ውጭ የተሰጠው ማንኛውም ነገር አለ ወይ?›› የሚል ጥያቄ ‹‹በሃይማኖት ሥርዓትም ቢኾን›› በመረጃ ሰብሳቢዎቹ መጠየቅ እንዳለበት በሥልጠናው ላይ በአጽንዖት መነገሩን የሚጠቁሙት አስተባባሪው፤ በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ለሕፃናት ከሚፈጸመው ቁርባን አንጻር ከአንድ ተሳታፊ ጥያቄ መነሣቱን አረጋግጠዋል፡፡
‹‹በሃይማኖት ሥርዓትም ቢኾን ብለን ጥያቄ ስንጠይቅ ኦርቶዶክስ ሊኾን ይችላል፤ ሙስሊም ሊኾን ይችላል፤ ባዕድ አምልኮ የሚከተል ሊኾን ይችላል፤ እኛ እርሱ አይደለም የሚያሳስበን፤ በሃይማኖታዊ ሥርዓትኮ ሥጋወደሙ ብቻ አይደለም፤ ልጆች ሲታመሙ ጠበልም ምንም በተከታታይ አብዝቶ ይሰጣል፤ ይህም ኾኖ ወላጆች የእናት ጡት ብቻ ነው የመገብነው ይላሉ፤ ጤና አዳም ውኃ ውስጥ አድርገው ይሰጡና ምንም አልሰጠንም ይላሉ፡፡ በዚኽ ኹኔታ የጤና ችግር የሚያጋጥማቸው ሕፃናት ይኖራሉ፤ ከኦርቶዶክስ እምነት ጋር ብቻ የተያያዘ አይደለም፤ ነገሩ ተገቢው ግምት ስለማይሰጠው በየትኛውም ሃይማኖት የሰጣችኹት ነገር አለ ወይ? ብለን እንጠይቃለን፡፡ ጥያቄው እንዲኽ ያሉ ነገሮችን ለማስተካከል ነው፤ ምክንያቱም አገሪቱ የሕፃናት ሕመምና ሞት መጠንን ማሻሻል ብትችልም የሚፈለገውን ያኽል መሔድ አልተቻለም፡፡ ስለዚኽ በሃይማኖታዊ ሥርዓትስ የሰጣችኹት ነገር የለም ወይ? ምን? የሚል ጥያቄ በመጠይቁ ተካትቷል፤›› ሲሉ አስተባባሪው አስረድተዋል፡፡  

ከኦባማ ቀጥሎ በአሜሪካ ከፍተኛው ደመወዝ ተከፋይ ነበሩ
ከ2ሺ በላይ የተሳኩ ቀዶ ህክምናዎችን አከናውነዋል
ወንድሞቻቸው፡- ፕሮቶን፣ ኒውትሮን፣ ዲዩትሮን፣ ኤሌክትሮን እና ፖሲትሮን ይባላሉ

