Administrator

Administrator

ስለዒድ አል-አድሐ “ዐረፋ” በዓል ስናስብ ሦስት ነገሮች ቀድመው ይታወሱናል። መስዕዋትነት፣ መታዘዝ እና መተጋገዝ። አባት ልጁን ለመስዕዋት ያቀረበበት፤ ልጅ የአባቱን ትዕዛዝ የፈጸመበት፤ ሙስሊሞች የመተጋገዝን እሴት ለዓለም የገለጡበት በዓል ስለሆነ “ዐረፋ” በሕዝበ-ሙስሊሙ ዘንድ ትልቅ ትርጉም አለው።
እስማኤል ለነብዩ ኢብራሂም የመጀመሪያ እና ተወዳጅ ልጃቸው ነው። አላህ (ሱ.ወ.) ይሄን ተወዳጅና የመጀመሪያ ልጅ እንዲሠዉለት ሲጠይቃቸው ታዘዙ እንጂ ወደኋላ አላሉም። ለመታዘዝ የሞከሩት ነገሩ ቀላል ሆኖ አይደለም። ልጅን ያህል ነገር መስዕዋት ማድረግ ምኑ ይቀላል? የአባትነት ስሜት ይተናነቃል። የሰይጣን ሹክሹክታ ይፈታተናል። የቤተዘመድን ወቀሳ እና የጎረቤትን አስተያየት መቋቋምም ይከብዳል። ነብዩ ኢብራሒም፥ በዚህ ሁሉ አጣብቂኝ ውስጥ አንድ ሐቅ ተገልጦላቸዋል። ከራስ ስሜት፣ ከሰው ሐሜት እና ከወዳጅ ፍላጎት የሚልቅ ታላቅ ዓላማ እንዳለ አምነዋል። ስለዚህም በፈተና ውስጥ ጸንተው ቆሙ፤ ቆራጥነታቸውም በተግባር ታየ።
ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው። የሚወዱትን ነገር እንኳን ሳይቀር ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት ሀገር ትበረታለች። እስማኤላቸውን ለመስጠት የማያመነቱ ዜጎች የሞሉባት ሀገር ጽኑ ናት።
የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም “ሀገርነት እና ሉአላዊነት” ይሰኛል። ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው። ሉአላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆም፤ በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል ነው።
የእውነት ኢትዮጵያ ሲያልፍላት ማየት የምንሻ ከሆነ ምኞታችን በተግባር ይገለጥ። የሀገር ኩስመና ካሳሰበን ለግዝፈቷ እንድከም። ያጎበጣትን የድህነት ቋጥኝ ለመሸከም ትከሻችንን እናመቻች። ጎተራዋ እንዲሞላ እጃችን አፈር ይንካ። የጠየመ ገጽዋ እንዲፈካ በሥራ ሌት-ተቀን እንሰለፍ። የተቀማ ክብሯ እስኪመለስ ድርሻችንን እንወጣ። ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዕዋት ለመሆን አናመንታ።
የዐረፋ በዓል የመታዘዝና የመስዕዋት ብቻ ሳይሆን የመደጋገፍና የመተጋገዝ በዓል ጭምር ነው። በዐረፋ ከሚከናወነው እርድ አንድ ሦስተኛው ለምስኪኖች እንዲሰጥ የእስልምና አስተምህሮ ያዛል። በዐረፋ ሕዝበ-ሙስሊሙ ደስታና ሐዘኑን እየተጋራ በዓሉን ያከብራል። የዐረፋ እለት አንድም ሰው ተከፍቶ አያሳልፍም፤ በዐረፋ ሰሞን ማንም ሰው ተርቦና ተጠምቶ አያድርም። በዓሉ ትርጉም የሚሰጠው ሕዝበ-ሙስሊሙ ያለውን ተካፍሎ ሲያከብረው ነው። ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታን የሚሻገሩበት መፍትሄው መተሳሰብና መተጋገዝ እንደሆነ ከዐረፋ እንማራለን። ሀገርም ከፈተናዎችዋ በላይ እንድትሆን እኒህ እሴቶች ወሳኝ ናቸው።
