Administrator

Administrator

መሠረት የበጎ አድራጐት ድርጅት 480 ችግረኛ ቤተሰቦች የገና በዓልን በደስታ እንዲያከብሩ  የዶሮና የእንቁላል ስጦታ ማበርከቱን ገለፀ፡፡
ለእያንዳንዱ ቤተሰብ አንድ ዶሮና ስድስት እንቁላል፣ በአጠቃላይ 480 ዶሮዎችንና 2880 እንቁላሎች የተበረከተ ሲሆን 64ሺ ብር እንደፈጀም ታውቋል፡፡
ለችግረኛ ቤተሰቦች የተበረከተው ስጦታ በአገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን  ከ5 ብር ጀምሮ ባደረጉት መዋጮ እንደሆነ መሰረት በጎ አድራጎት አስታውቋል፡፡
ይሄ ድጋፍ የተደረገበትን ዓላማ ያስረዱት የበጎ አድራጎቱ መስራችና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት አዛገ፤ “የባህል እሴቶቻችን ተጠብቀው ሁሉም ቤተሰብ ከልጆቹና ከጐረቤቱ ጋር ባህሉን በደስታ እንዲያከብርና ማንም ሰው ደሀ በመሆኑ ምክንያት በአሉን በችግር እንዳያሳልፍ ለማድረግ ነው” ብለዋል፡፡ መስራቿ፤ ፕሮግራሙ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ለረዷቸው የተለያዩ ግለሰቦች፣ ድርጅቶችና ለበጐ ፈቃድ አገልጋዮች፣ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
መሠረት የበጐ አድራጐት ድርጅት፤ በድህነት ለሚኖሩ ሴቶችና ህፃናት የተለያዩ ድጋፎችና ዕድሎች በመስጠት በማብቃት የሚተጋ የበጐ አድራጐት ድርጅት ነው፡፡  

ዳሽን ቢራ ፋብሪካ በስነ ፅሁፍና በስዕል ጥበብ ላይ የተሰማሩ ደራሲያንን፣ ሰአሊያንንና  በዘርፉ እየሰለጠኑ የሚገኙ ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ተማሪዎች የሚያሳትፍ በስነ ፅሁፍ፣ በግጥም እንዲሁም በስዕል ዘርፎች በማወዳደር በመሸለም በተሻለ ስራ እውቅና ሊያገኙ የሚችሉበትን መድረክ ማመቻቸቱን ገለፀ፡፡
በዚሁ በዳሽን አርት አዋርድ ላይ የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎችን ለመዳኘት ከኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር፣ ከኢትዮጵያ ሰአሊያን ማህበር፣ ከዜማ ብዕር ኢትዮጵያ ሴቶች የስነፅሁፍ ማህበርና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስነ ጥበባት ተመርጠው መሄዳቸውም ተገልጿል፡፡
ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አ/ማ ስፖርትና ኪነጥበብን በመሳሰሉ ሀገራዊ፣ ማህበራዊ እና ህዝባዊ የልማት እንቅስቃሴዎች ላይ ድጋፍ የሚያደርግ ድርጅት መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡

   በመቶዎች የሚቆጠሩ ፖሊሶች ለከንቲባው ጀርባቸውን ሰጥተዋል

   ባለፈው ወር መጨረሻ፡፡ አንድ ተሲያት ላይ ከብሮክሊን ሰማይ ስር ተደጋጋሚ የተኩስ ድምጽ ተሰማ፡፡ የተኩሱን ድምጽ የሰሙት የከተማዋ ፖሊሶች በአፋጣኝ ወደ ስፍራው ሲያመሩ፣ አስደንጋጭ ትእይንት ገጠማቸው፡፡ ራፋኤል ራሞስ እና ዌንጂን ሊዩ የተባሉ ሁለት የፖሊስ ባልደረቦች በጥይት ተመትተው ደማቸውን እያፈሰሱ ጎዳና ዳር ወድቀዋል፡፡ ተኳሹ ኢስማኤል ብሪንስሊ የተባለ ግለሰብ ነበር፡፡ ሰበቡ ደግሞ ንዴት፡፡ብሪንስሊ ከጥቂት ጊዜያት በፊት በፈርጉሰን እና በኒውዮርክ ሲቲ በነጭ ፖሊሶች በተገደሉት ሁለት ጥቁሮች ጉዳይ በንዴት ሲብከነከን ሰንብቷል፡፡ ንዴቱንና ቂሙን መርሳት ያልሆነለት ይሄው ግለሰብ ታዲያ፣ በገና ዋዜማ ጠመንጃውን አንስቶ ወደ ብሮክሊን ለበቀል ተንደረደረ፡፡ በሁለት ፖሊሶች ላይ አነጣጠረ፡፡ ጥይት ቆጠረ፡፡ በስተመጨረሻም በገዛ ጠበንጃው ራሱን አጠፋ፡፡
በግለሰቡ ድርጊትና መንግስት ተገቢውን ፍትህ ለመስጠት አልቻለም በሚል ክፉኛ የተበሳጩት በርካታ የኒውዮርክ ሲቲ ፖሊሶችም ታዲያ፣ ነግ በእኔ ብለው ተቃውሟቸውን በግልጽ አሰምተዋል፡፡ ላለፉት ሁለት ሳምንታት መደበኛ ስራቸውን በአግባቡ ማከናወን መተዋቸውንም ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡ፖሊሶቹ ስራቸውን በአግባቡ ማከናወን ማቆማቸውን ተከትሎ በከተማዋ ያለው የወንጀል ቁጥር መላላቱ ተነግሯል፡፡ ወንጀለኞችን በአግባቡ በቁጥጥር ስር በማዋል ከህገወጦች በቅጣት መልክ ሊሰበሰብ የሚገባው ገንዘብ እየተሰበሰበ አይደለም፡፡ ዘ ታይምስ እንዳለው፤ የከተማዋ ፖሊሶች ወንጀለኞችን በአግባቡ በቁጥጥር ውስጥ ለማዋል ተግተው ባለመስራታቸው የወንጀል ክሶች በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሰዋል፡፡ በቁጥጥር ውስጥ የሚውሉ ወንጀለኞች ቁጥር 66 በመቶ ያህል ቀንሷል፡፡ ባለፈው ሳምንት በከተማዋ ፖሊስ የተያዙ የወንጀል ክሶች 347 ብቻ መሆኑንና፣ ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ይህ ቁጥር ከ4 ሺህ በላይ እንደነበር ዘ ታይምስ ዘግቧል፡፡ ቀረጥና ፓርኪንግን ከመሳሰሉ ነገሮች የሚገኘው የመንግስት ገቢም፣ ስራ በፈቱ ፖሊሶች ሳቢያ በአግባቡ ሊሰበሰብ ባለመቻሉ ከ90 በመቶ በላይ ቀንሷል፡፡ ይህም በከተማዋ ኢኮኖሚ ላይ ትልቅ ጫና እየፈጠረ እንደሆነ እየተነገረ ነው፡፡የፖሊስ አባላት ስራ መፍታታቸው ምንም እንኳን በከተማዋ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በማበራከት ረገድ ይህ ነው የሚባል ተጽዕኖ ባይፈጥርም፣ በአንድ አካባቢ የዝርፊያ ድርጊቶች ከወትሮው በተለየ ከፍ ማለታቸውን የዋሽንግተን ፖስት ዘገባ ያሳያል፡፡ ባለፈው ሳምንት በተከበረው የፈረንጆች የገና በዓል ዋዜማ ላይ በተከናወነው የሟቹ የስራ ባልደረባቸውን ዌንጃን ሊዩን የቀብር ስነስርዓት ላይ የተገኙት በመቶዎች የሚቆጠሩ ፖሊሶች የከተማዋ ከንቲባ ቢል ዲ ባላሲዮ ወደ መድረክ ወጥተው የሃዘን መግለጫቸውን ሲያስተላልፉ ጀርባቸውን ሰጥተዋቸው ነበር - ተገቢውን ምላሽ አልሰጡንም በሚል፡፡
የከተማዋ የፖሊስ ኮሚሽነር ቢል ብራተን ባልደረቦቻቸው በቀብር ስነስርዓቱ ላይ ተቃውሞ እንዳያሰሙ አበክረው ቢያስጠነቅቁም፣ ፖሊሶቹ ግን ማስጠንቀቂያውን ችላ ብለው ተቃውሟቸውን በግልጽ አሳይተዋል፡፡የፖሊስ አባላቱን አቋም በተመለከተ የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰጡ ሲሆን፣ ለመብታቸው መከበር በጽናት መቆማቸውን ያደነቁ መኖራቸውን ያህል፣ በወጉ ከመንግስት ጋር ተወያይተው መፍትሄ መሻት ሲገባቸው ስራ መፍታታቸውን ክፉኛ የተቹም ብዙዎች ናቸው፡፡
 ይህ ድርጊት ያናደዳቸውና የፖሊሶች እምቢ ባይነት ያበሳጫቸው የከተማዋ ከንቲባም ታዲያ የፖሊስ አባላቱ በዚሁ ድርጊታቸው የሚገፉና የዕለት ተዕለት ስራቸውን በአግባቡ የማያከናውኑ ከሆነ፣ ስራቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንደለቀቁ ተቆጥሮ በሌሎች እንደሚተኩ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል፡፡