ትውልደ ኢትዮጵያዊው ዶክተር ኤሌክትሮን ክበበው፤ ለ33ኛ ጊዜ በመካሄድ ላይ በሚገኘው የ2015 “የዓመቱ የዓለማችን ልዩ ስም” ውድድር ላይ ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት በቀዳሚነት እየመሩ እንደሆነ አዘጋጆቹ አስታውቀዋል፡፡
በአለማቀፍ ደረጃ በሚካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ዘንድሮም የተለያዩ አገራት ዜጎችና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ 64 ግለሰቦች ያልተለመዱ ስሞች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን ኢትዮጵያዊው ዶ/ር ኤልክትሮን ክበበው፤ በ1ሺህ 132 ድምጽ፣ በ89.6 በመቶ ውጤት በቀዳሚነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በኢሜልና በተለያዩ መንገዶች ከቀረቡለት በርካታ ለየት ያሉ ስሞች 64 ያህሉን በመምረጥ፣ ለአንድ ሳምንት ያህል በድረ ገጽ አማካይነት ድምጽ እንዲሰጥባቸው የሚያደርገው የውድድር ኮሚቴው፤ የመጨረሻውን ውጤት ከጥቂት ቀናት በኋላ ይፋ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
የሰማይ እንሽላሊት፣  ጣፋጭ ቡና፣ ዳላስ፣ ቶክዮ፣ ቴኒስ እና የመሳሰሉ የአገር፣ የቦታ፣ የእቃ፣ የሰብል ወዘተ መጠሪያዎችን የያዙ የተለያዩ አገራት ዜጎች በዘንድሮው ውድድር እንደተሳተፉ አወዳዳሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
በዘንድሮው ውድድር ከፍተኛ ድምጽ በማግኘት በመምራት ላይ ለሚገኙት የ47 አመቱ ዶ/ር ኤሌክትሮን ይህን ስም ያወጡላቸው፣ ኤሌክትሪካል ኢንጂነር የሆኑት ኢትዮጵያዊው አባታቸው አቶ ክበበው ነበሩ፡፡
ልጆቻቸው የእሳቸውን ፈለግ ተከትለው በሳይንሱ ዘርፍ ላይሰማሩ ይችላሉ የሚል ስጋት ያደረባቸው አቶ ክበበው፤ በልጆቻቸው ልቦና ውስጥ ገና በለጋ እድሜያቸው የሳይንስን ስሜት ለማስረጽ በማሰብ ነው፣ ባልተለመደ ሁኔታ ለልጆቻቸው ከኤሌክትሪሲቲ ጋር የተያያዙ ስሞችን ያወጡት፡፡
አቶ ክበበው፤ ለአምስቱ ልጆቻቸው ፕሮቶን፣ ኒውትሮን፣ ዲዩትሮን፣ ኤሌክትሮን እና ፖሲትሮን የሚሉ ስሞችን አውጥተዋል፡፡ ዶ/ር ኤሌክትሮን በስማቸው ብቻ አይደለም የሚለዩት፡፡ ከስማቸው በላይ ብዙዎችን ያስገረመው፣ በህክምና ሙያቸው የአሜሪካ መንግስት የሚከፍላቸው ዳጎስ ያለ ደመወዝ ነው ይላል ድረ-ገጹ፡፡
ከአራት አመታት በፊት “ዊኪኦርግቻርትስ” የተባለ ተቋም “የአመቱ የአሜሪካ መንግስት 1000 ከፍተኛ ደመወዝ ተከፋዮች” በሚል ባወጣው ዝርዝር ውስጥ፣ ዶ/ር ኤሌክትሮንን ከአሜሪካው ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ቀጥሎ ከፍተኛ ደመወዝ የሚያገኙ የመንግስት ሰራተኛ በማለት በሁለተኛነት አስቀምጧቸዋል፡፡
በአዲስ አበባ በሚገኘው ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት የተማሩት ዶ/ር ኤሌክትሮን ክበበው፤ በአሜሪካ ሳንፍራንሲስኮ ከሚገኘው ዪኒቨርሲቲ ኦፍ ካሊፎርኒያ በህክምና የተመረቁ ሲሆን የአሜሪካን ቦርድ ኦፍ ሰርጀሪን የቀዶ ህክምና ሰርተፊኬትም አግኝተዋል፡፡
ላለፉት 20 አመታት በሳንፍራንሲስኮ በኢንዶክሪንና ታይሮይድ ካንሰር ዘርፍ የአጠቃላይ ቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ዶክተሩ፤ በአሜሪካ ብሄራዊ የካንሰር ኢንስቲትዩት፣ የካንሰር ምርምር ማዕከል የኢንዶክራይን ኦንኮሎጂ ቅርንጫፍ ሃላፊ ሲሆኑ የካንሰር ጄኔቲክስ ክፍሉንም በበላይነት በመምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
ዶክተሩ በእስካሁኑ የሙያ ዘመናቸው ከሁለት ሺህ በላይ የተሳኩ ቀዶ ህክምናዎችን ያከናወኑ ሲሆን ከ150 በላይ የጥናት ጽሁፎችንና መጽሃፍትን ለህትመት እንዳበቁ “ብሬኪንግጎቭ” የተሰኘ ድረገፅ አመልክቷል፡፡