ዐረፋ ማኅበረሰባዊ በዓል የሚባለው ለዚህ ነው። ሰዎች በግላቸው የሚያከብሩት አይደለም። ቤተሰቡ፣ ጎረቤቱ፣ ሠፈሩ፣ ከተማው የሚያከብረው በዓል ነው። ያላቸውና የሌላቸው፤ የሚችሉና የማይችሉ፤ ታላላቆችና ታናናሾች፤ ባለ ሥልጣናትና ተራ ዜጎች፣ በአንድነት የሚያከብሩት በዓል ነው። ሰው የሚኖረው በቤቱ ውስጥ አይደለም። በማኅበረሰቡ ውስጥ ነው።
ማኅበረሰባዊ ትሥሥርና ትብብር ለዜጎች እና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ ናቸው። ማኅበረሰባዊ ትሥሥር ስለሌሎች እንድናስብ፣ ስለሌሎች እንድንሠራ እና ስለ ሌሎች ዋጋ እንድንከፍል ያደርገናል። ራሳችንን በሌሎች ጫማ ላይ አቁመን እንድናይ ያስችለናል። የሁላችንም ሰላም፣ የሁላችንም ደኅንነት እና የሁላችንም ጥቅም ካልተከበረ በቀር የግላችንን ብቻ ልናስከብር እንደማንችል ያስገነዝበናል። ስለዚህም ማኅበራዊ ግዴታን እንደ ዜግነት ግዴታ ወስደን እንድንሠራ ያደርገናል።
ምርጫ ማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታዎችን ከምንወጣባቸው የዴሞክራሲ መገንቢያ መሳሪያዎች መካከል ዋነኛው ነው። ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም። የዴሞክራሲያችን መሰረት ጥንካሬው የሚለካው በተሳትፎአችን መጠን ነው።
የዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓታችን የሚጠነክርበት መሰረት ነው። የዴሞክራሲ ልምምዳችን አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት፤ የቀጣይ ዓመታት የሀገራችንን እጣ-ፈንታ የምንበይንበት፤ ከምንም በላይ ብዝሃ-ድምጽ የሚሰማበት የሕግ መወሰኛ ምክርቤት የምንመሰርትበት ወሳኝ አጋጣሚ ነው። በመሆኑም በዓሉን ስናከብር ዜግነታዊ ግዴታችንን ለመወጣት ብቻ ሳይሆን በካርዳችን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።
በድጋሚ መልካም የዐረፋ በዓል እንዲሆን እመኛለሁ!
ዒድ ሙባረክ!!
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ግንቦት 18፣ 2018 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ዓረብኛ: لَبَّيْكَ ٱللَّٰهُمَّ لَبَّيْكَ، لَبَّيْكَ لَا شَرِيكَ لَكَ لَبَّيْكَ، إِنَّ ٱلْحَمْدَ وَٱلنِّعْمَةَ لَكَ وَٱلْمُلْكَ، لَا شَرِيكَ لَكَ
ለበይክ አላሁመ ለበይክ፣ ለበይክ ላ ሸሪከ ለክ ለበይክ፣ እነልሐምዳ ወኒዕመታ ለከ ወልሙልክ ላ ሸሪከ ለክ
Translation: "Here I am, O Allah, here I am. Here I am, You have no partner, here I am. Surely all praise, favors, and sovereignty belong to You. You have no partner."