የኢቦላ በሽታ ተጠቂዎችን የመፈወስ አቅም ይኖረዋል ተብሎ የሚጠበቀውን ብሪንሲዶፎቪር የተባለ መድሃኒት በታማሚዎች ላይ የመሞከር ስራ ላይቤሪያ በሚገኘው የድንበር የለሽ የሃኪሞች ቡድን የህክምና ማዕከል ውስጥ መጀመሩ ተዘገበ፡፡በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች የተዘጋጀው መድሃኒቱ፣ በቫይረሱ በተያዙ ፈቃደኛ ግለሰቦች ላይ እየተሞከረ እንደሚገኝ የዘገበው ቢቢሲ፣ ውጤቱ በመጪዎቹ ጥቂት ወራት ውስጥ ይታወቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ገልጿል፡፡
ምንም እንኳን ከወራት በፊት ሌሎች መድሃኒቶች ተመርተው በታማሚዎች ላይ ቢሞከሩም፣ አንዳቸውም ፈዋሽነት ሳይኖራቸው እንደቀሩ ዘገባው አስታውሷል፡፡የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ይህንን መድሃኒት በታማሚዎች ላይ ለመሞከር የወሰኑት፣ መድሃኒቱ በቤተ ሙከራዎች ውስጥ በሚገኙ በኢቦላ ቫይረስ የተጠቁ ህዋሳት ላይ ተሞክሮ ውጤታማነቱ በመረጋገጡ ነው ተብሏል፡፡
መድሃኒቱ በኢቦላ በተጠቁ 100 የአገሪቱ ዜጎች ላይ እየተሞከረ እንደሚገኝና ጎን ለጎንም ሌሎች ምርምሮች መካሄዳቸው እንደሚቀጥል ዘገባው አስታውቋል፡፡


