Administrator

Administrator

በተለያዩ ድረ-ገፆች በኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሚያንሸራሽሩት ሃሳብ ይታወቃሉ፡፡ ስለ ኢትዮጵያኒዝም፣ ስለ ፓንአፍሪካኒዝም እንቅስቃሴዎች የተለያዩ ምልከታዎችና ምክረ ሃሳቦችን በማቅረብ ተሰሚነት ካላቸው ኢትዮጵያዊያን ምሁራን አንዱ ናቸው - ፕ/ር ማሞ ሙጬ፡፡ ሰሞኑን ጐንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 60ኛ አመት በዓል ሲያከብር  “Towards Innovative Africa: The Significance of Science, Technology, Engineering and Innovation for Sustainable Development” በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ አቅርበዋል፡፡
ፕሮፌሰሩ በአሁን ሰአት በደቡብ አፍሪካ ሊዋኔ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂና በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ በማስተማር ላይ ይገኛሉ፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ ባለፈው ሳምንት በጐንደር ሳለ ከፕ/ር ማሞ ሙጬ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡



የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና ምንድን ነው?
የኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና የተጀመረው በአሜሪካ ነው፡፡ ከዚያ በእንግሊዝና በፈረንሳይ ቅኝ ወደተያዙ የአፍሪካ ሃገሮች ተዛመተ፡፡ እነ ካሜሮን፣ ሴኔጋል፣ ጋና፣ ናይጄሪያ… ወደ መሳሰሉት ሃገሮች ነው የተስፋፋው። የመስፋፋት ማዕከላት የነበሩት ደግሞ ቤተ - ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ቤተ-ክርስቲያኖች የሃይማኖት አስተምህሮ ዘረኝነት ይደርስባቸው ነበር፡፡ ያንን እንዴት እንቃወመው ብለው ሲያስቡ ነው የኢትዮጵያኒዝም እንቅስቃሴ የመነጨው፡፡ ነጮች ሲሰብኩ ጥቁሮችን የሠይጣን ምሳሌ፣ ነጮቹን የመላእክት አምሳል አድርገው ነበር። ነገር ግን “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” የሚለውን የመፅሃፍ ቅዱስ ጥቅስ ስታይ ነጮቹን የሚወክል ስም የለም፡፡ ኢትዮጵያ የጥቁሮች ሃገርን ብቻ ነው የሚጠቅሰው፡፡ እናም “ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች” ሲል እግዚአብሔር ጥቁሮችን ይሰማል ማለት ነው ብለው ያምናሉ፡፡ የዚህ እንቅስቃሴ አራማጆች ለተጨቆኑ የጥቁር ህዝቦች “ኢትዮጵያን ማኒፌስቶ” የሚል እ.ኤ.አ በ1820 አወጡ። እነ አሜሪካና ሌሎች የበለፀጉት ሃገራት የስጋ ምግብ ሲሰጡ ኢትዮጵያ ግን የመንፈስ ምግብ ሰጠች ማለት ነው፡፡ በዚህ ከሁሉም ትበልጣለች፡፡ በአፍሪካ የነፃነት እንቅስቃሴ የተቋቋመው በኢትዮጵያኒዝም ፍልስፍና መነሻነት ነው፡፡ የመጀመሪያዎቹ የእንቅስቃሴ አራማጆች በኢትዮጵያዊነት ፍቅር የወደቁ ነበሩ፤ በዚህም ታስረዋል ተገድለዋል፡፡
ኢትዮጵያዊነት በዘርና በቋንቋ የሚለካ አይደለም፡፡ ሰዎች የመጣባቸውን ችግር ለመቋቋም ባደረጉት ትግል፣ ባገኙት ውጤትና ስኬት ውስጥ ያለፈ ፍልስፍና ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት የብሄር ትርጉም ያለው አይደለም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ኢትዮጵያዊነትን ከዘር ጋር :- ከአማራ፣ ከትግሬ ከጉራጌ ጋር ወዘተ ያያይዛሉ፤ ነገር ግን ይሄ የተሳሳተ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት ከትግል፣ ከስኬትና ከተገኙ የትግል ድሎች ጋር የተያያዘ ፍልስፍና ያለው ነው፡፡
ጥናትዎን ሲያቀርቡ፣ “ወደ ምዕራባውያኑ የሄደው ሁሉ የኛ ነገር ነው፤ ተመልሶ መምጣቱ አይቀርም” ብለው ነበር፡፡ ምን ለማለት ነው?
እኛ ሁሉም ነገር አለን፡፡ ቋንቋው፣ የስነ ህንፃ ጥበቡ፣ ስነፅሁፉ… ሁሉም አለን፡፡ ግን የራሳችንን ትተን ሌላውን ወደ መኮረጁ ገባን፣ ኩረጃ ጥሩ አይደለም፡፡ አወዛግቦናል። ሁሉንም ሚስጥራችንን የጥንት ኢትዮጵያውያን ተንትነው አስቀምጠውልናል፡፡ የእግዚአብሔር ማንነት ሚስጥር፣ የቀንና ሌሊት ሚስጥር የመሳሰሉት፡፡ በአቡሻከር እስከ 15 እና 22 ፕላኔቶ አሉ የሚል ተፅፏል፡፡ እኛ 9 ፕላኔቶች አሉ ተብለን ነው የተማርነው፡፡ አሁን ፈረንጆቹ 13 አድርሰዋቸዋል፡፡ እንግዲህ እኛ በመደበኛ ትምህርት ባንማረውም የቀደሙት ግን 22 ፕላኔቶች አሉ ብለው በአቡሻከር አስቀምጠዋል፡፡ አሁን እኔ ፕሮፌሰር ተብዬ በድጋሚ 13 ፕላኔቶች አሉ እየተባልኩ ልማር ነው ማለት ነው፡፡
ማንዴላ ከእስር ቤት ሲወጣ ነው ኤርትራ ከኢትዮጵያ የተገነጠለችው፡፡ ማንዴላ በወቅቱ ምን አለ አሉ? ለአቶ መለስ እና ለአቶ ኢሳያስ ስልክ ደውሎ “እንዴት አንድ ህዝብ ትከፋፍላላችሁ እኛ ከአውሮፓ የመጡ አፍሪካኖችንና ከአፍሪካ የተፈጠሩ አፍሪካኖችን አንድ እያደረግን፣ ለእናንተ አንድ የሆነውን ህዝብ እንዴት ትለያያላችሁ”? ብሏል ይባላል፡፡ በወቅቱም አቶ መለስ እና አቶ ኢሳያስ አንደኛቸው ፕሬዚዳንት አንደኛቸው ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ ምክር ለግሷል፡፡ አገሪቱ ሳትገነጠል ማለት ነው፡፡  ግን አልተቀበሉትም፤ መከፋፈሉ መጣ፡፡
እኔ ወደ ደቡብ አፍሪካ ስሄድ፣ አንድ ደስ ያለኝ ነገር ምርጫ ሲያደርጉ ማንም ይመረጥ ዋናው የምርጫው ሂደት ውጤታማ መሆኑ ነው፡፡ ተቃዋሚ ነኝ የሚለው ወገን ተጠቃሁ አይልም፡፡ ለምሳሌ አሁን በስልጣን ላይ ያለውን መሪ ብዙዎቹ አይወዱትም ግን ምርጫው ከወገናዊነት የፀዳ መሆኑን ነው የሚናገሩት፡፡ በዚህ ሂደት አምስት ጊዜ ሰላማዊ ምርጫ አድርገዋል፡፡ እኔ በዚህ በጣም  እኮራባቸዋለሁ፡፡ ነጮች ጥቁርን ሰይጣን ነው እንጂ ሰው አይደለም ይሉ ነበር፡፡ እነ ማንዴላ ያንን ችግር በግጭት ሳይሆን በእርቅና በሰላማዊ መንገድ ነው የፈቱት፡፡ አሁን ከአፍሪካ ሃገራት መካከል እነ ቻድ፣ ማሊ፣ ሊቢያ ሌሎችም በግጭት ውስጥ ናቸው፡፡ እነዚህ ሃገሮች የደቡብ አፍሪካን ፈለግ ተከትለው ችግራቸውን ቢፈቱ ህዝባቸው ምንኛ በታደለ ነበር፡፡ በኢትዮጵያም ቢሆን ለግጭቶች መላ ሲፈለግ በመገዳደል ባይሆን ጥሩ ነው፡፡ በመናናቅ፣ በመዘላለፍ፣ ባለመተማመንና በውይይት ቢሆን ሃገርን በማስበለጥ፣ በመረዳዳት፣ የአመለካከት ለውጥ በማምጣትና በመወያየት መሆን አለበት፡፡ እኛ የፈለግነው ወገን ሥልጣን ካልያዘ ሞተን እንገኛለን የሚለው አስተሳሰብ መለወጥ ይኖርበታል፡፡