ተዛማጅ ትርጉም፣
አላህ ሆይ እነሆ ጥሪህን ሰምቼ አቤት እላለሁ። አቤቱ አንተ ከቶ አጋር የለህም፤ ምስጋና፣ ሞገስና ሉዓላዊነትም ሁሉ የአንተ ነው። አቤቱ አጋር የለህም።
Teshome Berhanu Kemal-
የቴሌግራም ቻናልችንን በመቀላቀል የአዲስ አድማስን መረጃ ይከታተሉ…
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮች ያሉት ታዋቂው ይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ፣ በሐረር አስደናቂ ጊዜን አሳልፏል።
ዲላን በሐረር ቆይታው፣ የከተማዋን ልዩ መገለጫ የሆነውን የጅቦችን በምሽት የመመገብ ስነ-ስርአት ላይ ተሳትፏል። ይህ ሁነት የሰው እና የዱር እንስሳ የሆነው የጅብ ትስስር እንዲሁም የህዝቡን እንግዳ ተቀባይነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በድጋሚ ያስመሰከረ አጋጣሚ ሆኗል።
ለ88 ቀናት ሙሉ በሙሉ ከዓለም አቀፍ አውታረ መረቦች ተገልላ የቆየችው ኢራን፣ ማክሰኞ ዕለት የኢንተርኔት አገልግሎትን በከፊል መመለስ መጀመሯን የኢንተርኔት ክትትል የሚያደርገው ኔትብሎክስ አስታውቋል። ይህ እገዳ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ ረጅሙ አገር አቀፍ የኢንተርኔት መዘጋት ሆኖ ተመዝግቧል። አገልግሎቱ ሊመለስ የቻለው ፕሬዝዳንት መስዑድ ፔዘሽኪያን ባቋቋሙት ልዩ የሳይበር ምህዳር ኮሚቴ አማካኝነት፣ የኢንተርኔት ግንኙነቱ ጥር 2026 ዓ.ም. ወደነበረበት ይዞታ እንዲመለስ ሰኞ ዕለት በድምፅ ብልጫ በመወሰኑ እንደሆነ ታውቋል።
ይሁን እንጂ የኢንተርኔት መከፈቱ ትዕዛዝ ወዲያውኑ ከባድ የህግና የፖለቲካ ፈተና ገጥሞታል። የሀገሪቱ የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ሳታር ሀሺሚ ውሳኔው በ9 ለ 2 ድምፅ መፅደቁንና የቋሚ መስመር ኢንተርኔት መለቀቅ መጀመሩን ገልጸዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ኃላፊ ፔይማን ጀበሊ እና የከፍተኛ የሳይበር ምህዳር ምክር ቤት ዋና ፀሐፊ መሐመድ አሚን አጋሚሪ የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት መመለሱን አጥብቀው ከተቃወሙት መካከል መሆናቸው ታውቋል።
ከእስላማዊ አብዮት ጥበቃ ጦር ጋር ግንኙነት ያለው ፋርስ የዜና ወኪል መጀመሪያ ላይ የፕሬዝዳንቱ አስተዳደር ይህንን እገዳ የመሻር ስልጣን የለውም በሚል ተከራክሮ ነበር፤ ምክንያቱም እገዳው የተጣለው በከፍተኛ ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤት በመሆኑ ነው። ይሁን እንጂ በኋላ ላይ ባወጣው ፅሁፍ፣ እገዳው መጀመሪያ ላይ የተጣለው በጦርነት ወቅት ሊሰነዘሩ የሚችሉ የሳይበር ጥቃቶችን ለመከላከልና መሠረተ ልማቶችን ለመጠበቅ እንደነበር ገልጾ፣ አሁን ላይ ግንኙነቱን መመለስ አስፈላጊ "የቴክኒክና የደህንነት" ውሳኔ መሆኑን በመግለጽ አቋሙን አርቋል።