እስካሁን ያለው የምርጫ ሂደት ምን ይመስላል?
በኛ በኩል የምርጫው ሂደት በተቀመጠለት አቅጣጫ መሠረት እየሄደ ነው፡፡ ቀድመን ስትራቴጂና እቅድ አዘጋጅተናል፡፡ ካለፉት ምርጫዎች በተሻለ ለመንቀሳቀስ ዝግጅት አድርገን ነው እየሰራን ያለነው፡፡ ሃገሪቱን እንደሚመራ ገዢ ፓርቲና ተወዳዳሪ ፓርቲ ሁለት ሚናዎች ነው ያሉት፡፡ በመንግስት በኩል (ሀገሪቱን የሚመራ ፓርቲ እንደመሆኑ) ምርጫውን ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ሠላማዊ በማድረግ ረገድ እየተሠራ ነው፡፡ እንደ ተወዳዳሪ ፓርቲ ደግሞ አሸናፊ ሆነን የምንወጣበትን አጠቃላይ ዝግጅት እያደረግን ነው፡፡ እንደ ድርጅት፣ በስነምግባር ደንቡና በአጠቃላይ በምርጫ ህጐቹ ሂደት ላይ የአሠልጣኞች ስልጠና በከፍተኛ የአመራር ደረጃ ሰሞኑን ተሰጥቷል፡፡
በየደረጃው ለሌሎችም ስልጠናው ይሰጣል፡፡ ካለፉት ምርጫ ልምዶች ተነስተን 5ኛው ሃገራዊ ምርጫ ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ፣ ወሳኙ ህዝብ ስለሆነ የህዝቡን ወሳኝነት ለማረጋገጥ እየተንቀሳቀስን ነው፡፡
ከህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ ጋር ተያይዞ ተቃዋሚዎች፤ “ኢህአዴግ የ1ለ5 አደረጃጀቱን ተጠቅሞ አባላቱን አስመርጧል” ሲሉ ይወቅሣሉ፤ በዚህ ላይ የእናንተ ምላሽ ምንድን ነው?
የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫን በተመለከተ አንዳንድ ፓርቲዎች መሠል አስተያየቶችን ሲያቀርቡ ሰምተናል፡፡ አንደኛው ወቀሳቸው፣ የታዛቢዎች ምርጫ የተካሄደው ለኛ ሣይነገረን ኢህአዴግ ብቻ ተነግሮት ነው የሚል ነው፤ ይሄ በጣም መሠረታዊ ስህተት ነው፤ ምክንያቱም ኢህአዴግም እነዚህ ፓርቲዎችም ባሉበት የምርጫ ጊዜ ሠሌዳው ቀርቦ ውይይት አድርገንበታል፡፡ ምርጫ ቦርድ ያወጣው የጊዜ ሠሌዳ ኢህአዴግን ጨምሮ ለእያንዳንዱ ፓርቲ አቅርቧል፡፡ ስለዚህ ታህሣሥ 12  የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ እንደነበር ይታወቃል፡፡ የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች በሚዲያም ቀርበው ታህሣሥ 12 የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡ ስለዚህ በሚስጥር የተደረገ ነው፤ የሚለው የተሣሣተ ነው፤ በይፋ በደብዳቤም በሚዲያም ተገልጿል፡፡
በእለቱም ኢህአዴግ አባሎቹ እንዳይመረጡ ጥንቃቄ አድርጓል፡፡ አንዳንድ ቦታ እንኳ አባሎቻችን ሲጠቆሙ “እኔ አባል ነኝ፤ አልችልም” ብለው ከምርጫው የወጡበት ሁኔታ አለ፡፡ ስለዚህ ይህ የተቃዋሚዎች ውንጀላ የተለመደ ሂደቱን ከጅምሩ ጥላሸት የመቀባት አካል ነው፡፡ የተመረጡት የህዝብ ታዛቢዎች ገለልተኛ አይደሉም ለማስባል የሚረዳ ተራ የስም ማጥፋት ሂደት ነው፡፡
1ለ5 የሚባለው ለመንግስት የልማት ስራ የተደራጀ ነው እንጂ የፓርቲው አደረጃጀት አይደለም፡፡ የተቃዋሚም የኢህአዴግም አባል የሆነ ሊኖር ይችላል፤ ስለዚህ የ1ለ5 አደረጃጀትን ሂዱና የህዝብ ታዛቢ ምረጡ ቢል ችግር የለውም ማለት ነው፡፡ ኢህአዴግን ምረጡ ወይም ደጋፊ የሆነን ሰው ምረጡ የሚባል ነገር የለም፡፡ ስለዚህ በ1ለ5 አደረጃጀት ላይ ብዥታ ሊኖር አይገባም፤ አደረጃጀቱ የልማት አደረጃጀት ነው፡፡ ይህን አደረጃጀት ሂዳችሁ ታዛቢ ምረጡ ወይም በምርጫው ተሳተፉ ቢል ነውር አይደለም፡፡ ከዚህ አንፃር ህዝቡ ገለልተኛ ናቸው ያላቸውን ታዛቢዎቹን መርጧል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህ ውንጀላዎች ተቀባይነት የሌላቸው፣ ሂደቱን ጥላሸት ለመቀባት ሆነ ተብሎ የሚደረጉ ናቸው፡፡ የኢህአዴግ አባል ተመርጧል የሚሉ ከሆነና የተመረጠበትን ቦታ ከጠቆሙ እኛም ለማጣራት  ዝግጁ ነን፡፡ ድንገት ሾልኮ የገባ ካለም እንዲወጣ እናደርጋለን፡፡ እስካሁን ግን እንዲህ ያለ ነገር ስለመኖሩ ምንም መረጃ የለንም፡፡ ህዝቡ  ምርጫውን ማካሄዱ መብቱን ማረጋገጫ መንገድ ነው፡፡
የምርጫ ስነ ምግባር ደንቡን ካልፈረሙ ፓርቲዎች ጋር ኢህአዴግ ለመወያየት የማይችልበት መሠረታዊ ምክንያት ምንድን ነው? ደንቡን መፈረምን እንደ ግዴታ ማስቀመጥ የውይይት በርን መዝጋት አይሆንም?  
ደንቡ ሲዘጋጅ ብዙ ሂደት አልፏል፡፡ በወቅቱ የነበሩት ፓርቲዎች በእርጋታ እየተወያዩ ያለፉበት ሂደት ነበር፤ በዚህ ሂደት መድረክ ሶስት ጊዜ ረግጦ ወጥቷል፡፡ መጀመሪያ ሂደቱ ሲጀመር ወደ ውይይቱ ተጋብዞ መጣ፤ ያኔ ከኢህአዴግ ጋር እንጂ ከሌሎች ተቃዋሚዎች ጋር መወያየት የለብኝም አለ፡፡ ኢህአዴግ ደግሞ ብዙ ፓርቲዎች ባሉበት ሃገር፣ የተናጥል ውይይት ከእያንዳንዱ ጋር ማድረግ አይችልም፡፡ መድረክ፤ ሌሎች ፓርቲዎች ተቃዋሚዎች አይደሉም የሚል አመለካከት ስለለው ወጣ፡፡ በሌላ ጊዜም ተጋበዘ፤ ሂደቱን ትቶ ወጣ፡፡ ለ3ኛ ጊዜ 65 ፓርቲዎች ሲወያዩ ገብቶ ሂደቱን ለመበተን ነው ጥረት ያደረገው፤ ግን መጨረሻ ላይ 65 ፓርቲዎቹ ተስማምተው ህግ ሆኖ ወጣ፡፡ ህግ ሆኖ ሲወጣ በህጉ ውስጥ የተቀመጠ ቅድመ ሁኔታ አለ፡፡
የጋራ ምክር ቤቱ አባል ሆኖ ለመቀጠል የፈለገ ፓርቲ ህጉን መፈረም አለበት፡፡ ይሄ ማለት የፖለቲካ ቁርጠኝነት ማረጋገጫ ነው፡፡ ስለዚህ የስነ ምግባር ደንቡ ህግ ሆኖ እንዲወጣ ፓርቲዎቹ በራሳቸው ሊገፉት ይገባል ማለት ነው፡፡ የፊርማ ቅድመ ሁኔታን ኢህአዴግ አላስቀመጠም፤ ራሱ ህጉ ያስቀመጠው ነው፡፡ እያንዳንዱ ፓርቲ በስነምግባር መመራቱን, የፖለቲካ ቁርጠኝነቱን ቀድሞ ማረጋገጥ አለበት ነው የሚለው ህጉ፡፡ ይህን ያረጋገጡ የጋራ ምክር ቤት ውስጥ እየሠሩ ነው፡፡ ከኢህአዴግ ጋር እነዚህ ፓርቲዎች በፕሮግራም የተለዩ ናቸው፡፡ በምርጫ ሂደቱ ላይ ግን በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው የበሠለ ውይይት እያደረጉ ነው፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ስነ ምግባሩ ያስረናል ብለው ስለሚያስቡና አመፅና ብጥብጥ ለማስነሳት ያግደናል ብለው ስለሚያስቡ ቁርጠኝነት ስላነሣቸው ነው እንጂ ኢህአዴግ በተናጥል አልደራደርም ስላለ አይደለም፡፡ ከዚህ አንፃር ተስማምተን ህግ ሆኖ በወጣ ጉዳይ ላይ lምንድን ነው ተመልሰን ወደ ድርድር የምንገባው? የሚለው ጥያቄ መመለስ አለበት፤ ስለዚህ ተመልሰን ወደ ድርድር የምንገባበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ አሁንም ምርጫ ቦርድ በሚጠራቸው ስብሰባዎች ላይ አብረን እንሣተፋለን፤ የጋራ ምክር ቤት ውስጥ ለመግባት ግን ድርድር አያስፈልገውም፤ በስነምግባር ለመገዛት መስማማት ብቻ ነው፡፡ ኢህአዴግ ያለፈባቸውን ሂደቶች ስናይ ሁልጊዜም በድርድር የሚያምን መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
ለምንድን ነው የአለማቀፍ መስፈርቶችን ያሟላ ስነምግባር ተገዥ ሆናችሁ፣ ለፍትሃዊና ሠላማዊ ምርጫ ውድድር ዝግጁ ያልሆናችሁት የሚለውን ጥያቄ ተቃዋሚዎች መመለስ አለባቸው፡፡ በስነምግባር እንመራ የሚል ውይይት ማካሄድ እንዴት ይቻላል፡፡
ደንቡን ያልፈረሙ መድረክን የመሣሠሉ ድርጅቶች ከኢህአዴግ ጋር መወያየት ቢፈልጉ እንዴት ነው የሚስተናገዱት?
በተቀመጡ ማዕቀፎች መሠረት ይስተናገዳሉ፡፡ ገለልተኛ የሆነው የምርጫ ቦርድ አለ፡፡ ያልተሟሉ ነገሮች ካሉ ለምርጫ ቦርድ እያቀረቡ ሊፈቱ ይችላሉ፡፡ ኢህአዴግ ደግሞ በተቋማዊ አሠራር የሚያምን ድርጅት ነው፡፡ የስነምግባር ደንቡ በሌለበትና የጋራ ምክር ቤቶች ባልተቋቋሙበት ሁኔታ ጥያቄው ቢቀርብ ትክክል ነው፡፡ ከእያንዳንዱ ፓርቲ ጋር ኢህአዴግ እየተወያየ ሊሄድ ይችላል፡፡ አሁን ግን የጋራ ማዕቀፍ  በተዘረጋበት ኢህአዴግ እንዴት ብሎ ነው ከ70 ፓርቲዎች ጋር በተናጠል መወያየት የሚችለው? አሁን ተቋዋሚ አሠራር ተዘርግቷል፡፡
ለመወያየት የፈለገ የጋራ ምክር ቤቱ ውስጥ መግባት አለበት፡፡ ችግሮች ሲፈጠሩ ምክር ቤቱ አጣሪ ኮሚቴ አቋቁሞ ያጣራል፤ መፍትሔ እንዲያገኙም ያደርጋል፡፡ ከዚህ ውጪ በተናጠል መወያየት አይቻልም፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች በራሳቸው የሚፈጠረውን ችግር እንኳ ሣይቀር ኢህአዴግ ፈጠረው ነው የሚሉት፡፡
በአመራር እንኳ የተፈጠረባቸውን ችግር በኢህአዴግ የተፈጠረ ጥፋት አድርገው ይወስዱታል፡፡ ስለዚህ ይሄን መፍረድ ያለበት ህዝቡ ነው፡፡ ህዝቡ ሁሉንም ነገር ያያል፡፡ ማን ነው ጥፋተኛ? ኢህአዴግ ነው ለዲሞክራሲያዊ ስርአትና ፍትሃዊ ምርጫ ዝግጅ ያልሆነው ወይስ ሌላው? የሚለውን መፍረድ ያለበት ህዝቡ ነው፡
ኢህአዴግ የገዢነቱን ኃይል ተጠቅሞ በተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚደረጉ ሰላማዊ ሰልፎችን ለማፈን ይጥራል የሚሉ ቅሬታዎች ይቀርባሉ፡፡ ኢህአዴግ እንደፓርቲ በሰላማዊ ሰልፍ ላይ ያለው አቋም ምንድን ነው?
ፓርቲያችን ሰላማዊ ሰልፍ ለዜጎች የተሰጠ ህገ መንግስታዊ መብት ነው ብሎ ያምናል፡፡ ይሄ መብት ተግባራዊ የሚሆንባቸው አሰራሮች እንደሚዘረጉ ህገ መንግስቱም አስቀምጧል፡፡ በህገ መንግስቱ ዜጎች በጋራ ሆነው ቅሬታ የማቅረብ፣ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ የማድረግ መብት አላቸው ይላል፡፡ ይሄን መብት ተግባራዊ ለማድረግ አሰራሮች ሊዘረጉ እንደሚችሉ ተቀምጧል፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ አድራጊዎች የህዝቡን ሰላም፣ ክብርና የመሳሰሉ መብቶችን መጣስ እንደሌለባቸው ህገ መንግስቱ አስቀምጧል፡፡
አንድ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማሳወቅ እንደሚጠበቅበትም ተቀምጧል፡፡ የእውቅናውን ጥያቄ የሚያየው አካል የተጠየቀበትን ቦታና ጊዜ ይመለከትና በእውቅና ጥያቄው ላይ ምላሽ ይሰጥበታል፡፡ ቦታ ቀይር ወይም ቀን ቀይር የሚል ምላሽ ይሰጥበታል ማለት ነው፡፡ ዘጠኙ ፓርቲዎች የጠየቁት ቦታ መስቀል አደባባይ ነው፡፡ መስቀል አደባባይ ደግሞ ትልቅ የልማት እንቅስቃሴ እየተደረገበት ያለ ቦታ ነው፡፡ ለ24 ሰዓት ቆመ ማለት ብዙ ነገር ያስተጓጉላል፡፡
 ስለዚህ ቦታው ተገቢ አልነበረም ማለት ነው፡፡ በዚህ የተነሳ የተጠየቀው አካል አልተቀበለውም፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች ዕቅዳቸው ልማትን ማደናቀፍ፣ ህዝብን ወደ አመፅ መንዳት እንደሆነ ከዚህ መረዳት ይቻላል፡፡ ኢህአዴግ እንደ ፓርቲ ግን ሰላማዊ ሰልፍ የዜጎች መብት ነው የሚል አቋም አለው፡፡
ኢህአዴግ ለምርጫው ያስቀመጠው ግብ ምንድን ነው? አንዳንድ ወገኖች ሙሉ ለሙሉ አሸናፊ እንዳይሆን ተጠንቅቆ እስከ 15 በመቶ ወንበሮችን ለተቃዋሚዎች ሊለቅ ይችላል የሚል አስተያየት ይሰነዝራሉ?
ኢህአዴግ መንግስት ለመመስረት የሚያስችለውን ወንበር ማግኘት ነው ግቡ፡፡ ይሄ ሲባል ድምፁ እንደ እጩ ቁጥራችንም ይወሰናል በአገሪቱ ባሉ የምርጫ ክልሎች ሁሉ እንወዳደራለን፡፡ በእያንዳንዱ የምርጫ ክልል ለማሸነፍ እንሰራለን ማለት ነው፡፡ ኢህአዴግ ዲሞክራሲን የሚያየው በእውነተኛ ገፅታው ነው፡፡ ዲሞክራሲ በአርቴፊሻል ገፅታ መታየት የለበትም፡፡ ዲሞክራሲ የህዝብ ወሳኝነትን ማረጋገጫ መሳሪያ ነው፡፡ በእያንዳንዱ የምርጫ ክልል ተወዳድረን ህዝቡ የሚመርጠን ከሆነ እሰየው ብለን እንወስዳለን፤ ባይመርጠንም እንቀበላለን፡፡ ከዚህ ውጭ አርቴፊሻል በሆነ መንገድ፣ የህዝብን ውሳኔ ባላከበረ መንገድ የተወሰነ ወንበር እንለቃለን የሚል ሃሳብ የለም፡፡ ወሳኙ ህዝብ ነው፡፡ ምርጫ በውጤት አይመዘንም፤ ዋናው ሂደቱ ነው፡፡ ሂደቱ ማማር አለበት፡፡
በየጊዜው በሚደረጉ ምርጫዎች ላይ የአለማቀፍ ታዛቢዎች ቁጥር እየቀነሰ ሄዶ ዘንድሮ የአውሮፓ ህብረትም ቀርቷል፡፡ አለማቀፍ ታዛቢዎች ከምርጫው ለምን ተገለሉ?
 የኛ ምርጫ ማንም ሊታዘበው የሚችል ምርጫ ነው፡፡ በድብቅ የሚካሄድ ምርጫ ሳይሆን ማንም ሊያየው የሚችል ምርጫ ነው፤ ነገር ግን ምርጫን የአውሮፓ ህብረት ካልታዘበው ችግር ይኖርበታል ብሎ ማሰብ በራሱ የምርጫው ወሳኝ ማን ነው የሚለውን ጥያቄ ውስጥ ያስገባዋል፡፡ ህብረቱ ምርጫውን ለመታዘብ የበጀት እጥረት አለብኝ የመሳሰሉ ምክንያቶችን ነው ያቀረበው፡፡ ስለዚህ ምርጫውን የአፍሪካ ህብረት ይታዘበዋል፣ ከሃገር ውስጥም የተለያዩ የሲቪል ማህበራት ይታዘቡታል፡፡ ዋናው ወሳኙ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው፡፡ ይሄ ህዝብ ነው ውሳኔ የሚሰጠውም የሚታዘበውም፡፡
አለማቀፍ ታዛቢዎች የምርጫውን ገለልተኛነት ከማረጋገጥ አንጻር ምንም ዓይነት ሚና አይኖራቸውም እያሉን ነው?
 ሊታዘቡ ይችላሉ ግን ዋናው ሚና የህዝብ ነው፡፡ እያንዳንዱ ሂደት ከህዝብ ጋር የተገናኘ ነው አለማቀፍ ታዛቢ ተጨማሪ ነው፤ ወሳኝነት የለውም፡፡
ኢህአዴግ በዚህ ምርጫ ሊወዳደረኝ የሚችል ፓርቲ አለ ብሎ ያምናል?
ይሄን ህዝቡ ነው የሚመዝነው፡፡ ቀድመን ባንመዝነው እመርጣለሁ፡፡ ፓርቲዎች ምን እንደሚመስሉ የራሳችን ግምት አለን፡፡ የህዝብን ጥቅም ሊያስጠብቅ የሚችል ሌላ ይህች አገር የጀመረችውን ልማት፣ ዲሞክራሲ በቁርጠኝነት ይዞ ሊሄድ የሚችል ፓርቲ አለ ብለን አናምንም፡፡ በተለያዩ መንገዶች መመዘን እንችላለን፡፡ ከራሳቸው ባህሪ ተነስተን ማለት ነው፡፡
ፓርቲ ማለት የህዝብን ህይወትና ኑሮ ለመቀየር የሚሰራ ፓርቲ ነው፡፡ የትኛው ፓርቲ ነው ህዝቡ ለልማት ሲንቀሳቀስ ከጎኑ ተሰልፎ የሚሳተፈው? የትኛው ፓርቲ ነው ህዝቡ ተግዳሮቶች ሲያጋጥሙት አብሮ እየተንቀሳቀሰ ያለው? የትኛው ፓርቲ ነው ግልፅ የሆነ ሃገር የሚቀይር አማራጭ ፕሮግራም ያለው? የሚለው ስንጠይቅ፣ ሃገርን በዚህ መንገድ ወደፊት የሚያሻግር ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ የለም የሚል ድምዳሜ ላይ ያደርሰናል፡፡ ይሄን ግን ህዝቡ ነው ገምግሞ ሚዛን ላይ ማስቀመጥ ያለበት፡፡ አሁን ቅስቀሳ ባልተጀመረበት ሁኔታ በዚህ ጉዳይ ብዙ አስተያየት መስጠት አይቻልም፤ ግን ህዝብ ይታዘባል፡፡ እናሸንፋለን አናሸንፍም የሚለውም ቅስቀሳ ስለሚሆን የምረጡን ቅስቀሳ ሲካሄድ ብናየው የተሻለ ነው የሚሆነው፡፡
ኢህአዴግ በምርጫ ቦርድ ወይም በምርጫ ሂደቱ ላይ ቅሬታ አለው?
ምርጫ ቦርድ ጋ ቅሬታ የለንም፡፡ ቦርዱ በገለልተኝነት እየሰራ ያለ ተቋም ነው፡፡ ስብሰባ ሲጠራን አስተያየት እንሰጣለን፤ እስካሁን ግን ምንም ቅሬታ የለንም፡፡ ሌሎች ፓርቲዎች የሚያቀርቡትም አብዛኛው ቅሬታ ትክክል አይደለም ብለን እናምናለን፡፡
ፓርቲዎቹ ራሳቸው መጨረስ ያለባቸውን የቤት ስራ ሳይሰሩ፣ በቦርዱ ላይ የሚያቀርቡትን አብዛኞቹን ቅሬታዎች ስንገመግም፣ ቦርዱ ገለልተኛ አይደለም የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ የሚያደርጉት ጥረት መሆኑን እንገነዘባለን ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ለኛ የሚያደላልን ነገር የለም፡፡