በቀጣይ አመት በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ይካሄዳል? ከምርጫው ምን ይጠብቃል?
ምርጫው እግዚአብሄር ታክሎበትም ቢሆን ንፁህ መሆን አለበት፡፡ ንፁህ ከሆነና ያ ባህል ከተፈጠረ ለኢትዮጵያ ትልቅ ስኬት ነው፡፡ ደቡብ አፍሪካዎች ይሄን ማድረግ ችለዋል፡፡ በእነሱ እየቀናሁባቸው ነው፡፡ አሁን ለምሳሌ ዙማን ብዙዎች አይወዱትም፡፡ ኢኮኖሚያው ላይ ጥያቄ አለበት፤ ነገር ግን መርጠውታል፡፡ ዋናው ማን ተመረጠ የሚለው ሳይሆን ሂደቱን ሰው ማመን አለበት፡፡ ንፁህና እንከን የለሽ ነው ብሎ ከልቡ ሊቀበለው ይገባል፡፡ አለበለዚያ ምርጫ አያስፈልገንም፡፡
የዳያስፖራው ፖለቲካ ለዚህች ሃገር ባለው ፋይዳ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖች አሉ፡፡ እርስዎስ ምን ይላሉ?
ከቅንጅት በፊት እዚህ ሃገር መጥቼ ነበር፡፡ ገጠር ድረስ በበቅሎ ሄጄ አይቸዋለሁ፡፡ በወቅቱ የገጠሩ ሰው ሁሉ ስለምርጫ በሚገባ እንዳወቀ የተረዳሁበት አጋጣሚ ነበር፡፡ በጣም ደስ ይላል ብዬ ተስፋ አድርጌ ወደ መጣሁበት ተመለስኩ፡፡ ከምርጫው በኋላ ግን የሆነው አሳዛኝ ነው፡፡ በወቅቱም በፃፍኩት ፅሁፍ፤ እንዲህ ያለ እድል ተገኝቶ እንዴት እናበላሸዋለን ብዬ ተቆጭቻለሁ። ኢትዮጵያ አንዳች ነገር እንዳጣች ተናግሬያለሁ፡፡ በውጪ ሃገር የተለያዩ ተቃዋሚዎች አሉ፡፡ ግን በጣም የተበጣጠሱ፣ በአንድነት ተቀናጅተው ሃይል መሆን ያልቻሉ ናቸው፡፡ በሃገራችን ለውጥን በሰላማዊ መንገድ ማምጣት አለብን የሚለው አስተሳሰብ ቢዳብር ጥሩ ነው። እኔ ለኢትዮጵያ ጥሩ ነገር ነው የምመኘው፡፡
በዳያስፖራው አካባቢ የከፋ ዘረኝነት ይራመዳል ይባላል፡፡ እርስዎም በፅሁፍዎ ይሄን ነገር በተደጋጋሚ ይገልፁታል፡፡ የዚህ የዘረኝነት አንድምታው ምንድን ነው?
አንድ ጓደኛ አለኝ፡፡ ከሱ ጋር ሆነን አንድ ጊዜ የብሄራዊ መግባባት መድረክ ፈጠርን፡፡ ሁሉንም ብሄሮች የብሄር ፖለቲከኞች ጠራን፤ ኦነግን ጨምሮ፡፡ ግን ለመወያየት ከባድ ነበር፤ ዘረኝነት አይሎ አስቸገረን። ዘረኝነታቸው የእውነት ይሁን የይስሙላ አላውቅም፡፡ እኔን “የግራዚያኒን ሃውልት ለምን ትቃወማላችሁ? የአፄ ምኒልክ እያለ” ይሉኝ ነበር፡፡ እኔም በወቅቱ ተናድጄ “እንዴት አፄ ምኒልክን እንደዚህ ትላላችሁ” ብዬአቸዋለሁ። አፄ ምኒልክ ለአፍሪካ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል፡፡ ለአፍሪካውያን ድል የአፄ ምኒልክ እጅ አለበት፤ እሳቸውን ማጥቃት ማለት ጠቅላላ ኢትዮጵያን ማጥቃት ነው ብዬ ተቃውሜያለሁ፡፡ እንዲህ ያሉ ፅንፍ የያዙ አለመግባባቶች ይታያሉ፡፡ ግን ሰው ከዚህ ወጥቶ በውይይት መግባባትን ቢለምድ ጥሩ ነው፡፡ በአንድ የሆነ መላ ኢትዮጵያ አሁን ካለችበት የዘር ፖለቲካ ብትወጣ ጥሩ ነው፡፡
ይሄ በቅርቡ እውን የሚሆን ይመስልዎታል?
አሁን እንግዲህ እዚህ የምትኖሩት ናችሁ ይሄን የምታውቁት፡፡ እኔ ውጭ ነው የምኖረው፡፡ ነገር ግን የዘር ፖለቲካ አይጠቅምም የሚለው አቋሜ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊነት፣ አፍሪካዊነት ብቻ ይበቃል፡፡ ወደ ታች ወርዶ በቋንቋ ምናምን መከፋፈሉ አያዋጣም፡፡ ዋናው የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ መብቶቹ መጠበቃቸው ነው። ቋንቋ የሰውን ልጅ ሊከፋፍል አይገባውም፡፡ ለምሳሌ በደቡብ አፍሪካ 11 ያህል ቋንቋዎች ለማስተማሪያነት ይውላሉ፡፡ በእነሱ ዘንድ ቋንቋዎቹ ከመግባቢያነት ያለፈ ትርጉም የላቸውም፡፡ እኔ አሁን ኦሮሚኛ፣ ትግሪኛ፣ አማርኛ… የሌሎች ቋንቋዎችን ሙዚቃዎችም ስሰማ ደስ ይለኛል፡፡ ታዲያ እንዴት ነው አማራ ብዬ ራሴን የምነጥለው፡፡ በአማራ ክልል የኦሮሞ ዞን ማለት ምን ማለት ነው? እኔ ምን እንደሆነ አይገባኝም፡፡ መብቶች በሙሉ በህግ ጥበቃ ከተደረገላቸው በቂ ነው፡፡ እኔ አሁን ማሞ ሙጬ ነው ስሜ፡፡ አላውቅም አባቴ ኦሮሞ ሊሆን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ኦሮሞዎች ጎንደርን ለረጅም አመታት አስተዳድረዋል፡፡ ጎንደር ቤተ መንግስት ውስጥ ኦሮሚኛ ቋንቋ ይነገር ነበር፡፡ ኢትዮጵያዊነት ፍፁም የተደባለቀና የተቀላቀለ ነው፡፡
የፓን አፍሪካኒዝም እንቅስቃሴ ምን ያህል አፍሪካን ያስተሳስራል ይላሉ?
በዚህ አመት በፓን አፍሪካኒዝም ላይ መፅሃፍ ላወጣ እያዘጋጀሁ ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያን ከኢትዮጵያዊነትም ባለፈ አፍሪካዊነት ላይ አስቀድመን ብንንቀሳቀስ ለእኛም ሆነ ለአፍሪካውያን ትልድ ድል ነው፡፡ ህዝቡ የፓን አፍሪካኒዝምን ፅንሰ ሃሳብ ቢረዳ፣ ሌሎች አፍሪካውያን በፊት ከሚሰጡን ፍቅር የላቀ ፍቅር ይሰጡን ነበር፡፡ አሁን ያሉት ፖለቲከኞች በዚህ መንፈስ እንዲራመዱ እግዚሃር ይርዳቸው፡፡ ከዘረኝነት ወጥተው በኢትዮጵያዊነት እና በአፍሪካዊነት እንዲያስቡ እንፀልይላቸዋለን፡፡
በመንግስት በኩል ኢኮኖሚው እያደገ መሆኑ ይነገራል፡፡ በሌላ በኩል ግን ዕድገቱ ህዝቡን ከድህነት አላወጣውም የሚል ትችት ይሰነዘራል፡፡ የእርስዎ አስተያየት ምንድነው?
በኢኮኖሚ እድገት ብሄራዊ ገቢን ማብዛት ብቻውን ጥቅም የለውም፡፡ ሰዎችን በማፈናቀል መሬት ለባዕድ በመስጠት የሚመጣ እድገት ጥሩ አይደለም፡፡ እድገት ማለት የህዝቡን ህይወት መቀየር ሲችል ነው፡፡ እንደዚህ አይነት ሁኔታ ካልተፈጠረ እድገት አለ ለማለት ይከብዳል፡፡ የህዝቡን ህይወት መቀየር መቻል አለበት፡፡ ይሄን ለማድረግ ጥሩ የሆነ የኢኮኖሚ ፖሊሲና ማህበራዊ አቅጣጫ ያስፈልጋል፡፡ ብዙዎቹ የአፍሪካ ሃገሮች ይሄ ይጎድላቸዋል፡፡
ብዙውን ጊዜ በውጭ እርዳታ ላይ ስለሚንጠለጠሉ ያመኑበትን ፖሊሲያቸውን ትተው በለጋሾች ለመመራት ይገደዳሉ፡፡ ሌላው መኮረጅም ጥሩ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ከቻይና መማር ያለብን እንዴት ጎበዝ እንደሆኑ ብቻ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ የራስን የቤት ስራ መስራት ነው፡፡ አሁን ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ሃብት ስንመለከት፣ አንድም ዜጋዋ መራብ አልነበረበትም፡፡   