የኢትዮጵያን የጤና ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሸጋግረውና በ5.4 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ዘመናዊው የላፍቶ ሆስፒታል ተመርቋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እንደገለጹት፣ ይህ ታላቅ ተቋም ሀገራችንን ቀዳሚ የህክምና ቱሪዝም መዳረሻ ለማድረግና ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚወጣውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ለመቀነስ ለተሰነቀው ራዕይ ትልቅ ማሳያ ነው። ሆስፒታሉ የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን ከመቀየር ባለፈ፣ ኢትዮጵያ በሁሉም ዘርፎች ራሷን ለመቻልና ለሀገራዊ ልማት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያሳይ ህያው ምስክር መሆኑን ጠቅሰዋል።
ይህ ግዙፍ ሆስፒታል እጅግ ዘመናዊ አቅሞችን በመጠቀም እንደ ካንሰር፣ ውስብስብ የልብ ህመምና ተያያዥ የህክምና ሁኔታዎችን በዓለም አቀፍ ደረጃ በመስጠት ዜጎች እዚሁ ሀገራቸው ውስጥ ልዩ የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል። በተሻሻለው የመከላከልና አክሞ የማዳን የጤና ፖሊሲ መሠረት የተገነባው ይህ ተቋም፣ መሰል የረቀቁ የዘርፉ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ግንባታን ለማስቀጠል እንደ አሻጋሪ ምዕራፍ የሚቆጠር ነው።
የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ባቀረቡት "ታላቅ ሰብአዊነት" በተሰኘው ሰነዳቸው ሰው ሠራሽ አስተውሎት በአስቸኳይ "ትጥቅ መፍታት" እንዳለበት አስጠነቀቁ። ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳቱ በታሪክ ውስጥ ቤተ ክርስቲያኗ በባሪያ ንግድ ላይ ለነበራት ሚና ታሪካዊና ሁሉን አቀፍ ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን፣ አሁን እየመጣ ካለው የኤአይ ስጋት ጋር በማመሳሰል ዓለም ወደ "አዲስ የዲጂታል ባርነት" እና የሰው ልጅ ብዝበዛ እያመራ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ኤአይን በጦርነት ውስጥ መጠቀምን በጥብቅ ያወገዙት ሊቀ ጳጳሱ፣ የሰው ልጅ በጦር መሣሪያዎች ላይ ያለውን ቁጥጥር መቀነስ ጦርነቶች በፍጥነት እንዲቀሰቀሱ እንደሚያደርግ አስረድተዋል። "አንድም አልጎሪዝም ጦርነትን የሞራል ተቀባይነት ያለው ሊያደርገው አይችልም" ያሉት ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳቱ፣ ቴክኖሎጂው ተጎጂዎችን ወደ ተራ ዳታነት በማውረድ ጦርነትን ይበልጥ ኢሰብአዊ እንደሚያደርገውና ሥልጣን ላይ ያሉ አካላት ይህንን አደጋ የማስወገድ ቀጥተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በቫቲካን ሲቀርብ የአሜሪካው የኤአይ ኩባንያ 'አንትሮፒክ' መስራች ክርስቶፈር ኦላህን ጨምሮ የዘርፉ ባለሙያዎች የተገኙ ሲሆን፣ ክርስቶፈር ኦላህም የርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳቱን መልዕክት በመደገፍ የኤአይ ጉዳይ በኮምፒውተር ሳይንቲስቶች ብቻ ሊወሰን የማይገባውና ከምርምር ማኅበረሰቡ የገዘፈ አሳሳቢ የዓለም ስጋት መሆኑን አረጋግጧል።