•    ኢህአዴግ ዲሞክራሲን የሚያየው በእውነተኛ ገፅታው ነው
•    ምርጫ በውጤት አይመዘንም፤ ዋናው ሂደቱ ነው
የግንቦቱን ምርጫ እየተቃረበ ነው፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫ ሂደቱ ላይ የተለያዩ ቅሬዎችንና ተቃውሞዎችን እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡ ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግስ ምን ይላል? የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ በኢህአዴግ ምክር ቤት ፅ/ቤት የህዝብና ውጭ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደስታ ተስፋውን በምርጫው ዝግጅትና ሂደት ዙሪያ አነጋግሯቸዋል፡፡
እስካሁን ያለው የምርጫ ሂደት ምን ይመስላል?
በኛ በኩል የምርጫው ሂደት በተቀመጠለት አቅጣጫ መሠረት እየሄደ ነው፡፡ ቀድመን ስትራቴጂና እቅድ አዘጋጅተናል፡፡ ካለፉት ምርጫዎች በተሻለ ለመንቀሳቀስ ዝግጅት አድርገን ነው እየሰራን ያለነው፡፡ ሃገሪቱን እንደሚመራ ገዢ ፓርቲና ተወዳዳሪ ፓርቲ ሁለት ሚናዎች ነው ያሉት፡፡ በመንግስት በኩል (ሀገሪቱን የሚመራ ፓርቲ እንደመሆኑ) ምርጫውን ፍትሃዊ፣ ዲሞክራሲያዊና ሠላማዊ በማድረግ ረገድ እየተሠራ ነው፡፡ እንደ ተወዳዳሪ ፓርቲ ደግሞ አሸናፊ ሆነን የምንወጣበትን አጠቃላይ ዝግጅት እያደረግን ነው፡፡ እንደ ድርጅት፣ በስነምግባር ደንቡና በአጠቃላይ በምርጫ ህጐቹ ሂደት ላይ የአሠልጣኞች ስልጠና በከፍተኛ የአመራር ደረጃ ሰሞኑን ተሰጥቷል፡፡
በየደረጃው ለሌሎችም ስልጠናው ይሰጣል፡፡ ካለፉት ምርጫ ልምዶች ተነስተን 5ኛው ሃገራዊ ምርጫ ሠላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ፣ ወሳኙ ህዝብ ስለሆነ የህዝቡን ወሳኝነት ለማረጋገጥ እየተንቀሳቀስን ነው፡፡
ከህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ ጋር ተያይዞ ተቃዋሚዎች፤ “ኢህአዴግ የ1ለ5 አደረጃጀቱን ተጠቅሞ አባላቱን አስመርጧል” ሲሉ ይወቅሣሉ፤ በዚህ ላይ የእናንተ ምላሽ ምንድን ነው?
የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫን በተመለከተ አንዳንድ ፓርቲዎች መሠል አስተያየቶችን ሲያቀርቡ ሰምተናል፡፡ አንደኛው ወቀሳቸው፣ የታዛቢዎች ምርጫ የተካሄደው ለኛ ሣይነገረን ኢህአዴግ ብቻ ተነግሮት ነው የሚል ነው፤ ይሄ በጣም መሠረታዊ ስህተት ነው፤ ምክንያቱም ኢህአዴግም እነዚህ ፓርቲዎችም ባሉበት የምርጫ ጊዜ ሠሌዳው ቀርቦ ውይይት አድርገንበታል፡፡ ምርጫ ቦርድ ያወጣው የጊዜ ሠሌዳ ኢህአዴግን ጨምሮ ለእያንዳንዱ ፓርቲ አቅርቧል፡፡ ስለዚህ ታህሣሥ 12  የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ እንደነበር ይታወቃል፡፡ የምርጫ ቦርድ ሃላፊዎች በሚዲያም ቀርበው ታህሣሥ 12 የህዝብ ታዛቢዎች ምርጫ እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡ ስለዚህ በሚስጥር የተደረገ ነው፤ የሚለው የተሣሣተ ነው፤ በይፋ በደብዳቤም በሚዲያም ተገልጿል፡፡
በእለቱም ኢህአዴግ አባሎቹ እንዳይመረጡ ጥንቃቄ አድርጓል፡፡ አንዳንድ ቦታ እንኳ አባሎቻችን ሲጠቆሙ “እኔ አባል ነኝ፤ አልችልም” ብለው ከምርጫው የወጡበት ሁኔታ አለ፡፡ ስለዚህ ይህ የተቃዋሚዎች ውንጀላ የተለመደ ሂደቱን ከጅምሩ ጥላሸት የመቀባት አካል ነው፡፡ የተመረጡት የህዝብ ታዛቢዎች ገለልተኛ አይደሉም ለማስባል የሚረዳ ተራ የስም ማጥፋት ሂደት ነው፡፡
1ለ5 የሚባለው ለመንግስት የልማት ስራ የተደራጀ ነው እንጂ የፓርቲው አደረጃጀት አይደለም፡፡ የተቃዋሚም የኢህአዴግም አባል የሆነ ሊኖር ይችላል፤ ስለዚህ የ1ለ5 አደረጃጀትን ሂዱና የህዝብ ታዛቢ ምረጡ ቢል ችግር የለውም ማለት ነው፡፡ ኢህአዴግን ምረጡ ወይም ደጋፊ የሆነን ሰው ምረጡ የሚባል ነገር የለም፡፡ ስለዚህ በ1ለ5 አደረጃጀት ላይ ብዥታ ሊኖር አይገባም፤ አደረጃጀቱ የልማት አደረጃጀት ነው፡፡ ይህን አደረጃጀት ሂዳችሁ ታዛቢ ምረጡ ወይም በምርጫው ተሳተፉ ቢል ነውር አይደለም፡፡ ከዚህ አንፃር ህዝቡ ገለልተኛ ናቸው ያላቸውን ታዛቢዎቹን መርጧል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህ ውንጀላዎች ተቀባይነት የሌላቸው፣ ሂደቱን ጥላሸት ለመቀባት ሆነ ተብሎ የሚደረጉ ናቸው፡፡ የኢህአዴግ አባል ተመርጧል የሚሉ ከሆነና የተመረጠበትን ቦታ ከጠቆሙ እኛም ለማጣራት  ዝግጁ ነን፡፡ ድንገት ሾልኮ የገባ ካለም እንዲወጣ እናደርጋለን፡፡ እስካሁን ግን እንዲህ ያለ ነገር ስለመኖሩ ምንም መረጃ የለንም፡፡ ህዝቡ  ምርጫውን ማካሄዱ መብቱን ማረጋገጫ መንገድ ነው፡፡
የምርጫ ስነ ምግባር ደንቡን ካልፈረሙ ፓርቲዎች ጋር ኢህአዴግ ለመወያየት የማይችልበት መሠረታዊ ምክንያት ምንድን ነው? ደንቡን መፈረምን እንደ ግዴታ ማስቀመጥ የውይይት በርን መዝጋት አይሆንም?  
ደንቡ ሲዘጋጅ ብዙ ሂደት አልፏል፡፡ በወቅቱ የነበሩት ፓርቲዎች በእርጋታ እየተወያዩ ያለፉበት ሂደት ነበር፤ በዚህ ሂደት መድረክ ሶስት ጊዜ ረግጦ ወጥቷል፡፡ መጀመሪያ ሂደቱ ሲጀመር ወደ ውይይቱ ተጋብዞ መጣ፤ ያኔ ከኢህአዴግ ጋር እንጂ ከሌሎች ተቃዋሚዎች ጋር መወያየት የለብኝም አለ፡፡ ኢህአዴግ ደግሞ ብዙ ፓርቲዎች ባሉበት ሃገር፣ የተናጥል ውይይት ከእያንዳንዱ ጋር ማድረግ አይችልም፡፡ መድረክ፤ ሌሎች ፓርቲዎች ተቃዋሚዎች አይደሉም የሚል አመለካከት ስለለው ወጣ፡፡ በሌላ ጊዜም ተጋበዘ፤ ሂደቱን ትቶ ወጣ፡፡ ለ3ኛ ጊዜ 65 ፓርቲዎች ሲወያዩ ገብቶ ሂደቱን ለመበተን ነው ጥረት ያደረገው፤ ግን መጨረሻ ላይ 65 ፓርቲዎቹ ተስማምተው ህግ ሆኖ ወጣ፡፡ ህግ ሆኖ ሲወጣ በህጉ ውስጥ የተቀመጠ ቅድመ ሁኔታ አለ፡፡
የጋራ ምክር ቤቱ አባል ሆኖ ለመቀጠል የፈለገ ፓርቲ ህጉን መፈረም አለበት፡፡ ይሄ ማለት የፖለቲካ ቁርጠኝነት ማረጋገጫ ነው፡፡ ስለዚህ የስነ ምግባር ደንቡ ህግ ሆኖ እንዲወጣ ፓርቲዎቹ በራሳቸው ሊገፉት ይገባል ማለት ነው፡፡ የፊርማ ቅድመ ሁኔታን ኢህአዴግ አላስቀመጠም፤ ራሱ ህጉ ያስቀመጠው ነው፡፡ እያንዳንዱ ፓርቲ በስነምግባር መመራቱን, የፖለቲካ ቁርጠኝነቱን ቀድሞ ማረጋገጥ አለበት ነው የሚለው ህጉ፡፡ ይህን ያረጋገጡ የጋራ ምክር ቤት ውስጥ እየሠሩ ነው፡፡ ከኢህአዴግ ጋር እነዚህ ፓርቲዎች በፕሮግራም የተለዩ ናቸው፡፡ በምርጫ ሂደቱ ላይ ግን በጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው የበሠለ ውይይት እያደረጉ ነው፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ስነ ምግባሩ ያስረናል ብለው ስለሚያስቡና አመፅና ብጥብጥ ለማስነሳት ያግደናል ብለው ስለሚያስቡ ቁርጠኝነት ስላነሣቸው ነው እንጂ ኢህአዴግ በተናጥል አልደራደርም ስላለ አይደለም፡፡ ከዚህ አንፃር ተስማምተን ህግ ሆኖ በወጣ ጉዳይ ላይ lምንድን ነው ተመልሰን ወደ ድርድር የምንገባው? የሚለው ጥያቄ መመለስ አለበት፤ ስለዚህ ተመልሰን ወደ ድርድር የምንገባበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ አሁንም ምርጫ ቦርድ በሚጠራቸው ስብሰባዎች ላይ አብረን እንሣተፋለን፤ የጋራ ምክር ቤት ውስጥ ለመግባት ግን ድርድር አያስፈልገውም፤ በስነምግባር ለመገዛት መስማማት ብቻ ነው፡፡ ኢህአዴግ ያለፈባቸውን ሂደቶች ስናይ ሁልጊዜም በድርድር የሚያምን መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
ለምንድን ነው የአለማቀፍ መስፈርቶችን ያሟላ ስነምግባር ተገዥ ሆናችሁ፣ ለፍትሃዊና ሠላማዊ ምርጫ ውድድር ዝግጁ ያልሆናችሁት የሚለውን ጥያቄ ተቃዋሚዎች መመለስ አለባቸው፡፡ በስነምግባር እንመራ የሚል ውይይት ማካሄድ እንዴት ይቻላል፡፡