“ሰዌን ሰንትዲ ጌለእዮ ኤኬቴስ” - የወላይታ ተረት

             ኒኮስ ካዛንትዛኪስ፤ “ዞርባ ዘ ግሪክ” የሚከተለውን ይላል፤ ሟቹ ዶክተር ዮናስ አድማሱ እንደተረጐመው:-  
ከዕለታት አንድ ቀን ጠዋት በአንድ ዛፍ ቅርፊት ሥር ሊፈለፈል የሚዘጋጅ አንድ የቢራቢሮ ሙጭ አፍጥጬ ስመለከት፣ ቢራቢሮዋ የተሸፈነችበትን ኮፈን ሰብራ ለመውጣት ቀዳዳ ስትቦረቡር አስተዋልኩ፡፡ ትንሽ ጠበቅሁ፣ ነገር ግን ጨርሳ ለመውጣት ብዙ ጊዜ ስለፈጀች ትዕግስቴን ጨረስኩ፡፡ ከዚያም ትንሽ ጐንበስ ብዬ ሙቀት እንዲሆናት በማለት ተነፈስኩባት፡፡ የምችለውን ያህል በፍጥነት እየተነፈስኩ ሙቀት ዘራሁባት፡፡ ዓይኔ እያየ እዚያው አፍንጫዬ ሥር ታምር ሲሰራ ተመለከትኩ፡፡ እንደህይወት ቅጽበት፡፡
ኮፈኑ ተገለጠና ቢራቢሮዋ ቀስ እያለች መውጣት ጀመረች፡፡ ክንፎቿ ወደኋላ ታጥፈውና ጭምድድ ብለው ስመለከት መላ ሰውነቴን የወረረኝን ድንጋጤ ምን ጊዜም አልረሳውም፡፡ ምስኪኗ ቢራቢሮ ባላት ኃይል ሁሉ ሰውነቷ በሙሉ እየተንዘፈዘፈ ክንፎቿን ለመዘርጋት ሞከረች፡፡ እንደገና ጐንበስ ብዬ በትንፋሼ ልረዳት ሞከርኩ፡፡ ሙከራዬ ከንቱ ነበር፡፡ ቢራቢሮዋ መውጣት የነበረባት በዝግታ፣ ክንፎቿም መዘርጋት የነበረባቸው በፀሐይ ሙቀት በዝግመት መሆን ነበረበት፡፡ አሁን ግን አልሆነም፡፡ ይረዳታል ያልኩት የኔ ትንፋሽ ቢራቢሮዋን ጊዜዋ ከመድረሱ በፊት፣ ክንፎቿም ጭምድድ ብለው የግድ ከኮፈኗ እንድትፈለፈል አድርጓት ኖሯል፡፡ ተስፋ በቆረጠ ሁኔታ ለጥቂት ሴኮንዶች ከታገለች በኋላ መዳፌ ላይ ሕይወቷ አለፈ፡፡
ሸማ በፈርጅ እንደሚለበስ ዕውቀትም ፈርጅ ፈርጅ አለው፡፡ ከዕውቀትና ከተመክሮም በላይ ተፈጠሮ የራሱ ሂደት፣ የራሱ የላቀ የተለቀ እንዲሁም የጠለቀ መንገድ አለው፡፡ ከልኩ በላይ ሙቀት የተሰጣት ቢራቢሮ፣ ከልኩ በላይ ትንፋሽ የበዛባት ሙጭ ከተፈጥሮ ማህፀን ትላቀቅ እንጂ፤ ህይወቷን መቀጠል አልሆነላትም - ከተፈጥሮአዊ ጉዞዋ ቀድሞውኑ ተናጥባለችና ሁሉም የየራሱ ተፈጥሮአዊ ሂደት አለው - የየራሱም አቅም አለው፡፡ ስለሆነም በራሱ ሐዲድ ላይ እንጂ አንዱ በሌላው ሐዲድ ላይ አይሄድም፡፡ ዛሬ ሁሉም መንገዶች ወደ ሮማ አያመሩም፡፡ የተለያዩት መንገዶች ወደተለያዩ ከተሞች ይሄዳሉ እንጂ!
“”ቆሎ ለዘር፣ እንዶድ ለድግር አይሆንም” ይሏልና ሁሉን በቦታው ማዋል እጅግ ተገቢ ነገር ነው፡፡ በዓለም ላይ፤ በተለይም በፖለቲካ ትግል ውስጥ፣ ጊዜ የለየ፣ ቦታ የመረጠ ብቻ ነውና እግቡ የሚደርሰው፡፡
ጥበበኛ የፖለቲካ መሪ፣ ታጋይ፣ የሥራ ኃላፊ፣ የጐበዝ አለቃ ማስተዋል ካለበት ፍሬ ጉዳዮች መካከል የሚከተሉት የሮበርት ግሪን አስተያየቶች ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በማናቸውም የሥልጣን ዘመን የሚያጋጥሙ “አምስት ዓይነት አደገኛ ሰዎች አሉ - በዓለም ላይ - ከእነዚህ ተጠንቀቅ” ሲል እንዲህ ይደረድራቸዋል :-
አንደኞቹ - ትዕቢተኛና ኩራተኛ ሰዎች ናቸው - ከነዚህ ዓይነቶቹ ራቅ፡፡
ሁለተኞቹ - ተስፋ - በሚያስቆርጥ ሁኔታ አደጋ ላይ ነን ብለው የሚያስቡ ስሜታቸው ስስና በቀላሉ ተሠባሪ ናቸው - ረዥም ጊዜ ራቃቸው፡፡ ሦስተኞቹ - እነ አቶ ጥርጣሬ ናቸው፡፡ እንደ ስታሊን ያሉቱ ናቸው፡፡ ሁሉ ሰው አጥፊዬ ነው የሚሉ ናቸው፡፡ ዒላማቸው ያደረጉህ ከመሰለህ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርግ፡፡ አራተኞቹ - የረዥም ጊዜ የማስታወስ ችሎታ ያላቸው እባቦች የሚባሉት ዓይነት ናቸው፡፡ አይቆጡም፣ በፊት ለፊት የሚያሳዩት የንዴት ባህሪ የለም - ያደባሉ፣ ያሰላሉ፤ ጊዜ ይጠብቃሉ፡፡ ይበቀላሉ፡፡ ማሺንክ ናቸው፡፡ ከእንዲህ ያለው እባብ እጥፍ -ጥንቃቄ አድርግ፡፡ አንዴ ካቆሰልከው እስከመጨረሻው ተገላገለው - ከሱ ጋር ግማሽ መንገድ አትሂድ - ከእይታህ ውጪ አድርገው፡፡ አምስተኞቹ - ግልብ፣ የሚያደርጉትን አስበው የማያደርጉ፣ አብዛኛውን ጊዜ ዕውቀት - ጠገብ ያልሆኑ (Unintelligent) ናቸው፡፡ ከምታስበው በላይ የማይታለሉ ናቸው፡፡ እንዲህ ያለ ሰው ከመጉዳቱ ወይም ከመበቀሉ ይልቅ የሚከፋው ጊዜህን፣ ጉልበትህን፣ ሀብትህን ከማባከኑም አልፎ ተርፎ ንጽህናህን ያጐድፍብሃል፡፡ በግልጽ አጥንተህ በግልጽ ፈትሸው፡፡
በሀገራችን ከፖለቲካ፣ ከኢኮኖሚና ከማህበራዊ ችግሮች ለመላቀቅ በርካታ ጊዜ ጥያቄዎች ቢነሱም ባንዱ ችግር ላይ ሌላ እየጨመረ መፍትሔ እየራቀ መሄዱ ገሃድ ነው፡፡
ዕውቁ የሀገራችን ገጣሚና ፀሐፌ - ተውኔት ፀጋዬ ገ/መድህን በምኒልክ አንደበት “ችግሬን አላገኛችሁልኝም፡፡ ህመሜን አላወቃችሁልኝም፡፡ መድሃኒት አልኳችሁ እንጂ ለመከራዬ …አውጫጪኝ ምን ያደርግልኛል?”
እንዲሉ፤ ለችግራችን መድሃኒት ዛሬም በጋራ መፈለግ አለብን፡፡ የቃናችን፣ የልሣናችን፤ የቋንቋችን ህብር በአንድ ካልተቃኘ አገራችንን ከገባችበት አረንቋ ማውጣት ይከብደናል፡፡
“አንዱ ባለቀረርቶ፣ ሌላው ባለቄሬርሳ፣ ሦስተኛውም ያው ባለሽለላ ናችሁ፡፡ የሁላችሁም ውጤት በጠቅላላው ሲደመር፣ አንድ ባዶ ፉከራ ብቻ ነው ጩኸታችሁ፡፡ በኔ በምኒልክ ላይ ተቀያየራችሁብኝ እንጂ እናንተ ከቶም አልተቀየራችሁም፡፡ አንድ ናችሁ፡፡ ዛቻ፡፡ ማስፈራሪያ ብቻ…” ይላል፤ ያው ፀሐፌ- ተውኔት፡፡
ጩኸታችንን ቀንሰን ፍሬ የሚያፈራ ሥራ እንሥራ! በየጊዜው “በወደቀው ግንድ ላይ ምሳር ከማብዛት” የተለየ ነገር አገኘን ስንል፤ መልሰን ለጋውን ትውልድም ያላንዳች በሳል ጉዞ የምንረመርም ከሆነ፤ ሁለት ትውልድ ባንድ ጊዜ እናጣለን፡፡ ትውልድን ለማለምለም ገና ብርቱ ጥረት ይጠበቅብናል፡፡ ካለፈው እየተማርን መጪውን ካላሳመርን ውሃ - ወቀጣ ነው የሚሆነው፡፡ ከሁሉም ወገን “በፈት እየተለማመዱ ልጃገረድ ያገቧል”ን በቀና ትርጉሙ አይተን፣ “ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል” ካላልን ከልማታችን ጥፋታችን እንደሚበረክት ልብ እንበል!!