የአፍሪካ ሀገራትን አጠቃላይ እንቅስቃሴና ተጨባጭ እውነታ በጥናት እየፈተሸ ደረጃ በመስጠት የሚታወቀው “አፍሪካ ክራድል” ድረገፅ፤ ሰሞኑን 10 ተፅዕኖ ፈጣሪ የአፍሪካ አገራትን ይፋ ያደረገ ሲሆን ኢትዮጵያ ከደቡብ አፍሪካ በመቀጠል ሁለተኛዋ ተፅዕኖ ፈጣሪ አገር ተብላለች፡፡ የሀገራቱ የተፅዕኖ ፈጣሪነት ደረጃ የተሠጠው በጦር ሃይል፣ በዲፕሎማሲ እና በአለማቀፍ ደረጃ ባላቸው እውቅና ሲሆን የመጀመሪያ ደረጃ የተሠጣት ደቡብ አፍሪካ በአህጉሪቱ ብቸኛ የ “ቡድን 20 እና የ “BRICS” አባል ሀገር እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ቀዳሚ የንግድ ሸሪክ መሆኗ ለደረጃው አብቅቷታል ተብሏል፡፡
የደቡብ አፍሪካ ስም ሲነሳ የማንዴላ የአፓርታይድ ተጋድሎ አብሮ እንደሚነሣ የጠቆመው ሪፖርቱ፤ ዛሬ በሀገሪቱ ለተገነባው ዲሞክራሲያዊ ስርአት የማንዴላና ተከታዮቻቸው የእነታቦ ኢምቤኪ አስተዋጽኦ የጐላ እንደሆነ ጠቁሟል፡፡
በተፅዕኖ ፈጣሪነት ሁለተኛ ደረጃ የተሠጣት ኢትዮጵያ፤ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስሟ 44 ጊዜ ያህል መጠቀሱን፣ በታሪክ፣ ቅኝ ባለመገዛት፣ በጦር ሃይል፣ በፖለቲካና ዲፕሎማሲ ወደር የለሽ ታሪክና ተሞክሮ እንዳላት በማውሳት በዚህ ረገድ ከአፍሪካ አገራት የሚስተካከላት እንደሌለ ሪፖርቱ ጠቁሟል። አገሪቱ በአድዋ ጦርነት የተቀዳጀችውን ድል ተከትሎ ከ20 በላይ የሚሆኑ የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን የባንዲራ ቀለማት በተለያየ ቅርፅና ይዘት ለመጠቀም እንደተገደዱ፣ የቡና የትውልድ አገር እንዲሁም፣ የሰው ዘር መገኛ መሆኗን፣ የራሷ የቀን አቆጣጠርና ፊደላት እንዳላትም የጠቆመው ሪፖርቱ፤ ነዳጅ ሳይኖራት ከድህነት ለመውጣት የምታደርገው ጥረት ኢኮኖሚዋን በከፍተኛ መጠን እያሳደገው መሆኑን፣ በጦር ሃይልም ቢሆን ጠንካራ ሃይል ከገነቡ የአፍሪካ ሀገሮች ተጠቃሽ እንደሆነች አመልክቷል፡፡
ሀገሪቱ ለወደፊቱ በአለም ላይ ተፅዕኖ ይፈጥራሉ ተብለው ተስፋ ከሚጣልባቸው የአፍሪካ ሀገራት አንዷ እንደምትሆንም ሪፖርቱ ተንብይዋል።
ከኢትዮጵያ ቀጥሎ ግብፅ በ3ኛ ደረጃ ተፅዕኖ ፈጣሪ ተብላለች፡፡ በርካታ የተማሩ ሰዎች አሏት የተባለችው ኬንያ 4ኛ ደረጃ ሲሰጣት፣ የአለማቀፍ ኩባንያዎች መቀመጫ የተባለችው ሞሮኮ 5ኛ፣ ቀዳሚ የኢኮኖሚና የሃይል ባለቤት የተባለችው ናይጄሪያ 6ኛ፣ ውጤታማ የኢኮኖሚ ገበያ ስርአት ባለቤት እንደሆነች የተነገረላት ኡጋንዳ 7ኛ፣ዜጎቿ ከእርስ በእርስ ግጭት ወጥተው በፍቅር ይኖሩባታል የተባለችው ሩዋንዳ 8ኛ፣ ህዝቧ ፈሪሃ አምላክ ነው የተባለችው ዚምባቡዌ 9ኛ ሲሆኑ በመጨረሻም የተረጋጋ የኢኮኖሚ ባለቤት የተባለችው አልጄሪያ 10ኛ ደረጃ ተሰጥቷል፡፡
 በአፍሪካ ተፅዕኖ ፈጣሪነት፡፡      