ደንቡን ያልፈረሙ መድረክን የመሣሠሉ ድርጅቶች ከኢህአዴግ ጋር መወያየት ቢፈልጉ እንዴት ነው የሚስተናገዱት?
በተቀመጡ ማዕቀፎች መሠረት ይስተናገዳሉ፡፡ ገለልተኛ የሆነው የምርጫ ቦርድ አለ፡፡ ያልተሟሉ ነገሮች ካሉ ለምርጫ ቦርድ እያቀረቡ ሊፈቱ ይችላሉ፡፡ ኢህአዴግ ደግሞ በተቋማዊ አሠራር የሚያምን ድርጅት ነው፡፡ የስነምግባር ደንቡ በሌለበትና የጋራ ምክር ቤቶች ባልተቋቋሙበት ሁኔታ ጥያቄው ቢቀርብ ትክክል ነው፡፡ ከእያንዳንዱ ፓርቲ ጋር ኢህአዴግ እየተወያየ ሊሄድ ይችላል፡፡ አሁን ግን የጋራ ማዕቀፍ  በተዘረጋበት ኢህአዴግ እንዴት ብሎ ነው ከ70 ፓርቲዎች ጋር በተናጠል መወያየት የሚችለው? አሁን ተቋዋሚ አሠራር ተዘርግቷል፡፡ ለመወያየት የፈለገ የጋራ ምክር ቤቱ ውስጥ መግባት አለበት፡፡ ችግሮች ሲፈጠሩ ምክር ቤቱ አጣሪ ኮሚቴ አቋቁሞ ያጣራል፤ መፍትሔ እንዲያገኙም ያደርጋል፡፡ ከዚህ ውጪ በተናጠል መወያየት አይቻልም፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች በራሳቸው የሚፈጠረውን ችግር እንኳ ሣይቀር ኢህአዴግ ፈጠረው ነው የሚሉት፡፡ በአመራር እንኳ የተፈጠረባቸውን ችግር በኢህአዴግ የተፈጠረ ጥፋት አድርገው ይወስዱታል፡፡ ስለዚህ ይሄን መፍረድ ያለበት ህዝቡ ነው፡፡ ህዝቡ ሁሉንም ነገር ያያል፡፡ ማን ነው ጥፋተኛ? ኢህአዴግ ነው ለዲሞክራሲያዊ ስርአትና ፍትሃዊ ምርጫ ዝግጅ ያልሆነው ወይስ ሌላው? የሚለውን መፍረድ ያለበት ህዝቡ ነው፡፡
ኢህአዴግ የገዢነቱን ኃይል ተጠቅሞ በተቃዋሚ ፓርቲዎች የሚደረጉ ሰላማዊ ሰልፎችን ለማፈን ይጥራል የሚሉ ቅሬታዎች ይቀርባሉ፡፡ ኢህአዴግ እንደፓርቲ በሰላማዊ ሰልፍ ላይ ያለው አቋም ምንድን ነው?
ፓርቲያችን ሰላማዊ ሰልፍ ለዜጎች የተሰጠ ህገ መንግስታዊ መብት ነው ብሎ ያምናል፡፡ ይሄ መብት ተግባራዊ የሚሆንባቸው አሰራሮች እንደሚዘረጉ ህገ መንግስቱም አስቀምጧል፡፡ በህገ መንግስቱ ዜጎች በጋራ ሆነው ቅሬታ የማቅረብ፣ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ የማድረግ መብት አላቸው ይላል፡፡ ይሄን መብት ተግባራዊ ለማድረግ አሰራሮች ሊዘረጉ እንደሚችሉ ተቀምጧል፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ አድራጊዎች የህዝቡን ሰላም፣ ክብርና የመሳሰሉ መብቶችን መጣስ እንደሌለባቸው ህገ መንግስቱ አስቀምጧል፡፡
አንድ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማሳወቅ እንደሚጠበቅበትም ተቀምጧል፡፡ የእውቅናውን ጥያቄ የሚያየው አካል የተጠየቀበትን ቦታና ጊዜ ይመለከትና በእውቅና ጥያቄው ላይ ምላሽ ይሰጥበታል፡፡ ቦታ ቀይር ወይም ቀን ቀይር የሚል ምላሽ ይሰጥበታል ማለት ነው፡፡ ዘጠኙ ፓርቲዎች የጠየቁት ቦታ መስቀል አደባባይ ነው፡፡ መስቀል አደባባይ ደግሞ ትልቅ የልማት እንቅስቃሴ እየተደረገበት ያለ ቦታ ነው፡፡ ለ24 ሰዓት ቆመ ማለት ብዙ ነገር ያስተጓጉላል፡፡ ስለዚህ ቦታው ተገቢ አልነበረም ማለት ነው፡፡ በዚህ የተነሳ የተጠየቀው አካል አልተቀበለውም፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች ዕቅዳቸው ልማትን ማደናቀፍ፣ ህዝብን ወደ አመፅ መንዳት እንደሆነ ከዚህ መረዳት ይቻላል፡፡ ኢህአዴግ እንደ ፓርቲ ግን ሰላማዊ ሰልፍ የዜጎች መብት ነው የሚል አቋም አለው፡፡
ኢህአዴግ ለምርጫው ያስቀመጠው ግብ ምንድን ነው? አንዳንድ ወገኖች ሙሉ ለሙሉ አሸናፊ እንዳይሆን ተጠንቅቆ እስከ 15 በመቶ ወንበሮችን ለተቃዋሚዎች ሊለቅ ይችላል የሚል አስተያየት ይሰነዝራሉ?
ኢህአዴግ መንግስት ለመመስረት የሚያስችለውን ወንበር ማግኘት ነው ግቡ፡፡ ይሄ ሲባል ድምፁ እንደ እጩ ቁጥራችንም ይወሰናል በአገሪቱ ባሉ የምርጫ ክልሎች ሁሉ እንወዳደራለን፡፡ በእያንዳንዱ የምርጫ ክልል ለማሸነፍ እንሰራለን ማለት ነው፡፡ ኢህአዴግ ዲሞክራሲን የሚያየው በእውነተኛ ገፅታው ነው፡፡ ዲሞክራሲ በአርቴፊሻል ገፅታ መታየት የለበትም፡፡ ዲሞክራሲ የህዝብ ወሳኝነትን ማረጋገጫ መሳሪያ ነው፡፡ በእያንዳንዱ የምርጫ ክልል ተወዳድረን ህዝቡ የሚመርጠን ከሆነ እሰየው ብለን እንወስዳለን፤ ባይመርጠንም እንቀበላለን፡፡ ከዚህ ውጭ አርቴፊሻል በሆነ መንገድ፣ የህዝብን ውሳኔ ባላከበረ መንገድ የተወሰነ ወንበር እንለቃለን የሚል ሃሳብ የለም፡፡ ወሳኙ ህዝብ ነው፡፡ ምርጫ በውጤት አይመዘንም፤ ዋናው ሂደቱ ነው፡፡ ሂደቱ ማማር አለበት፡፡
በየጊዜው በሚደረጉ ምርጫዎች ላይ የአለማቀፍ ታዛቢዎች ቁጥር እየቀነሰ ሄዶ ዘንድሮ የአውሮፓ ህብረትም ቀርቷል፡፡ አለማቀፍ ታዛቢዎች ከምርጫው ለምን ተገለሉ?
 የኛ ምርጫ ማንም ሊታዘበው የሚችል ምርጫ ነው፡፡ በድብቅ የሚካሄድ ምርጫ ሳይሆን ማንም ሊያየው የሚችል ምርጫ ነው፤ ነገር ግን ምርጫን የአውሮፓ ህብረት ካልታዘበው ችግር ይኖርበታል ብሎ ማሰብ በራሱ የምርጫው ወሳኝ ማን ነው የሚለውን ጥያቄ ውስጥ ያስገባዋል፡፡ ህብረቱ ምርጫውን ለመታዘብ የበጀት እጥረት አለብኝ የመሳሰሉ ምክንያቶችን ነው ያቀረበው፡፡ ስለዚህ ምርጫውን የአፍሪካ ህብረት ይታዘበዋል፣ ከሃገር ውስጥም የተለያዩ የሲቪል ማህበራት ይታዘቡታል፡፡ ዋናው ወሳኙ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው፡፡ ይሄ ህዝብ ነው ውሳኔ የሚሰጠውም የሚታዘበውም፡፡
አለማቀፍ ታዛቢዎች የምርጫውን ገለልተኛነት ከማረጋገጥ አንጻር ምንም ዓይነት ሚና አይኖራቸውም እያሉን ነው?
 ሊታዘቡ ይችላሉ ግን ዋናው ሚና የህዝብ ነው፡፡ እያንዳንዱ ሂደት ከህዝብ ጋር የተገናኘ ነው አለማቀፍ ታዛቢ ተጨማሪ ነው፤ ወሳኝነት የለውም፡፡
ኢህአዴግ በዚህ ምርጫ ሊወዳደረኝ የሚችል ፓርቲ አለ ብሎ ያምናል?
ይሄን ህዝቡ ነው የሚመዝነው፡፡ ቀድመን ባንመዝነው እመርጣለሁ፡፡ ፓርቲዎች ምን እንደሚመስሉ የራሳችን ግምት አለን፡፡ የህዝብን ጥቅም ሊያስጠብቅ የሚችል ሌላ ይህች አገር የጀመረችውን ልማት፣ ዲሞክራሲ በቁርጠኝነት ይዞ ሊሄድ የሚችል ፓርቲ አለ ብለን አናምንም፡፡ በተለያዩ መንገዶች መመዘን እንችላለን፡፡ ከራሳቸው ባህሪ ተነስተን ማለት ነው፡፡ ፓርቲ ማለት የህዝብን ህይወትና ኑሮ ለመቀየር የሚሰራ ፓርቲ ነው፡፡ የትኛው ፓርቲ ነው ህዝቡ ለልማት ሲንቀሳቀስ ከጎኑ ተሰልፎ የሚሳተፈው? የትኛው ፓርቲ ነው ህዝቡ ተግዳሮቶች ሲያጋጥሙት አብሮ እየተንቀሳቀሰ ያለው? የትኛው ፓርቲ ነው ግልፅ የሆነ ሃገር የሚቀይር አማራጭ ፕሮግራም ያለው? የሚለው ስንጠይቅ፣ ሃገርን በዚህ መንገድ ወደፊት የሚያሻግር ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ የለም የሚል ድምዳሜ ላይ ያደርሰናል፡፡ ይሄን ግን ህዝቡ ነው ገምግሞ ሚዛን ላይ ማስቀመጥ ያለበት፡፡ አሁን ቅስቀሳ ባልተጀመረበት ሁኔታ በዚህ ጉዳይ ብዙ አስተያየት መስጠት አይቻልም፤ ግን ህዝብ ይታዘባል፡፡ እናሸንፋለን አናሸንፍም የሚለውም ቅስቀሳ ስለሚሆን የምረጡን ቅስቀሳ ሲካሄድ ብናየው የተሻለ ነው የሚሆነው፡፡
ኢህአዴግ በምርጫ ቦርድ ወይም በምርጫ ሂደቱ ላይ ቅሬታ አለው?
ምርጫ ቦርድ ጋ ቅሬታ የለንም፡፡ ቦርዱ በገለልተኝነት እየሰራ ያለ ተቋም ነው፡፡ ስብሰባ ሲጠራን አስተያየት እንሰጣለን፤ እስካሁን ግን ምንም ቅሬታ የለንም፡፡ ሌሎች ፓርቲዎች የሚያቀርቡትም አብዛኛው ቅሬታ ትክክል አይደለም ብለን እናምናለን፡፡ ፓርቲዎቹ ራሳቸው መጨረስ ያለባቸውን የቤት ስራ ሳይሰሩ፣ በቦርዱ ላይ የሚያቀርቡትን አብዛኞቹን ቅሬታዎች ስንገመግም፣ ቦርዱ ገለልተኛ አይደለም የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ የሚያደርጉት ጥረት መሆኑን እንገነዘባለን ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ ለኛ የሚያደላልን ነገር የለም፡፡