የኩባንያዋ ዓመታዊ ገቢ 5ሚ.ዶላር ነው

         ‘ሶል ሪበልስ’ የተባለው የጫማ አምራች ኩባንያ መስራችና ባለቤት የሆነችው ኢትጵያዊቷ የንግድ ስራ ፈጣሪ ቤተልሄም ጥላሁን፣ በታዋቂው ፎርብስ መጽሄት ለአርአያነት የሚበቁ የአመቱ 10 አፍሪካውያን ወጣት ሚሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ ተካተተች፡፡
ፎርብስ ሰሞኑን ባወጣው ዝርዝር ከ39 አመት ዕድሜ በታች ያሉና በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር የሚያንቀሳቅሱ ቢዝነሶች ያሏቸው አፍሪካውያን በማለት ከጠቀሳቸው አስር ባለሃብቶች አንዷ የሆነችው ቤተልሄም፤ ከአስር አመታት በፊት ያቋቋመችው ‘ሶል ሪበልስ’ በአሁኑ ወቅት አምስት ሚሊዮን ዶላር አመታዊ ገቢ በማግኘት ላይ እንደሚገኝ ተነግሯል፡፡
የ34 አመቷ ኢትየጵያዊት ቤተልሄም ጥላሁን ያቋቋመችው የጫማ አምራች ኩባንያ፣ ባህላዊውን የጫማ አሰራር ዘመናዊ መልክ በመስጠት በተለያዩ ዲዛይኖች የሚያመርታቸውን ምርቶቹን ወደተለያዩ የአለም አገራት በመላክ ከአመት ወደ አመት ትርፋማነቱን እያሳደገ የመጣ ሲሆን፣ ለ100 ያህል ዜጎችም የስራ ዕድል ፈጥሯል፡፡
በአፍሪካ ውስጥ በሃያዎቹና በሰላሳዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ ሆኖ በሚሊዮን ዶላሮች የሚቆጠር ሃብት ማፍራት መቻል፣ በእርግጥም አድናቆትና ሙገሳ የሚያስፈልገው ትልቅ ስኬት ነው ያለው የፎርብስ ዘጋቢ ሞፎኖቦንግ ኒስሄ፣ እ.ኤ.አ ከ2012 ጀምሮ መሰል ስኬት ያስመዘገቡ 10 ተጠቃሽና ለአርአያነት የሚበቁ ሚሊየነሮችን በየአመቱ እየመረጠ ይፋ ማድረጉንም አስታውሷል፡፡
ፎርብስ መጽሄት ለአርአያነት የሚበቁ የአመቱ 10 አፍሪካውያን ወጣት ሚሊየነሮች በማለት ከመረጣቸው ተጠቃሽ ባለሃብቶች መካከል፣ ብቸኛዋ ሴት ቤተልሄም መሆኗን ከመጽሄቱ ድረገጽ ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡
በንግድ ስራ ፈጠራ መስክ ባስመዘገበችው ተጨባጭ ስኬት ፎርብስን ጨምሮ በተለያዩ ታዋቂ መጽሄቶች፣ በአህጉራዊና አለማቀፍ ድርጅቶች፣ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችና መገኛኛ ብዙሃን ስሟ በተደጋጋሚ በግንባር ቀደምትነት የተጠቀሰው ቤተልሄም፣ በዘርፉ በርካታ ሽልማቶችን ለመቀበል ችላለች፡፡
በዝርዝሩ ውስጥ በትራንስፖርትና በነዳጅ ምርት፣ በፋሽን ስራ፣ በሸቀጣ ሸቀጥ ንግድ፣ በአምራች ኢንዱስትሪ፣ በኤሌክትሮኒክ ንግድ፣ በቴሌኮም፣ በኮምፒውተርና በሌሎች የቴክኖሎጂ መስኮች ተሰማርተው ትርፋማ የንግድ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ የታንዛኒያ፣ የናይጀሪያ፣ የኬኒያና የደቡብ አፍሪካ ሚሊየነሮች ተካተዋል፡፡

            ጥንታውያኑ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና የጎንደር ፋሲለደስ አብያተ መንግስታት ህንፃዎች ለዘመናት ሳይፈራርሱ እንዲቆዩ ለማድረግ ያስችላል በተባለው ናኖ ቴክኖሎጂ ለማደስ ታቅዷል፡፡
በጎንደር ዩኒቨርሲ የእውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰለሞን መስፍን፤ ቴክኖሎጂው በዓለም ላይ እየተስፋፋ እንደሆነ ጠቁመው፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲም የናኖ ቴክኖሎጂ ማዕከል አቋቁሞ በቅድሚያ በአብያተ ክርስቲያናቱና ቤተመንግስቱ ህንፃዎች ላይ ቴክኖሎጂውን ቻመተግበር እቅድ መያዙን፤ በቀጣይ ዓመትም ፕሮጀክቱ እንደሚጀመር ተናግረዋል፡፡
የፊዚክስ የፈጠራ ውጤት የሆነው ናኖ ቴክኖሎጂ ከሞሎኪዮሎች (ቅንጣቶች) የተፈጠረ ሲሆን ከሲሚንቶ ጋር በመቀላቀል ለህንፃ ግንባታዎችና እድሳቶች ከዋለ፣ ለህንፃው ጥንካሬና እድሜ ይሰጠዋል ተብሏል፡፡
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ናኖ ቴክኖሎጂን በሃገራችን ለማስተዋወቅ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑ ጠቁመው፤ “ናኖ ግሎባል” ከሚባል ድርጅት ጋር አብሮ ለመስራት ስምምነት መፈረሙን ገልፀዋል፡፡ በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂው ማዕከል የተቋቋመ ሲሆን የቴክኖሎጂው ሊህቃን ከውጭ ሀገር መጥተው የላሊበላና ጎንደር አብያተ ክርስቲናትና ቤተመንግስታት እንዴት ይቀቡ በሚለው ላይ የምርምር ስራዎችን ያከናውናሉ ብለዋል፤ አቶ ሰለሞን፡፡
ቴክኖሎጂው በምግብ ሳይንስ፣ በኤሌክትሮኒክስ ቁሶች፣ በኢነርጂ፣ በህክምና፣ በህንፃዎች ወዘተ ላይ እየተሰራበት ሲሆን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሚከፈተው ማዕከል ለወደፊት አቅሙ ሲጠናከር የመኪና አካላትንም በቴክኖሎጂው ለመቀባት እቅድ መያዙ ተጠቁሟል፡፡