ዩናይትድ ስቴትስ በደቡባዊ ኢራን በሚገኙ የነዳጅ ማደያዎችና የፈንጂ ማከማቻዎች ላይ አዲስ ጥቃት መፈጸሟን አስታውቃለች። እንደ ቢቢሲ ዘገባ ከሆነ አሜሪካ ይህንን እርምጃ የወሰደችው ከኢራን ኃይሎች ሊሰነዘሩ የሚችሉ ጥቃቶችን አስቀድሞ ለመከላከል በማሰብ ነው።
ኢራን እስካሁን ለተሰነዘረባት ጥቃት ይፋዊ ምላሽ ያልሰጠች ሲሆን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኢል ባቃኢ ግን ቀደም ሲል በሰጡት መግለጫ ጦርነቱን ለማቆም በሚደረገው ንግግር ላይ የተወሰነ መሻሻል ቢታይም እስካሁን ድረስ የመጨረሻ ስምምነት ላይ መድረስ እንዳልተቻለ ገልጸው ነበር።
ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ኪቭ በሚገኙ የወታደራዊና ከመንግሥት ጋር ግንኙነት ያላቸው ተቋማት ላይ “ስልታዊ ጥቃቶችን” ለመሰንዘር መዘጋጀቷን ይፋ አድርጋለች። ይህንን ተከትሎም በኪቭ የሚገኙ የውጭ አገር ዜጎች፣ ዲፕሎማቶችና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በአስቸኳይ ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ይህ የሞስኮ ከባድ ማስጠንቀቂያ የወጣው፣ ሩሲያ በቅርቡ በኪቭ ላይ ካደረገቻቸው ትልልቅ የሚሳይልና የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃቶች ማግስት ነው። ሩሲያ ይህንን እርምጃ የወሰደችው ዩክሬን በሩሲያ ቁጥጥር ስር በምትገኘው ሉሃንስክ ግዛት ላይ ለሰነዘረችው ጥቃት የአጸፋ ምላሽ ለመስጠት መሆኑን ገልጻለች።
ሰሜን ኮሪያ በቅርቡ ባካሄደችው ምርጫ 99.93% የሚሆኑት መራጮች መንግሥት ያጸደቃቸውን ዕጩዎች መደገፋቸውን ይፋ አድርጋለች። ነገር ግን በሚገርም ሁኔታ መላው ዓለም በሰፊው እያወራና እየተወያየበት ያለው ስለ አብዛኛው ድምፅ ሳይሆን፣ ስለቀረችው 0.07% ድምፅ ብቻ ሆኗል። ይህ ምርጫ በዲሞክራሲያዊ አገራት እንደሚታየው ዓይነት ተወዳዳሪዎች ያሉበት ሳይሆን፣ ለሰሜን ኮሪያ ጠቅላይ ሕዝባዊ ምክር ቤት የተደረገ ምርጫ ነበር። መራጮች የቀረቡላቸው በገዢው ፓርቲ ብቻ የጸደቁ ዕጩዎችን በመሆኑ፣ እንደተለመደው ገዢው ፓርቲና አጋሮቹ ሁሉንም መቀመጫዎች ሙሉ በሙሉ አሸንፈዋል። የመንግሥት መገናኛ ብዙኃንም ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ሳይቀሩ “አዎ” ብለው መምረጣቸውን ገልጸዋል።
ሁሉም ማለት ይቻላል ተመረጡ… ግን ሙሉ በሙሉ አይደለም! ምክንያቱም ይፋዊው ውጤት እንደሚያሳየው 0.07% የሚሆኑት መራጮች የቀረቡትን ዕጩዎች በድፍረት ውድቅ አድርገዋል። በሌሎች አገራት ይህ ቁጥር እጅግ በጣም አነስተኛና ኢምንት ሊሆን ቢችልም፣ በሰሜን ኮሪያ ግን እጅግ አስደንጋጭና ያልተለመደ ክስተት ሆኗል። በዚህም ምክንያት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ያሉ ሰዎች ወዲያውኑ በዚህ ምስጢራዊ 0.07% ላይ ትኩረት በማድረግ ትልቅ መነጋገሪያ አድርገውታል። “እነዚህ ሰዎች እነማን ሊሆኑ ይችላሉ? ምን ዓይነት ድፍረትስ ቢኖራቸው ነው? ከዚያ በኋላስ ድምፃቸው ይሰማ ይሆን?” እያሉ በሰፊው እየቀለዱና እየተወያዩበት ይገኛሉ። በአንድ አገር 99.93% የድጋፍ ድምፅ ተመዝግቦ፣ የኢንተርኔቱ ዓለም ግን ስለ 0.07ቱ% ብቻ አጥብቆ መገረሙን ቀጥሏል።
Page 5 of 807