(ምር ያሜቴ የንግበከቤ ፏ አሚተኽ ባንዘነቤ)
(የጉራጊኛ ተረት )
      ከዕለታት አንድ ቀን ሁለት ሊቅ አዋቂ የተባሉ ሳይንቲስቶች ስለንጉሣቸው ሲወያዩ አንደኛው፤
“ንጉሦችና መሪዎች ብዙ ስራ ስለሚበዛባቸው ለዕውቀት ብዙ ቦታ አይሰጡምና ግኝቶቻችንን እንድናሳውቃቸው በየጊዜው እየቀረብን ንግግር እናድርግላቸው” ይላል፡፡
ሁለተኛው፤
“ወዳጄ ሞኝ አትሁን! ንጉሦችና መሪዎች የሚበልጣቸውን ሰው አይወዱም፡፡ ስለዚህም ከማዳመጥና ከመለወጥ ይልቅ አንተን ዝም የሚያሰኙበትን መንገድ ነው ሲያሰላስሉ የሚያድሩት፡፡ የሚሻለው አንተ ድምፅህን አጥፍተህ ምርምርህን መቀጠል ነው፡፡”
አንደኛው፤
“ግዴለህም እንሞክር፡፡ እስከዛሬ ያላወቁትን ነገር ስትነግራቸው በዚያ ይማረኩና፣ ንግግርህን በማድነቅ እንዲያውም ሽልማትና ሹመት ሁሉ ሊሰጡህ ይችላሉ፡፡”
ሁለተኛው፤ ትንሽ ከረር ብሎ፤
“ወዳጄ! ሳይንቲስት ሆነህ እንዴት ሽልማትና ሹመት ያምርሃል፡፡ ዓለም ካንተ ሥራ ውጤት በመጋራት የጥበብህ ተጠቃሚ ለመሆን እንዲችል ለማድረግ መጣጣርህን ትተህ ንጉሥ ንግግሬን ያዳምጡ በማለት እንዴት ልብህን ታወልቃለህ? ይልቁንስ ሊዮናርዶ ዳቬንቺ ያለውን አንድ ምሳሌ ልንገርህ፡-
አንደኛው፤ “ምን አለ?”
ሁለተኛው ቀጠለ:-
‹የባህር እንስሳት የሆኑት ኦይስተሮች ጨረቃ ሙሉ በሆነች ሰዓት አፋቸውን በሰፊው ሙሉ ለሙሉ ይከፍታሉ፡፡ የፈረስ ጫማ ቅርፅ ያላቸው የውሃ እንስሳት ክራቦች ደግሞ የተከፈተውን የኦይስተሮች አፍ ሲያዩ ጠጠር ወይም የባህር አረም ይወረውሩና እዚያ አፍ ውስጥ ይከታሉ፡፡ ኦይስተሮቹ አፋቸውን መግጠም ያቅታቸዋል፡፡ እንደዚያው አፋቸውን አንደከፈቱ ክራቦቹ ምግብ ያደርጓቸዋል፡፡ አፉን በብዛት የሚከፍት ሰው ዕጣ - ፈንታም እንደዚያው ነው፡፡ የሰሚው ሰለባ ይሆናል፡፡” አለው፡፡
* *  *
የምንናገረውን እንወቅ፡፡ የምናውቀውን መጥነን እንናገር፡፡ ለምንናገረው ቦታና ጊዜ እንምረጥ፡፡ የሰሚያችንን ስሜትና እንቅስቃሴ እናጢን፡፡ ቢያንስ በወጉ እንገምት፡፡ “ካፍ ከወጣ አፋፍ” የሚለውን ተረት ለደቂቃም ቢሆን አንዘንጋ!
መጥኖ ትንሽ መናገር ኃይልና አቅምን ማግኘት ነው፤ የሚለውን እንደሚባል ብዙ ፀሐፍት ይናገራሉ፡፡ አንዲ ዋርሆል የተባለው አርቲስት “በህይወቴ የተማርኩት ነገር ቢኖር ዝም ባልኩ ቁጥር የበለጠ ኃይል እንዳለኝ ነው፡፡ ለነገሩ ብዙ አለመናገር ጅል ንግግር ከመናገርም ያድናል” ይለናል፡፡
በሩሲያ የታህሣሣውያን አመፅ (Decemberist Uprising) በመባል የሚታወቀው ንቅንቄ መሪ የነበረውን ኮንድራቲ ራይሌዩቭ ንጉሥ ቀዳማዊ ኒኮላስ ሞት ይፈርድበትና አንገቱ ላይ ገመድ ይጠልቃል፡፡ ከስር የቆመበት ወንበር ሲነሳ ይሰቀላል ተብሎ ሲጠበቅ፤ ገመዱ ተበጠሰና ዳነ፡፡ በዚያን ጊዜ ዕምነት፤ እንዲህ ያለ ሁኔታ ሲከሰት አምላክ መሞቱን አልፈለገም ስለሚባል፤ በል የመጨረሻ ይቅርታ ጥያቄ አቅርብ ተባለ፡፡ ተሰቃዩ እንዲህ አለ፡- “አይ ራሺያ! ገመድ እንኳ በትክክል የማይገመድብሽ አገር!” ንጉሡ፤ “ምን አለ?” ብለው ጠየቁ፡፡ ያለውን ሲነግሯቸው፤ የይቅርታ ደብዳቤውን ቀደዱና “በሉ ጠንካራ ገመድ ሥሩና አሳዩት!” አሉ ይባላል፡፡ ጊዜና ቦታን ማወቅ ለሁሉ ነገር ቁልፍ ነው፡፡
ሀገራዊ ስሜትና ዲሞክራሲያዊ አመለካከት ካልተዋሃዱና፤ በዚያም ላይ ብስለት ካልታከለበት ሁነኛ ለውጥና ዕድገት ለማምጣት ብዙ ጊዜ አዳጋች ነው፡፡ ወቅታዊ ትኩሳት፣ ስሜታዊነት ወይም በፖለቲካዊ አጠራሩ አብዮታዊ ወኔ ብዙ ጊዜ፤ ከድርጊቱ ሞቅ ሞቁ፣ ከተግባሩ ፉከራው፣ መሬት ከረገጠ ለውጡ፤ አየር ባየር የሚሄድ የወሬ ንፋሱ፤ ይበረክታል፡፡ በዚህ ምክንያት ዕሙናዊና ተጨባጭ ለውጥ ከማግኘት ይልቅ እንደሳሙና አረፋ የሚኩረፈረፍ ስሜታዊነት ብቻ ይታያል፡፡ “ምን ያደርጋል ስላስገመገመ፣ ፏ ብሎ ካልዘነመ” የሚለው የጉራጊኛ ተረት የሚጠይቀን ይሄንኑ ነው፡፡