                 የመን ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ታዚ በተባለ አካባቢ በቁጥጥር ስር የዋሉትንና የስደተኝነትን መስፈርት አያሟሉም፣ ጥገኝነት ጠያቂም አይደሉም ያለቻቸውን 44 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወደ አገራቸው ልትመልስ እንደሆነ የመን ታይምስ ጋዜጣ ከትናንት በስቲያ ከሰንዓ ዘገበ፡፡
የኮስት ጋርድ ቃል አቀባይ የሆኑትን ሁሴን አል ሃራዚን ጠቅሶ ጋዜጣው ከሰንኣ እንደዘገበው፣ በኢትዮጵያዊ ካፒቴን በምትንቀሳቀስ ጀልባ ተሳፍረው ሲጓዙ ሞካ ተብሎ ከሚጠራው የየመን ወደብ አቅራቢያ የተያዙት እነዚሁ ስደተኞች፣ በአካባቢው ወደሚገኝ የደህንነት ማዕከል እንዲገቡ ተደርገዋል፡፡
በኢትዮጵያና በየመን መካከል ይህ ነው የሚባል የጎላ ግጭት እንደሌለ የገለጹት የኮስት ጋርድ አካባቢ የኦፕሬሽን ዳይሬክተር ኮሎኔል ሳልህ አልፋኒ በበኩላቸው፤ አገሪቱ ኢትዮጵያውያንን በአግባቡ እንደምትይዝና እንደማንኛውም ስደተኛ እንደማታያቸው ተናግረዋል፡፡
“ኢትዮጵያውያኑ ከአገራቸው ወጥተው ወደ የመን ለመግባት ጥረት ያደረጉት በሁለት ምክንያቶች ነው፡፡ አንደኛው በየመን የስራ ዕድል ለማግኘት ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ በየመን በኩል አድርገው ወደሌሎች የመካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመግባት ነው” ብለዋል ኮሎኔል አልፋኒ፡፡
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲ የመገናኛ ብዙሃን ረዳት የሆኑት ዚያድ አል አልአያ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያኑ ስደተኞች ወደ አገሪቱ ለመግባት የሞከሩት የኢኮኖሚ ችግራቸውን ለመፍታት እንጂ ጥገኝነት ለመጠየቅ በማሰብ አለመሆኑንና በስደተኞች መጠለያ ለመቆየት እንደማይፈልጉ ተናግረዋል፡፡ ወደ አገሪቱ የሚገቡ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደ ሶማሊያዊያን ስደተኞች በአፋጣኝ በስደተኛ ጣቢያዎች መኖር የሚያስችላቸውን ፍቃድ እንደማያገኙና በአጠቃላይም በስደተኝነት ለመቀበል ብቁ እንዳልሆኑ ገልጸዋል፡፡
በሰንዓ የፓስፖርትና የኢሚግሬሽን ባለስልጣን የስደተኞች መላሽ ክፍል ስራ አስኪያጅ የሆኑት አብዱላ አል ዙርቃ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያውያኑ በስደተኛነት እስካልተመዘገቡ ወይም ጥገኝነት ጠያቂ እስካልሆኑ ድረስ በአገሪቱ መቆየት ስለማይችሉ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ ተናግረዋል፡፡
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኤጀንሲን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ እ.ኤ.አ በ2013 ብቻ 53 ሺህ 941 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የመን ገብተዋል፡፡

1. ጁሊዮ ሴዛር
2. ካይሎር ናቫስ
3. ማኑዌል ኑዌር
4. ጉሌርሞ ኦቾ
5.ቪንሰንት ኢንየማ
6. ቲም ሀዋርድ

ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር በእያንዳንዱ የዓለም ዋንጫ ስድስት ልዩ  ልዩ ሽልማቶችን በተለያዩ ዘርፎ ለሚመረጡ ተጨዋቾች እና ቡድኖች ያበረክታል፡፡  ለምርጥ በረኛ የወርቅ ጓንት፤ ለኮከብ ግብ አግቢ የወርቅ ጫማና ለኮከብ ተጨዋች የወርቅ ኳስ  የሚሰጡት ሶስትይ ሽልማቶች ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ በዓለም ዋንጫ አብይ ስፖንሰርነት የሚታወቀው አዲዳስ የወርቅ ኳስ እና የወርቅ ጫማ ሽልማቶችን በኩባንያው  ስም ያበረክታል፡፡ በሶስቱም ሽልማቶች በተጨማሪ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ደረጃ ለሚያገኙት ተጨዋቾች የብር እና የነሐስ  ሽልማቶች ይሰጣሉ፡፡ በዓለም ዋንጫ በሁለተኛ ደረጃ የሚታዩ ሌሎች ሶስት የክብር ሽልማቶችም አሉ፡፡ የዓለም ዋንጫ ምርጥ ተጨዋች፤ የዓለም ዋንጫው ምርጥ ስፖርታዊ ጨዋነት እና የዓለም ዋንጫው ምርጥ ቡድን የሚሸለሙባቸው ናቸው፡፡ የዓለም ዋንጫ ምርጥ ወጣት ተጨዋች ምርጫ ለመጀመርያ ጊዜ የተካሄደው በ1958 እኤአ ቢሆንም በደንበኛ ትኩረት መሸለም የተጀመረው በ2006 እኤአ ላይ ጀርመን ባዘጋጀችው 18ኛው የዓለም ዋንጫ ሲሆን የጀርመኑ ሉካስ ፖዶልስኪ ቀዳሚው ተሸላሚ ነበር፡፡ የዚህ ሽልማት ስፖንሰር የመኪና አምራቹ ሃዩንዳይ ኩባንያ ነው፡፡ በ2010 እኤአ በተደረገው 19ኛው የዓለም ዋንጫ ደግሞ የጀርመኑ ቶማስ ሙለር ተሸልሞበታል፡፡ የዓለም ዋንጫው የስፖርታዊ ጨዋነት አሸናፊን መሸለም የተጀመረው በ1970 እኤአ ላይ ነው፡፡ ከ4 ዓመት በፊት የስፖርታዊ ጨዋነት ሽልማቱን የወሰደው ሻምፒዮኑ የስፔን ብሄራዊ ቡድን ነበር፡፡ የዓለም ዋንጫው ምርጥ ቡድን ደግሞ ከ1994 እኤአ ወዲህ ሲሸለም ቆይቷል፡፡


በጎል ፌሽታው፤ ማን ብዙ አግብቶ ይጨርሳል?
20ኛው ዓለም ዋንጫ በጎሎች ብዛት የምንግዜም ምርጥ በመሆን ላይ ነው፡፡ ከሩብ ፍፃሜ በፊት በተደረጉ 56 ጨዋታዎች 154 ጎሎች ተመዝግበዋል፡፡  በየጨዋታው በአማካይ 2.75 ጎል እየገባ ነው፡፡ በዓለም ዋንጫ 64 ጨዋታዎች መደረግ ከጀመረበት ከ1986 እኤአ ወዲህ ዘንድሮ ከፍተኛው የጎል ብዛት እንደሚመዘገብ ተጠብቋል፡፡ በ1994 እ.ኤ.አ 171፤ በ2002 እ.ኤ.አ 161፤ በ2006 እ.ኤ.አ 147 እንዲሁም በ2010 እ.ኤ.አ 145 ጎሎች በ64 ጨዋታዎች ተመዝግበዋል፡፡ ትናንት ከተጀመሩት ሁለት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች በፊት የኮከብ ግብ አግቢነቱን ሲመራ የነበረው በ4 ጨዋታዎች አምስት ጎሎች ከመረብ ያዋሃደው የኮሎምቢያው ጀምስ ሮድሪጌዝ ነው። በ4 ጎሎቻቸው የሚከተሉት ደግሞ የአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ፤ የጀርመኑ ቶማስ ሙለር እና የብራዚሉ ኔይማር ዳሲልቫ ናቸው፡፡ እያንዳንዳቸው 3 ጎሎች ያስመዘገቡ 5 ተጨዋቾች ናቸው፡፡ ቡድኖቻቸው ወደ ሩብ ፍፃሜ በማለፋቸው በፉክክር የሚቆዩት የሆላንዶቹ ቫንፕርሲ እና ሮበን እንዲሁም የፈረንሳዩ ካሬም ቤንዜማ ናቸው፡፡ የኢኳደሩ ኢነር ቫሌንሽያ እና የስዊዘርላንዱ ሻኪሪ 3 ጎሎች ቢኖራቸውም ቡድኖቻቸው ሩብ ፍፃሜ ባለመድረሳቸው ከፉክክር ውጭ ሆነዋል፡፡ 2 ጎሎች በማስመዝገብ ስማቸው የተመዘገበላቸው 16 ተጨዋቾች ሲሆኑ አንድ ጎል ያገቡት ደግሞ 88 ተጨዋቾች ናቸው፡፡
በዓለም ዋንጫው ኮከብ ግብ አግቢነት ለወርቅ ጫማ ሽልማት የሚበቃው ተጨዋች በጎሎቹ ብዛት የሚመረጥ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ የጎል ብዛት የሚጨርሱ ተጨዋቾች ከአንድ በላይ ከሆኑ ደግሞ አሸናፊው የሚለየው ለጎል የበቁ ኳሶችን በብዛት ማን አቀብሏል ተብሎ ነው፡፡ በግብ ብዛትና ለጎል የበቁ ኳሶችን በማቀበል እኩል የሆኑ ተጨዋቾች ከሁለት በላይ ከሆኑ ደግሞ አሸናፊነቱ አነስተኛ ደቂቃዎች ተሰልፎ ብዙ ላገባው ተጨዋች የሚሰጥ ይሆናል፡፡
የወርቅ ጫማ አሸናፊ ሽልማት በሁሉም ዓለም ዋንጫዎች ሲሸለም የቆየ ነው፡፡ በ20ኛው ዓለም ዋንጫ ባገባው ጎል አዲስ ታሪክ የሰራው ተጨዋች የ36 ዓመቱ ጀርመናዊ አጥቂ ሚሮስላቭ ክሎሰ ነው፡፡ በዚህ ዓለም ዋንጫ የውድድሩ የምንግዜም ከፍተኛ ጎል አግቢ ሊሆን የሚችልበት እድል ይዞ መሳተፍ የጀመረው ሚሮስላቭ ክሎሰ ከጀርመን ብሄራዊ ቡድን ጋር በተሳተፈባቸው 3 የዓለም ዋንጫዎች 14 ጎሎች ነበሩት፡፡ ጀርመን ከጋና ባደረጉት ጨዋታ ላይ ተቀይሮ ከገባ በኋላ 15ኛውን ጎል አስመዘገበ፡፡  በዚህም የዓለም ዋንጫ የምንግዜም ከፍተኛ ግብ አግቢ  ከነበረው ብራዚላዊው ሊውስ ናዛርዮ ዴሊማ ጋር ክብረወሰኑን ተጋርቷል፡፡ ከሩብ ፍፃሜው በኋላ ሚሮስላቭ ክሎስ አንድ ተጨማሪ ጎል ካስመዘገበ የዓለም ዋንጫ የምንግዜም ከፍተኛ ግብ አግቢ ለመሆን ይችላል፡፡