Saturday, 28 March 2015 10:17

የፍቅር ጥግ

አንዳንዴ ለዓይን የተሰወረውን ልብ ያየዋል፡፡
ኤች ጃክሰን ብራውን ጄአር.
ፍቅር ማለት ራስን ያለ ዋስትና መስጠት ነው፡፡
አኔ ካምቤል
አበባ ያለ ፀሐይ ብርሃን አያብብም፤ ሰው ያለ ፍቅር አይኖርም፡፡
ማክስ ሙለር
የፍቅር የመጀመሪያ ተግባሩ ማድመጥ ነው፡፡
ፓውል ቲሊች
ፍቅር፣ ዕድሜ፣ ገደብና ሞት አያውቅም፡፡
ጆን ግላስዎርዚ
የሌላው ሰው ደስታ የናንተ ደስታ ሲሆን ያኔ ፍቅር ይባላል፡፡
ላና ዴል ራይ
ማፍቀር ያለባችሁ ብቸኛ ስትሆኑ አይደለም፤ ዝግጁ ስትሆኑ ነው፡፡
ያልታወቀ ሰው
ለዘላለም እንዲዘልቅ የምትሹትን ነገር አታጣድፉት፡፡
ያልታወቀ ሰው
10 የማፍቀሪያ መንገዶች፡- ማድመጥ፣ መናገር፣ መስጠት፣ መፀለይ፣ መመለስ፣ መጋራት፣ መደሰት፣ ማመን፣ ይቅር ማለት፣ ቃል መግባት፡፡
ዊል ስሚዝ
በዓይኖቻችሁ ሳይሆን በልባችሁ አፍቅሩ፡፡
ያልታወቀ ሰው
ፍቅር አደገኛ የአዕምሮ በሽታ ነው፡፡
ፕሌቶ
ፍቅር ፍፁም እንዲሆን መጠበቅ የለብንም፤ እውነተኛ መሆን ብቻ ነው ያለበት፡፡
ያልታወቀ ሰው
በፍቅር መውደቅ፤ ደካማ አማልክት ያለው ሃይማኖት መፍጠር ነው፡፡
ጆርጅ ሉይስ ቦርግሰ
ለዓለም አንድ ሰው ብትሆኑም፣ ለአንድ ሰው ግን ዓለም ልትሆኑ ትችላላችሁ፡፡
ያልታወቀ ሰው

Saturday, 28 March 2015 10:05

የሲኒማ ጥግ

ሴት ተዋናዮች ስለሙያቸው)
በተዋናይነቴ እጅግ አስደሳቹ የትወና ክፍል ዳይሬክተሩን ማስደሰት ነው፡፡ ሁሌም ዳይሬክተሬን ማስደሰት እፈልጋለሁ፡፡
ጆን አን ቼን
ጠንክሬ መስራቴና ግሩም ሥልጠና ማግኘቴ ከአንዳንድ ተፎካካሪዎቼ የተሻልኩ ተዋናይት እንድሆን አስችሎኛል፡፡
ፓላ ኔግሪ
እንደሌላ ሰው የምዘፍን ከሆነ ጨርሶ መዝፈን አያስፈልገኝም፡፡
ቢሊ ሆሊዴይ
ሰዎች ሁለት ነገሮችን ፈጽሞ አይረሱም፡- የመጀመሪያ ፍቅራቸውንና ቀሽም ፊልም ለመመልከት የከፈሉትን ገንዘብ፡፡
አሚት ካላንትሪ
ተዋናይት መሆን አልፈልግም ነበር፡፡ የጥርስ ሃኪም መሆን ነበር ፍላጐቴ፤ ነገር ግን ህይወት የሚያመጣላችሁን አታውቁትም፡፡
ሶፍያ ቬርጋራ
ተዋናይት የምትተውነው ሴትን ብቻ ነው። እኔ ተዋናይ ነኝ፤ ምንም ነገር ልተውን እችላለሁ፡፡
ውፒ ጐልድበርግ (ሴት ተዋናይት)
በዘጠኝ ዓመት ዕድሜዬ ባልጀምር ኖሮ ተዋናይት እሆን ነበር ብዬ አላስብም፡፡
ክሪስቲን ስቴዋርት
ስጀምር ተዋናይት የመሆን ወይም ትወና የመማር ፍላጐት አልነበረኝም፡፡ ዝነኛ መሆን ብቻ ነበር የምፈልገው፡፡
ካታሪን ሄፕበርን
አምስት ዓመት ሲሆነኝ ይመስለኛል ተዋናይት ለመሆን መፈለግ የጀመርኩት፡፡
ማርሊን ሞንሮ
በተዋናይትነት ስኬታማ ለመሆን ሰብፅና በጣም ወሳኝ ነገር ነው፡፡
ማ ዌስት
እስከ 45 ዓመቴ ድረስ ፍቅር የያዛት ሴት ሆኜ መጫወት እችላለሁ፡፡ ከ55 ዓመቴ በኋላ አያት ሆኜ እተውናለሁ፡፡ በሁለቱ መካከል ያሉት 10 ዓመታት ግን ለሴት ተዋናይ አስቸጋሪ ነው፡፡
ኢንግሪድ በርግማን
ዝነኛ ተዋናይት መሆን የትልቅነት ስሜት ሊፈጥርባችሁ ይችላል፡፡ ግን እመኑኝ…ቅዠት ነው፡፡
ጁሊቴ ቢኖቼ