    እኤአ በ1995 በፊፋ የአለማችን ኮከብ እግር ኳስ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠው ላይቤሪያዊ እግር ኳስ ተጫዋች ጆርጅ ዊሃ ሰሞኑን በተካሄደው የአገሪቱ የሴኔት ምርጫ ከፍተኛ ድምጽ በማግኜት አሸናፊ መሆኑን ቢቢሲ ዘገበ፡
በኢቦላ ወረርሽኝ ክፉኛ በተጎዳችዋ ላይቤሪያ ሰሞኑን በተካሄደው ምርጫ ሞንቴራዶ የተባለችውን ግዛት በመወከል የተወዳደረው ዊሃ፣ 78 በመቶ ድምጽ በማግኘት ማሸነፉን የጠቆመው ዘገባው፣ ግዛቲቱን ወክሎ የተወዳደረው ተፎካካሪው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ልጅ ሮበርት ሰርሊፍ 11 በመቶ ድምጽ በማግኜት መሸነፉን አስታውቋል፡፡በምርጫው ካሸነፉት ተወዳዳሪዎች መካከል የቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ቻርለስ ቴለር የቀድሞ የትዳር አጋር ጄዌል ሃዋርድ ቴለር አንዷ ናቸው፡፡
በ2005 በተካሄደው የአገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ተወዳድሮ የነበረው ዊሃ፣ በኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ መሸነፉን ዘገባው አስታውሷል፡፡