በረኞች ያልተዘመረላቸው የእግር ኳስ ጀግኖች
20ኛው የዓለም ዋንጫ ላይ  በርካታ ጎሎች ሲመዘገቡ መቆየታቸው የበረኞችን ብቃት አጠያያቂ ቢያደርገውም ቢያንስ ስምንት በረኞች በየቡድኖቻቸው አስገራሚ ብቃት አሳይተዋል፡፡  እነዚህ በረኞች በወሳኝ ጨዋታዎች ያለቀላቸውን የግብ እድሎች ሲያመክኑ፤ ቡድኖቻቸውን በአምበልነት በመምራት የሚደነቅ አስተዋፅኦ ሲያበረክቱ፤ የቡድኖችን ውጤት ለማስጠበቅ ከፍተኛ ጥረት ሲያሳዩ፤ በጥሎ ማለፍ በተከሰቱ የመለያ ምቶችን በማዳን  ውጤቶችን ሲወስኑ ሰንብተዋል፡፡ በእርግጥ በእግር ኳስ ስፖርት  በኮከብ ተጨዋችነት ብዙውን ጊዜ  ለአጥቂዎች እና ለአማካዮች ትኩረት የሚሰጥ ቢሆንም ፤ በዚህ ዓለም ዋንጫ በረኞች  በምርጥ አቋማቸው ለቡድናቸው የኮከብነት ሚና እንደሚኖራቸው ተረጋግጧል፡፡ በርካታ ስፖርት አፍቃሪዎች ከበረኞች ስህተት የመጠበቅ ልማድ አለባቸው፡፡ በየጨዋታው በረኞችን አንድ ስህተት ሲያጋጥማቸው ወይም ጎል ሲገባባቸው ለቡድናቸው ሽንፈት ተጠያቂ ያደርጓቸዋል፡፡   አጥቂዎች ብዙ ጎሎችን ሲስቱ የሚደርስባቸው ወቀሳ ግን ያን ያህል ነው። ለበረኞች ሚና አነስተኛ ትኩረት እንደሚሰጥ በብራዚላዊው ጁሊዮ ሴዛር ላይ የተከሰተውን ሁኔታ እንደ ማስረጃ መጥቀስ ይቻላል፡፡ በብራዚል ለግብ ጠባቂዎች ብዙም አድናቆት የለም፤ እንደውም አንዳንድ ስፖርት አፍቃሪዎች ጁሊዮ ሴዛርን “ዶሮው ሰውዬ” እያሉ ያሾፉበታል፡፡ ብራዚል በጥሎ ማለፍ ከቺሊ ጋር ባደረገችው ጨዋታ ላይ ግን አዘጋጇን አገር ከውድቀት ያዳነው እሱ ነበር፡፡ ከብራዚልና ቺሊ ጥሎ የሚያልፈው ቡድን በመለያ ምቶች ሲታወቅ ሁለት ኢሊጎሬዎችን በማዳን ጁሊዮ ሴዛር የእለቱ ኮከብ ነበር፡፡ በዚህ ጀግንነቱም ከሌሎች ምርጥ ተጨዋቾች ይልቅ ትኩረት ተሰጥቶት ተደጋጋሚ ቃለምልልሶች አድርጓል፡፡  “በፊት የሚያናግረኝ አልነበረም፤ አሁን  ሁሉም አስተያየቴን ስለሚጠይቅ በጣም ደስ ብሎኛል” በማለት ጁሊዮ ሴዛር እያነባ ተናግሯል፡፡
በ20ኛው ዓለም ዋንጫ የታየ ምርጥ በረኛ የብራዚሉ ጁሊዮ ሴዛር ብቻ አይደለም፡፡  ቡድኖቻቸውን ለሩብ ፍፃሜ በማብቃት ጉልህ ሚና ከነበራቸው ምርጥ በረኞች የቤልጅዬሙ ቲቦልት ኮርትዬስ፤ የኮስታሪካው ኬዬሎር ናቫስ፤ የኮሎምቢያው ዴቪድ ኦስፒና፤ የአርጀንቲናው ሰርጂዮ ሮሜሮ፤ የፈረንሳዩ ሁጎ ሎሪስና የጀርመኑ ማንዌል ኑዌር ዋናዎቹ ተጠቃሾች ናቸው።  ከምድብ ጨዋታዎች እስከ ጥሎ ማለፉ  ቡድኖቻቸውን በአስገራሚ ብቃታቸው ያገለገሉ ሌሎችም ምርጥ በረኞች ነበሩ፡፡ የአሜሪካው ቲም ሃዋርድ፤ የናይጄርያው ቪንሰንት ኢኒዬማ እንዲሁም  የቺሊው  ጉሌርሞ ኦቾ  ናቸው፡፡ የዓለም ዋንጫ ኮከብ በረኛ ሆኖ የወርቅ ጓንት ለመሸለም የሚበቃው ከእነዚህ ምርጥ ግብ ጠባቂዎች አንዱ መሆኑ አይቀርም፡፡ በምድብ ማጣርያው በ3 ጨዋታዎች ግብ ሳይገባበት አንደኛ ደረጃ የተሰጠው የፈረንሳዩ ሁጎ ሎሪስ ነው፡፡ የ22 ዓመቱ የቤልጅዬም በረኛ ቲቦልት ኮርትዬስ  ወደ ጎል ከሚሞከሩ ኳሶች 87 በመቶውን  በማዳን ተደንቋል፡፡ የጀርመኑ ማኑዌል ኑዌር ደግሞ በዓለም ዋንጫው  ፍፁም ቅጣት ምት በማዳን 29 በመቶ ብቃት አስመዝግቧል፡፡ ማኑዌል ኑዌር ከሌሎቹ ምርጥ በረኞች ልዩ የሚያደርገው  ከግብ ክልል ውጭ እንቅስቃሴ በማድረግ  እንደሊብሮ ተጨዋች ማገልገሉ ነው፡፡ ይህ የማንዌል ኑዌር ብቃት በተለይ ጀርመንና አልጄርያ ባደረጉት ጨዋታ  የታየ ነበር፡፡
የአሜሪካው ግብ ጠባቂ ቲም ሃዋርድ አገሩ ከቤልጅዬም ጋር ባደረገችው ጨዋታ 15 ያለቀላቸው የግብ ሙከራዎችን አድኖ በውድድሩ ታሪክ አዲስ ክበረወሰን ተመዝግቦለታል፡፡ ከ4 ዓመት በፊት ደቡብ አፍሪካ ባስተናገደችው ኛው የዓለም ዋንጫ በረኞች የአዲዳስ ምርት በሆነችው ጃቡላኒ የተባለች ኳስ ምርጥ ብቃታቸውን ለማሳየት አልታደሉም ነበር፡፡ ዘንድሮ ግን በብራዙካ ኳስ አንድም በረኛ ሲቸገር አልታየም፡፡
የፊፋ ቴክኒክ ቡድን የዓለም ዋንጫውን ኮከብ በረኛ በውድድሩ ላይ ባሳየው አጠቃላይ ብቃት መሰረት መርጦ ለሽልማት ያበቃዋል፡፡ የዓለም ዋንጫ ምርጥ በረኛ ከ1994 እኤአ ወዲህ በታዋቂው ራሽያዊ ግብ ጠባቂ ሌቭ ያሺን መታሰቢያነት የሚሸለም ነበር፡፡ ከ2010 እኤአ በኋላ ግን የወርቅ ጓንት ሽልማት ተብሎ ለአሸናፊው መበርከት ጀምሯል፡፡