   ናይጀሪያ በዛሬው ዕለት የምታከናውነውን ፕሬዚዳንታዊና የፓርላማ ምርጫ ከቦኮ ሃራም ጥቃትና ከውጭ ሃይሎች ጣልቃ ገብነት ለመከላከል እንዲሁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ  በሚል ካለፈው ረቡዕ ምሽት ጀምሮ ሁሉንም የባህርና የየብስ ድንበሮቿን መዝጋቷን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
የናይጀሪያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ፓትሪክ አባ ሞሮ ለቢቢሲ እንደገለጹት፣ የሌሎች አገር ዜጎች ድንበር አቋርጠው በመግባት በአገሪቱ ምርጫ ድምጽ ለመስጠት እንዳቀዱ የሚያመለክቱ መረጃዎች በመገኘታቸው፣ ምርጫውን ከውጭ ጣልቃ ገብነቶች ለመከላከል ሲባል ድንበሮቹ ተዘግተዋል፡፡
ቦኮ ሃራም በተባለው የአገሪቱ ጽንፈኛ ቡድን ላለፉት ስድስት አመታት ሲፈጸሙ የቆዩ ጥቃቶችን በመሸሽ ወደ ጎረቤት አገራት የተሰደዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ናይጀሪያውያን፣ በዛሬው ምርጫ ድምጽ መስጠት እንደማይችሉም ዘገባው አስታውቋል፡፡
ባለፉት ስድስት ሳምንታት የአገሪቱ ሃይሎች በአሸባሪው የቦኮሃራም ቡድን ቁጥጥር ስር የነበሩ የድንበር አካባቢዎችን መልሰው መያዝ ቢችሉም፣ በተለይ በሰሜን ምስራቃዊ የአገሪቱ አካባቢዎች ሰርጎ ገቦች ድንበር ጥሰው ገብተው ምርጫውን ያደናቅፋሉ በሚል ስጋት መንግስት ሁሉንም የአገሪቱ ድንበሮች ለመዝጋት መወሰኑን ዘገባው ገልጧል፡፡
ምርጫው በሰላማዊ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ለማስቻል ሲባል፣ ሁሉም የአገሪቱ ድንበሮች እስከ ዛሬ እኩለ ሌሊት ድረስ ዝግ ሆነው እንደሚቆዩና ቦኮ ሃራም በሚንቀሳቀስባቸው ቦርኖ፣ ዮቢና አዳማዋ ግዛቶች የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንደተጣለም ተዘግቧል፡፡
የቦኮ ሃራምን ጥቃት የመቋቋም ቁርጠኝነትና ብቃት ያንሳቸዋል በሚል በስፋት ሲተቹ የቆዩት ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን፣ በጸጥታ ስጋት ለሳምንታት ተራዝሞ  ዛሬ በሚካሄደው ምርጫ ከተቀናቃኛቸው የቀድሞው የጦር መሪ ሙሃማዱ ቡሃሪ ብርቱ ፉክክር እንደሚጠብቃቸው ቢቢሲ ጠቁሟል፡፡
ፕሬዚዳንት ጉድላክ ጆናታን፤ ጦራቸው በቦኮ ሃራም ቁጥጥር ስር የሚገኙ የአገሪቱ ግዛቶችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ውስጥ እንደሚያደርግ ባለፈው ሳምንት ቢናገሩም፤ ቦኮ ሃራም እስከ 11 ዓመት ዕድሜ ያላቸው 500 ህጻናትን ዳማሳክ ከተባለችው የአገሪቱ ከተማ አፍኖ መውሰዱን ቢቢሲ ባለፈው ማክሰኞ ዘግቧል፡፡