ከ162 መንገደኞች እስካሁን የ7ቱ አስከሬን ተገኝቷል

ባለፈው እሁድ 162 ሰዎችን ይዞ በበረራ ቁጥር 8501 ከኢንዶኔዥያዋ ሱራያባ ከተማ ወደ ሲንጋፖር በመጓዝ ላይ እያለ ድንገት የተሰወረው ንብረትነቱ የኤርኤዥያ አየርመንገድ የሆነው ኤርባስ ኤ320-200 አውሮፕላን እጣ ፋንታ አለምን አሳዝኗል፡፡ ኢንዶኔዢያውያንም አዲሱን የፈረንጆች አመት በጥልቅ ሃዘንና በአስከሬን ፍለጋ ተቀብለውታል፡፡
አውሮፕላኑን መሰወሩን ተከትሎ ኢንዶኔዢያና ሌሎች አገራት በመርከብና በአውሮፕላን ታግዘው ለፍለጋ በተሰማሩ በሶስተኛው ቀን የተሰማው ነገር፣ አዲስ አመትን በደስታ ለማክበር ለተዘጋጁ ኢንዶኔዢያውያን ትልቅ መርዶ ሆኗል፡፡
137 አዋቂዎች፣ 17 ህጻናት አንድ ጨቅላ፣ ሁለት አብራሪዎችና አምስት የበረራ ሰራተኞች፣ ሁሉም የጃቫ ባህር ውስጥ ሰምጠው ለህልፈተ ህይወት ተዳርገዋል፡፡ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት መንገደኞች 155 ኢንዶኔዢያውያን፣ 3 ደቡብ ኮርያውያን፣ አንድ እንግሊዛዊ፣ አንድ ፈረንሳዊ፣ አንድ ማሌዢያዊና አንድ ሲንጋፖራዊ ነበሩ ተብሏል፡፡
ለአውሮፕላኑ መከስከስ በሰበብነት የተጠቀሰው አስቸጋሪ የአየር ንብረት ሁኔታ ሲሆን፣ ሌሎች ምክንያቶች እንዳሉ የማጣራቱ ሂደትና የመንገደኞችን አስከሬን የማውጣቱ ሂደት እንደቀጠለ ነው፡፡ እስካለፈው ረቡዕ ድረስም የአራት ወንድ እና የሶስት ሴት መንገደኞች አስከሬን ከባህር መውጣቱንና በአካባቢው ያለው የአየር ንብረት ሁኔታ ፍለጋውን አስቸጋሪ እንዳደረገው ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የኢንዶኔዢያው ፕሬዚደንት ጆኮ ዊዶዶ ግን ምንም እንኳን አስቸጋሪ የአየር ንብረት ሁኔታው ፍለጋውን እጅግ አዳጋች ቢያደርገውም፣ አስከሬንና የአውሮፕላኑን ስብርባሪዎችን የማውጣቱ ስራ በመርከቦችና በሄሊኮፕተሮች በመታገዝ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ባለፈው ማክሰኞ አስታውቀዋል፡፡
በራዳር መረጃዎች ላይ በተደረገ ማጣራት፣ አውሮፕላኑ ከሚገባው የበረራ ከፍታ በላይ ወጥቶ እንደነበርና ይህም ለመከስከሱ ምክንያት እንደሆነው የሚያመላክቱ መረጃዎች ተገኝተዋል፡፡
ከዚህ ቀደም ጥሩ የሚባል የደህንነት ታሪክ እንደነበረው ያስታወሰው ዘገባው፣ በአውሮፕላኖቹ ላይም ይህ ነው የሚባል አስከፊ አደጋ ደርሶ እንደማያውቅ አክሎ ገልጧል፡፡

Monday, 05 January 2015 08:40

2014 አመቱን በቁጥር

55 በመቶ
ስኮትላንድ ከእንግሊዝ ተገንጥላ ራሷን ለመቻል ባካሄደችው ሪፈረንደም ከእንግሊዝ ጋር ብንቆይ ይሻላል ሲሉ ድምጻቸውን የሰጡ ስኮትላንዳውያን፡፡
3 ሺህ 400
በአመቱ ወደተለያዩ የአውሮፓ አገራት ለመግባት ሲሞክሩ በሜዲትራኒያን ባህር ሰጥመው የሞቱ ስደተኞች ቁጥር፡፡
529
በመጋቢት ወር በግብጽ ውስጥ በተካሄደ የፍርድ ሂደት የሞት ፍርድ የተወሰነባቸው የቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሞሃመድ ሙርሲ ደጋፊዎች፡፡

17.6 ትሪሊዮን ዶላር
በአመቱ የቻይና ኢኮኖሚ ከአሜሪካ በመብለጥ በአለማችን ቀዳሚነቱን የያዘበት፡፡

51 ቢሊዮን ዶላር
በኦሎምፒክ ታሪክ ከፍተኛ ወጪ እንደወጣበት የተነገረውና በአመቱ በሩስያ የተካሄደው የ2014 የሱሺ የዊንተር ኦሎምፒክ ውድድር አጠቃላይ ወጪ፡፡

44.4 ሚሊዮን ዶላር
ጂምሰን ዊድ/ ዋይት ፍላወር 1 የተሰኘውና በሴት ሰኣሊያን ከተሰሩ የስዕል ስራዎች በከፍተኛ ገንዘብ በመሸጥ ክብረወሰን ያስመዘገበው የሰዓሊ ጂዮርጂያ ኦኬፌ የስዕል ስራ ባለፈው ህዳር ወር የተሸጠበት ዋጋ፡፡

3 ሺህ
በሶርያና በኢራቅ የሚንቀሳቀሱ አክራሪ እስላማዊ ቡድኖችን በ2014 የተቀላቀሉ አውሮፓውያን ቁጥር፡፡

10 ሚሊዮን
ታዋቂው የቴክኖሎጂ ኩባንያ አፕል ባለፈው መስከረም ወር ለገበያ ያቀረባቸው አይፎን6 እና አይፎን6 ፕላስ ዘመናዊ የሞባይል ቀፎዎች በአንድ ሳምንት ጊዜ የተሸጡበት ቁጥር፡፡

7ሺህ 857
የዓለም የጤና ድርጅት እስከዚህ ሳምንት ድረስ በኢቦላ ሳቢያ ለህልፈተ ህይወት ተዳርገዋል ያላቸው ሰዎች ቁጥር፡፡
61 ሺህ ሴተኛ አዳሪዎች
የእንግሊዝ ብሄራዊ የስታስቲክስ ቢሮ መረጃ እንደሚለው በአገሪቱ በሴተኛ አዳሪነት ስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ሴቶች ቁጥር በተጠናቀቀው የፈረንጆች አመት 61 ሺህ ደርሷል፡፡
አንድ ሴተኛ አዳሪ ለአንድ ጊዜ ወሲባዊ ግንኙነት የምታስከፍለው ገንዘብ በ2014 በአማካይ 67 ፓውንድ መድረሱን የጠቆመው መረጃው፣ አንዲት ሴተኛ አዳሪ በሳምንት በአማካይ ከ23 ወንዶች ጋር ወሲባዊ ግንኙነት ትፈጽማለች ብሏል፡፡
814 ሚሊዮን
በታሪክ በርካታ ዜጎች ድምጽ የሰጡበት ቀዳሚው የፖለቲካ ምርጫ በተባለውና ባለፈው ሚያዝያ ወር በተከናወነው የህንድ ምርጫ ድምጽ የሰጡ የአገሪቱ ዜጎች ቁጥር፡፡
9223372036854775808 ወይም 9 ኩንቲሊዮን
ደቡብ ኮርያዊው ድምጻዊ ፒኤስዋይ ከሁለት አመታት በፊት የለቀቀው ጋንጋም ስታይል የተሰኘ የሙዚቃ ክሊፕ በዩቲዩብ ድረገጽ የታየበት ቁጥር፡፡
(ምንጭ፡- ፋይናንሺያል ታይምስና ሌሎች ድረገጾች)

Monday, 05 January 2015 08:41

የገና ስጦታ

የገና በዓል ለአንድ ሰው ትንሽ ተጨማሪ ደግነት የምናሳይበት ወቅት ነው፡፡
 ቻርልስ ሹልዝ
የገና ስጦታ ሃሳብ -
ለጠላት - ይቅርታን
ለተቀናቃኝ - መቻቻልን
ለወዳጅ - ልብን
ለደንበኛ - መስተንግዶን
ለህፃናት - መልካም አርአያነትን
ለሁሉም - ፍቅርን
ለራስ - አክብሮትን
            ኦሬን አርኖልድ
* ገና የደስታና የፍቅር ቀን ነው፡፡ ፈጣሪ በሁለቱም ያበልፅጋችሁ፡፡
ፊሊፕስ ብሩክስ
* በአሁኑ የልደት በዓል ልጆቻችሁን ሁለት ጥያቄዎች ጠይቋቸው
በመጀመሪያ - “በገና በዓል ለሰዎች ምን መስጠት ትፈልጋላችሁ?”
በመቀጠል - “ለገና እናንተ ምን ትፈልጋላችሁ?”
የመጀመሪያው ጥያቄ፤ የልብን ደግነትና ውጭያዊ አትኩሮትን ያዳብራል፡፡ ሁለተኛው ጥያቄ በመጀመሪያው ካልተገራ ራስ ወዳድነትን ይፈጥራል፡፡
ያልታወቀ ደራሲ
* የገና ሻማ ውብ ነው፡፡ ጨርሶ ሁካታ አያውቅም፡፡ ይልቁንም በዝምታ ለሌሎች ብርሃን በመሆን ራሱን ያቀልጣል፡፡
ኢቫ ሎጉ
* ለገና ሁሉም መንገዶች ወደ አገር ቤት ያመራሉ፡፡
ማርጆሪ ሆልመስ
* ገና በልቡ ውስጥ የሌለው ሰው፣ በዓሉን ጨርሶ ከገና ዛፍ ስር አያገኘውም፡፡
ቻርሎቴ ካርፔንተር