በ1ኛው ዓለም ዋንጫ የኡራጋዩ ኢነሪኬ ባሌስትሮ
በ2ኛው የዓለም ዋንጫ የስፔኑ ሪካርዶ ዛሞራ
በ3ኛው የዓለም ዋንጫ የኡራጋዩ ሮክዌ ማስፖሊ
በ4ኛው የዓለም ዋንጫ የቼኮስላቫኪያው ፍራንቲሴክ ፕላኒካ
በ5ኛው የዓለም ዋንጫየሃንጋሪው ጉዮላ ግሮሲክስ
በ6ኛው የዓለም ዋንጫ  የሰሜን አየርላንዱ ሃሪ ግሬግ
በ7ኛው የዓለም ዋንጫ የቼኮስላቫኪያው ቪሊያም ሽኮሪጄፍ
በ8ኛው የዓለም ዋንጫ የእንግሊዙ ጎርደን ባንክስ
በ9ኛው የዓለም ዋንጫ የኡራጋዩ ላዲሳሎ ማዙሪኪኤውሲዝ
በ10ኛው የዓለም ዋንጫ የምዕራብ ጀርመኑ ሴፕ ማዬር
በ11ኛው የዓለም ዋንጫ የአርጀንቲናው ኡባልዶ ፊሎል
በ12ኛው የዓለም ዋንጫ የጣሊያኑ ዲኖ ዞፍ
በ13ኛው የዓለም ዋንጫነየቤልጅዬሙ ጂን ማርዬ ፕፋፍ
በ14ኛው የዓለም ዋንጫ የኮስታሪካው ሊውስ ጋቤሎና የአርጀንቲናው ሰርጂዮ ጎይኮቻ
በ15ኛው የዓለም ዋንጫ የቤልጅዬሙ ሚሸል ፕሩድሜ
በ16ኛው የዓለም ዋንጫ የፈረንሳዩ ፋብያን ባርቴዝ
በ17ኛው የዓለም ዋንጫ የጀርመኑ ኦሊቨር ካን
በ18ኛው የዓለም ዋንጫ የጣሊያኑ ጂያንሉጂ ቡፎን
በ19ኛው የዓለም ዋንጫ የስፔኑ ኤከር ካስያስ
በጎል ፌሽታው፤ ማን ብዙ አግብቶ ይጨርሳል?
20ኛው ዓለም ዋንጫ በጎሎች ብዛት የምንግዜም ምርጥ በመሆን ላይ ነው፡፡ ከሩብ ፍፃሜ በፊት በተደረጉ 56 ጨዋታዎች 154 ጎሎች ተመዝግበዋል፡፡  በየጨዋታው በአማካይ 2.75 ጎል እየገባ ነው፡፡ በዓለም ዋንጫ 64 ጨዋታዎች መደረግ ከጀመረበት ከ1986 እኤአ ወዲህ ዘንድሮ ከፍተኛው የጎል ብዛት እንደሚመዘገብ ተጠብቋል፡፡ በ1994 እ.ኤ.አ 171፤ በ2002 እ.ኤ.አ 161፤ በ2006 እ.ኤ.አ 147 እንዲሁም በ2010 እ.ኤ.አ 145 ጎሎች በ64 ጨዋታዎች ተመዝግበዋል፡፡ ትናንት ከተጀመሩት ሁለት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች በፊት የኮከብ ግብ አግቢነቱን ሲመራ የነበረው በ4 ጨዋታዎች አምስት ጎሎች ከመረብ ያዋሃደው የኮሎምቢያው ጀምስ ሮድሪጌዝ ነው። በ4 ጎሎቻቸው የሚከተሉት ደግሞ የአርጀንቲናው ሊዮኔል
በ1ኛው ዓለም ዋንጫ  በ8 ጎሎች የኡራጋዩ ጉሌርሞ ስታብል
በ2ኛው የዓለም ዋንጫ በ5 ጎሎች የቼኮስሎቫኪያው ኦሊድሪች
በ3ኛው የዓለም ዋንጫ በ7 ጎሎች የብራዚሉ ሊዮኒዴስ
በ4ኛው የዓለም ዋንጫ በ8 ጎሎች የብራዚሉ አዴሚር
በ5ኛው የዓለም ዋንጫ በ11 ጎሎች የሃንጋሪው ሳንዶር ኮሲስ
በ6ኛው የዓለም ዋንጫ በ13 ጎሎች የፈረንሳዩ ጀስት ፎንታይኔ
በ7ኛው የዓለም ዋንጫ በእኩል 4 ጎሎች የብራዚሎቹ ጋሪንቻና ቫቫ፤ የዩጎስላቪያው ድራዛን ጄርኮቪች እና የቺሊ ሊዮኔል ሳንቼዝ
በ8ኛው የዓለም ዋንጫ በ9 ጎሎች የፖርቱጋሉ ዩዞብዮ
በ9ኛው የዓለም ዋንጫ በ10 ጎሎች የጀርመኑ ገርድ ሙለር
በ10ኛው የዓለም ዋንጫ በ7 ጎሎች የፖላንዱ ግሬጎርዝ ላቶ
በ11ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የአርጀንቲናው ማርዮ ኬምፐስ
በ12ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የጣሊያኑ ፓውሎ ሮሲ
በ13ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የእንግሊዙ ጋሪ ሊንከር
በ14ኛው በ6 ጎሎች የጣሊያኑ ሳልቫቶሪ ስኪላቺ
በ15ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የሩስያው ሳሌንኮና የቡልጋሪያው ስቶችኮቭ
በ16ኛው የዓለም ዋንጫ በ6 ጎሎች የክሮሽያው ዳቮር ሱከር
በ17ኛው የዓለም ዋንጫ በ8 ጎሎች የብራዚሉ ሮናልዶ
በ18ኛው የዓለም ዋንጫ በ5 ጎሎች የጀርመኑ ሚሮስላቭ ክሎሰ
በ19ኛው የዓለም ዋንጫ በ5 ጎሎች የጀርመኑ ቶማስ ሙለር

ኮከብ ተጨዋች ከዋንጫው አሸናፊ ይገኛል
የዓለም ዋንጫው ኮከብ ተጨዋች ለማወቅ እስከ ዋንጫው ጨዋታ መጠበቅ ይጠይቃል፡፡ ከሩብ ፍፃሜው በፊት ለዚህ ሽልማት እጩ ተፎካካሪ እንደሚሆኑ የተነገረላቸው በምርጥ ጎሎቻቸው የተደነቁት የሆላንዱ ቫን ፒርሲ እና የኮሎምቢያው ጄምስ ሮድሪጌዝ ናቸው፡፡ የብራዚሉ ኔይማርና የአርጀንቲናው ሊዮኔል ሜሲ ቡድኖቻቸውን ለዋንጫ የሚያበቁ ከሆነም ለሽልማቱ ግንባር ቀደም እጩዎች ይሆናሉ፡፡ የዓለም ዋንጫ ኮከብ ተጨዋች የሚሸለመው የወርቅ ኳስ ሲሆን ምርጫውን የሚያከናውኑት ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች እና ፊፋ ናቸው፡፡

በ1ኛው ዓለም ዋንጫ የኡራጋዩ ጆሴ ናሳዚ
በ2ኛው የዓለም ዋንጫ የጣሊያኑ ጁሴፔ ሜዛ
በ3ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ሊዮኒዴስ
በ4ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ዚዝንሆ
በ5ኛው የዓለም ዋንጫ የሃንጋሪው ፌርኔክ ፑሽካሽ
በ6ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ዲዲ
በ7ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ጋሪንቻ
በ8ኛው የዓለም ዋንጫ የእንግሊዙ ቦቢ ቻርልተን
በ9ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ፔሌ
በ10ኛው የሆላንዱ ዮሃን ክሩፍ
በ11ኛው የአርጀንቲናው ማርዮ ኬምፐስ
በ12ኛው የጣሊያኑ ፓውሎ ሮሲ
በ13ኛው የአርጀንቲናው ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና
በ14ኛው የጣሊያኑ ሳልቫቶሬ ስኪላቺ
በ15ኛው የብራዚሉ ሮማርዮ
በ16ኛው የዓለም ዋንጫ የብራዚሉ ሮማርዮ
በ17ኛው የጀርመኑ ኦሊቨር ካን
በ18ኛው የፈረንሳዩ ዚነዲን ዚዳን
በ19ኛው የኡራጋዩ ዲያጎ ፎርላን

ቢዮንሴ የመጀመሪያዋ ሆናለች
ዘፋኞች ዘንድሮም ቀዳሚነቱን ይዘዋል

ታዋቂው ፎርብስ መጽሄት በየአመቱ እንደሚያደርገው ሁሉ ዘንድሮም በሙዚቃ፣ በፊልም፣ በስፖርት፣ በሞዴሊንግ፣ በስነጽሁፍና በሌሎች መስኮች ተሰማርተው የሚገኙ ስኬታማ የ2014 የዓለማችን መቶ ሃያላን ዝነኞችን ዝርዝር በሳምንቱ መጀመሪያ ይፋ አድርጓል፡፡
ፎርብስ ለ15ኛ ጊዜ ያወጣው የዘንድሮው ዝርዝር እንደሚያሳየው፣ ታዋቂዋ ድምጻዊት ቢዮንሴ ኖውልስ ከአለማችን ዝነኞች ሁሉ በሃያልነቷ አቻ አልተገኘላትም፡፡ ለ32 አመቷ የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ አመቱ የገድ እንደነበር የገለጸው ፎርብስ፣ በገፍ የተቸበቸበላትን በስሟ የሰየመችውን አልበም ለአድማጮቿ ያቀረበችበትና ስኬታማ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን በተለያዩ የአለም አገራት የሰራችበት ወቅት እንደነበርም ጠቅሷል፡፡
ቢዮንሴ በሙዚቃው መስክ ካስመዘገበችው ስኬት በተጨማሪ ያቋቋመችውን የአልባሳት አምራች ኩባንያ በመምራትና ፔፕሲን ከመሰሉ ታዋቂ የዓለማችን ኩባንያዎች ጋር በፈጠረችው አጋርነት ተጠቃሽ ስራ በማከናወኗ በዘንድሮ ዓመት 115 ሚሊዮን ዶላር ያህል ገቢ ለማግኘት ችላለች። ፎርብስም ድምጻዊቷን በአመቱ ባስመዘገበችው ስኬቷ መሰረት የአለማችን ቁጥር 1 ሃያል ዝነኛ አድርጓታል፡፡
እሷን ተከትሎ የሁለተኛነትን ስፍራ የያዘው አሜሪካዊው የቅርጫት ኳስ ተጫዋች ሊብሮን ጄምስ ሲሆን፣ በአመቱ ከማናቸውም ዝነኞች በላይ የሆነ 620 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንዳገኘ የተነገረለት ድምጻዊው ዶክተር ድሬ ሶስተኛ ሆኗል፡፡
ባለፈው አመት የፎርብስ ዝርዝር የዓለማችን ሃያላን ዝነኞች ቁንጮ የነበረችው ጥቁር አሜሪካዊቷ የቶክ ሾው አዘጋጅ ኦፕራ ዊንፍሬይ፣ ዘንድሮ በእነዚህ በሶስቱ ተቀድማ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ሚስቱን ቢዮንሴን ከሁሉም ፊት ያደረገው ድምጻዊው ጄይ ዚ ደግሞ፣ በስድስተኛነት ይገኛል፡፡
ዝነኞቹ በ2014 ብቻ ያገኙትን ገቢ በተመለከተ ፎርብስ ባወጣው መረጃ እንዳለው፤ ቢዮንሴ 115 ሚ፣ ሊቦርን ጄምስ 72 ሚ፣ ዶክተር ድሬ 620 ሚ የአሜሪካ ዶላር ገቢ አግኝተዋል፡፡
እንደ አምናው ሁሉ ዘንድሮም ዘፋኞች በላይነቱን የያዙበት የፎርብስ ዝርዝር እንደሚለው፣ ድምጻውያን በአልበም ሽያጭ፣ በኮንሰርትና በመሳሰሉ መንገዶች ጠቀም ያለ ገንዘብ ከማግኘት በተጨማሪ፣ ማህበራዊ ድረገጾችን በመጠቀም እውቅናቸውን በማስፋት ረገድ በአመቱ ስኬታማ ነበሩ፡፡
ፎርብስ የአመቱን ሃያላን በመምረጡ ሂደት የግለሰቦቹን የሃብትና የዝና መጠኖችን፣ የተሰሚነትና በመዝናኛው ኢንዱስትሪ ላይ ያላቸውን የተጽዕኖ ፈጣሪነት ደረጃ እንደ መስፈርት የተጠቀመ ሲሆን፣ ዝነኞቹ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ ምን ያህል ጊዜ በህትመትና በኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ስማቸው ተጠቅሷል የሚለውንም ለማወዳደሪያነት ተጠቅሞበታል፡፡
በተለያዩ የመዝናኛው ኢንዱስትሪ መስክ የተሰማሩ የአለማችን 100 ዝነኞች በተካተቱበት በዘንድሮው የፎርብስ ዝርዝር፣ በቀዳሚነት ከተቀመጡት 25 ዝነኞች መካከል ቢዮንሴ፣ ሪሃና፣ ቡርኖ ማርስ፣ ሌዲ ጋጋ፣ ካንያ ዌስትና ቴለር ስዊፍትን ጨምሮ 13 ያህሉ ድምጻውያን ናቸው፡፡
በ2014 የፎርብስ የአለማችን 100 ሃያላን ዝነኞች ዝርዝር ውስጥ እስከ አስረኛ ደረጃ ከያዙት መካከል አምስቱ ሴቶች ሲሆኑ፣ ሰባቱ ደግሞ አፍሪካ አሜሪካውያን ናቸው ተብሏል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት መካከል፤ ድምጻዊው ቡርኖ ማርስ፣ የፊልም ተዋንያኑ ብራድሊ ኩፐርና ቪን ዲዝል፣ ሞዴል ኬት አፕተንና ደራሲ ቬሮኒካ ሮዝ ይገኙበታል፡፡
አምና በዝርዝሩ ውስጥ የነበሩና ዘንድሮ ካልቀናቸው መካከልም፤ ታዋቂዋ ድምጻዊት ማዶና፣ እግር ኳስ ተጫዋቹ ዴቪድ ቤካም፣ የፊልም ተዋናዩ ቶም ክሩዝና የቴሌቪዥን ቶክ ሾው አዘጋጁ ዴቪድ ሌተርማን ይጠቀሳሉ፡፡

ታዋቂው የፒያኖ ተጫዋችና የሙዚቃ ቀማሪ ግርማ ይፍራሸዋ ‘ላቭ ኤንድ ፒስ’ የሚል ርዕስ ያለውን አዲስ የፒያኖ ሙዚቃ አልበሙን በዚህ ወር መጨረሻ አሜሪካ ውስጥ በሚያቀርበው ኮንሰርት ያስመርቃል፡፡
በሜሪላንድ ቤተሳዳ ውስጥ በሚገኘው ‘ቤተሰዳ ብሉዝ ኤንድ ጃዝ ሱፐር ክለብ’ በሚከናወን ስነስርዓት የሚመረቀው አልበሙ፣ ቀረጻ ባለፈው አመት ኒውዮርክ ብሮክሊን ውስጥ መጠናቀቁን የዘገበው ታዲያስ መጽሄት፤ አልበሙን ለገበያ ያቀረበው ‘አንሲን ሪከርድስ’ የተባለው ታዋቂ የሙዚቃ አሳታሚ ኩባንያ መሆኑን ገልጿል፡፡
‘አምባሰል’፣ ‘ጨዋታ’፣ ‘ሰመመን’ና ‘እልልታ’ን ከመሳሰሉ በአገርኛ የሙዚቃ ስልቶች የተቀመሩ የሙዚቀኛውን ወጥ ስራዎች በያዘው በዚህ አልበም፤ በታዋቂው ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ሰው በፕሮፌሰር አሸናፊ ከበደ የተደረሰው ‘ባለ ዋሽንቱ እረኛ’ የተባለ ተወዳጅ ሙዚቃ በግርማ እንደገና ተሰርቶ እንደተካተተበት ተነግሯል፡፡
በቡልጋሪያ፣ በለንደን ሮያል የሙዚቃ አካዳሚና ጀርመን ውስጥ በሚገኘው ሌፕዚግ የሙዚቃና የቲያትር ተቋም ትምህርቱን የተከታተለው ግርማ ይፍራሸዋ፤ በተለያዩ የአለም አገራት በተዘጋጁ ኮንሰርቶች የሙዚቃ ስራዎቹን በማቅረብ የሚታወቅ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓትም የኢትዮጵያንና የክላሲካል ሙዚቃን ለማስተዋወቅ በአፍሪካና በአውሮፓ አገራት እየተዘዋወረ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ተዘግቧል፡፡

በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን “የልጆች ፕሮግራም”  ተረት በማቅረብ ህፃናትን ለረጅም አመታት ያዝናኑትና ያስተማሩት እንዲሁም በተዋናይነታቸው የሚታወቁት አርቲስት ተስፋዬ ሳህሉ (አባባ ተስፋዬ) 91ኛ ዓመት የልደት በዓል ዛሬ ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ በእቴጌ ጣይቱ ሆቴል እንደሚከበር ተገለፀ፡፡
የአባባ ተስፋዬን የልደት በዓል ያዘጋጁት ቤተሰቦቻቸውና “ልጆች ኢንተርቴይንመንት” ሲሆኑ አርቲስቶች፣ ታዋቂ ሰዎችና ጋዜጠኞች በሚታደሙበት በዚህ የልደት በዓል ላይ የተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚካሄዱ ተጠቁሟል፡፡

“windmills of the Gods” የተሰኘው የእንግሊዛዊው ደራሲ የሲድኒ ሼልደን ልቦለድ መጽሐፍ “የፍቅር ፈተና” በሚል በፋንታሁን ኃይሌ /አስኳል/ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ሰሞኑን ለገበያ ቀረበ። በ302 ገፆች የተቀነበበው ልቦለዱ፤ በ50 ብር ከ70 እየተሸጠ ሲሆን መጽሐፉን የሚያከፋፍለው ብርሃኔ መፃህፍት መደብር ነው፡፡